ኢያሱ 19 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 19:1-51

ለስምዖን ነገድ የተመደበው ድርሻ

19፥2-10 ተጓ ምብ – 1ዜና 4፥28-33

1ሁለተኛው ዕጣ ለስምዖን ነገድ በየጐሣ በየጐሣው ወጣ፤ ርስታቸውም ዙሪያውን በይሁዳ ነገድ ርስት የተከበበ ነበር፤ 2ይህም የሚከተሉትን ያካትታል፤

ቤርሳቤህ፣ ሤባ፣ ሞላዳ፣ 3ሐጸር ሹዓል፣ ባላ፣ ዔጼም፣ 4ኤልቶላድ፣ በቱል፣ ሔርማ፣ 5ጺቅላግ፣ ቤትማርካቦት፣ ሐጸርሱሳ፣ 6ቤተ ለባኦትና ሻሩሔን ነበሩ፤ እነዚህ ዐሥራ ሦስት ከተሞችና መንደሮቻቸው ናቸው።

7ዐይን፣ ሪሞን፣ ዔቴርና ዓሻን የተባሉት አራት ከተሞቻቸውና መንደሮቻቸው፣ 8ደግሞም እስከ ባዕላትብኤር ወይም ኔጌብ ውስጥ እስካለው እስከ ራማት ድረስ ባሉት ከተሞች ዙሪያ የሚገኙት መንደሮች ሁሉ ከእነዚሁ ጋር ይጠቃለላሉ።

እንግዲህ በየጐሣው የተደለደለው የስምዖን ነገድ ርስት ይህ ነበር። 9የይሁዳ ነገድ የያዘው ርስት እጅግ ሰፊ ስለ ነበር፣ ከይሁዳ ነገድ ድርሻ ተከፍሎ ለስምዖን ነገድ በርስትነት ተሰጠ። ከዚህ የተነሣም የስምዖን ነገድ በይሁዳ ነገድ ድርሻ ርስት ሊካፈል ቻለ።

ለዛብሎን ነገድ የተመደበው ድርሻ

10ሦስተኛው ዕጣ ለዛብሎን ነገድ በየጐሣ በየጐሣው ወጣ፤

የርስታቸውም ድንበር እስከ ሣሪድ ይደርሳል። 11ወደ ምዕራብም በመሄድ በመርዓላ በኩል ያልፋል፤ ደባሼትን ተጠግቶም በዮቅንዓም አጠገብ እስካለው ወንዝ ድረስ ይዘልቃል። 12ከሣሪድም ወደ ምሥራቅ በመታጠፍ፣ የፀሓይ መውጫ ወደ ሆነው አገር ወደ ኪስሎትታቦር በመዝለቅ እስከ ዳብራት ሄዶ ወደ ያፊዓ ያቀናል። 13ከዚያም ወደ ምሥራቅ በመቀጠል፣ ወደ ጋትሔፍርና ወደ ዒትቃጺን ይዘልቃል፤ ከዚያ ደግሞ ወደ ሪሞን በመሄድ ወደ ኒዓ ይታጠፋል። 14በስተ ሰሜንም በኩል ወደ ሐናቶን ይዞርና በይፍታሕኤል ሸለቆ ላይ ይቆማል።

15ደግሞም ቀጣትን፣ ነህላልን፣ ሺምሮንን፣ ይዳላንና ቤተ ልሔምን ይጨምራል፤ እነዚህም ከነ መንደሮቻቸው ዐሥራ ሁለት ከተሞች ናቸው።

16እነዚህ ሁሉ ለዛብሎን ነገድ ርስት ሆነው ለየጐሣ ለየጐሣው የተደለደሉ ከተሞችና መንደሮቻቸው ነበሩ።

ለይሳኮር ነገድ የተመደበው ድርሻ

17አራተኛው ዕጣ ለይሳኮር ነገድ በየጐሣ በየጐሣው ወጣ፤ 18ምድራቸውም የሚከተሉትን ያካትታል፤

ኢይዝራኤል፣ ከስሎት፣ ሱነም፣ 19ሐፍራይም፣ ሺኦን፣ አናሐራት፣ 20ረቢት፣ ቂሶን፣ አቤጽ፣ 21ሬሜት፣ ዐይንጋኒም፣ ዐይንሐዳ እንዲሁም ቤትጳጼጽ።

22ድንበራቸውም ታቦርና፣ ሻሕጹማን፣ ቤትሳሚስን ይነካና በዮርዳኖስ ላይ ያቆማል።

እነዚህ ከነ መንደሮቻቸው ዐሥራ ስድስት ከተሞች ናቸው።

23እነዚህ ለይሳኮር ነገድ ርስት ሆነው ለየጐሣ ለየጐሣው የተደለደሉ ከተሞችና መንደሮቻቸው ነበሩ።

ለአሴር ነገድ የተመደበው ድርሻ

24አምስተኛ ዕጣ ለአሴር ነገድ በየጐሣ በየጐሣው ወጣ፤ 25ምድራቸውም የሚከተሉትን ያካትታል፤

ሔልቃት፣ ሐሊ፤ ቤጤን፣ አዚፍ፣ 26አላሜሌክ፣ ዓምዓድ እንዲሁም ሚሽአል። ድንበሩ በስተ ምዕራብ ቀርሜሎስንና ሺሖርሊብናትን ይነካል፤ 27ከዚያም በምሥራቅ በኩል ወደ ቤትዳጎን ይመለስና ዛብሎንንና የይፍታሕኤልን ሸለቆ ይዞ፣ ካቡልን በስተ ግራ በመተው በሰሜን በኩል ወደ ቤትዔሜቅና ወደ ንዒኤል ይቃናል። 28በመቀጠልም ወደ ዔብሮን19፥28 አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ነገር ግን ጥቂት ቅጆች ኢያ 21፥30 ይመ፣ አብዩን ይላሉ።፣ ወደ ረአብ፣ እንዲሁም ወደ ሐሞንና ወደ ቃና ሽቅብ ወጥቶ እስከ ታላቁ ሲዶና ይደርሳል። 29ድንበሩ ወደ ራማ ከዞረ በኋላ ወደ ተመሸገው ወደ ጢሮስ ከተማ ታጥፎ ወደ ሖሳ ይመለስና በአክዚብ በኩል ሜድትራኒያን ባሕር ደርሶ ይቆማል፤ 30ይህም የዑማን፣ የአፌቅንና የረአብን ምድር ይጨምራል።

በዚህም ሃያ ሁለት ከተሞችና መንደሮቻቸው ይገኛሉ።

31እነዚህ ለአሴር ነገድ ሆነው በየጐሣው የተደለደሉ ከተሞችና መንደሮቻቸው ነበሩ።

ለንፍታሌም ነገድ የተመደበው ድርሻ

32ስድስተኛው ዕጣ ለንፍታሌም ነገድ በየጐሣ በየጐሣው ወጣ፤

33ድንበራቸውም ከሔሌፍና በጸዕነኒም ካለው ከትልቁ የወርካ ዛፍ ይነሣና በአዳ ሚኔቄብና በየብኒኤል ዐልፎ ወደ ለቁም በመምጣት ዮርዳኖስ ላይ ይቆማል፤ 34ድንበሩ በአዝኖት ታቦር ያልፍና ወደ ምዕራብ በመታጠፍ ሑቆቅ ላይ ይቆማል፤ ይኸው ድንበር በደቡብ ዛብሎንን፣ በምዕራብ አሴርን፣ በምሥራቅ ዮርዳኖስን ይነካል19፥34 የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ከዚህ ጋር ይስማማል፤ ነገር ግን የዕብራይስጡ ቅጅ ምሥራቅ ይሁዳንና ዮርዳኖስን ይከብባል ይላል።

35የተመሸጉትም ከተሞች እነዚህ ናቸው፤ ጺዲም፣ ጼር፣ ሐማት፣ ረቃት፣ ኬኔሬት፣ 36አዳማ፣ ራማ፣ አሦር፣ 37ቃዴስ፣ ኤድራይ፣ ዐይንሐጾር፣ 38ይርኦን፣ ሚግዳልኤል፣ ሖሬም፣ ቤትዓናትና ቤትሳሚስ።

እነዚህ ከነ መንደሮቻቸው ዐሥራ ዘጠኝ ከተሞች ናቸው።

39እነዚህ ለንፍታሌም ነገድ ርስት ሆነው በየጐሣው የተደለደሉ ከተሞችና መንደሮች ነበሩ።

ለዳን ነገድ የተመደበው ድርሻ

40ሰባተኛው ዕጣ ለዳን ነገድ በየጐሣው ወጣ፤ 41የወረሱትም ምድር የሚከተሉትን ያካትታል፤

ጾርዓ፣ ኤሽታኦል፣ ዒርሼሜሽ፣ 42ሸዕለቢን፣ ኤሎን፣ ይትላ፣ 43ኤሎን፣ ተምና፣ አቃሮን፣ 44ኢልተቄ፣ ገባቶን፣ ባዕላት፣ 45ይሁድ፣ ብኔብረቅ፣ ጋትሪሞን፣ 46ሜያርቆንና በኢዮጴ ፊት ለፊት ያለው ርቆን።

47ነገር ግን የዳን ዘሮች ርስታቸው አልበቃቸውም፣ ወደ ሌሼም ወጥተው አደጋ በመጣል ያዟት፤ ሰዎቹንም በሰይፍ ስለት ፈጅተው ይዞታቸው አደረጓት፤ በዚያው ሰፈሩ፤ ስሟንም ለውጠው በአባታቸው ስም ዳን አሏት።

48እነዚህ ለዳን ነገድ ርስት ሆነው በየጐሣው የተደለደሉ ከተሞችና መንደሮች ነበሩ።

ለኢያሱ የተመደበው ድርሻ

49እስራኤላውያን ድርሻ ድርሻቸውን ከያዙ በኋላ፣ ለነዌ ልጅ ለኢያሱ በመካከላቸው ርስት ሰጡት፤ 50እግዚአብሔር ባዘዘውም መሠረት በኰረብታማው የኤፍሬም ምድር የምትገኘውን ተምናሴራ የምትባለውን የፈለጋትን ከተማ ሰጡት፤ እርሱም ከተማዪቱን ሠራ፤ መኖሪያውም አደረጋት።

51እንግዲህ ካህኑ አልዓዛር፣ የነዌ ልጅ ኢያሱና የእስራኤል ነገድ የየጐሣ መሪዎች ሴሎ ላይ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ፣ በእግዚአብሔር ፊት ዕጣ ያደላደሉት ርስት ይህ ነው፤ የምድሪቱንም አከፋፈል በዚህ ሁኔታ ፈጸሙ።

King James Version

Joshua 19:1-51

1And the second lot came forth to Simeon, even for the tribe of the children of Simeon according to their families: and their inheritance was within the inheritance of the children of Judah. 2And they had in their inheritance Beer-sheba, or Sheba, and Moladah, 3And Hazar-shual, and Balah, and Azem, 4And Eltolad, and Bethul, and Hormah, 5And Ziklag, and Beth-marcaboth, and Hazar-susah, 6And Beth-lebaoth, and Sharuhen; thirteen cities and their villages: 7Ain, Remmon, and Ether, and Ashan; four cities and their villages: 8And all the villages that were round about these cities to Baalath-beer, Ramath of the south. This is the inheritance of the tribe of the children of Simeon according to their families. 9Out of the portion of the children of Judah was the inheritance of the children of Simeon: for the part of the children of Judah was too much for them: therefore the children of Simeon had their inheritance within the inheritance of them.

10¶ And the third lot came up for the children of Zebulun according to their families: and the border of their inheritance was unto Sarid: 11And their border went up toward the sea, and Maralah, and reached to Dabbasheth, and reached to the river that is before Jokneam; 12And turned from Sarid eastward toward the sunrising unto the border of Chisloth-tabor, and then goeth out to Daberath, and goeth up to Japhia, 13And from thence passeth on along on the east to Gittah-hepher, to Ittah-kazin, and goeth out to Remmon-methoar to Neah;19.13 methoar: or, which is drawn 14And the border compasseth it on the north side to Hannathon: and the outgoings thereof are in the valley of Jiphthah-el: 15And Kattath, and Nahallal, and Shimron, and Idalah, and Beth-lehem: twelve cities with their villages. 16This is the inheritance of the children of Zebulun according to their families, these cities with their villages.

17And the fourth lot came out to Issachar, for the children of Issachar according to their families. 18And their border was toward Jezreel, and Chesulloth, and Shunem, 19And Hapharaim, and Shion, and Anaharath, 20And Rabbith, and Kishion, and Abez, 21And Remeth, and En-gannim, and En-haddah, and Beth-pazzez; 22And the coast reacheth to Tabor, and Shahazimah, and Beth-shemesh; and the outgoings of their border were at Jordan: sixteen cities with their villages. 23This is the inheritance of the tribe of the children of Issachar according to their families, the cities and their villages.

24¶ And the fifth lot came out for the tribe of the children of Asher according to their families. 25And their border was Helkath, and Hali, and Beten, and Achshaph, 26And Alammelech, and Amad, and Misheal; and reacheth to Carmel westward, and to Shihor-libnath; 27And turneth toward the sunrising to Beth-dagon, and reacheth to Zebulun, and to the valley of Jiphthah-el toward the north side of Beth-emek, and Neiel, and goeth out to Cabul on the left hand, 28And Hebron, and Rehob, and Hammon, and Kanah, even unto great Zidon; 29And then the coast turneth to Ramah, and to the strong city Tyre; and the coast turneth to Hosah; and the outgoings thereof are at the sea from the coast to Achzib:19.29 Tyre: Heb. Tzor 30Ummah also, and Aphek, and Rehob: twenty and two cities with their villages. 31This is the inheritance of the tribe of the children of Asher according to their families, these cities with their villages.

32¶ The sixth lot came out to the children of Naphtali, even for the children of Naphtali according to their families. 33And their coast was from Heleph, from Allon to Zaanannim, and Adami, Nekeb, and Jabneel, unto Lakum; and the outgoings thereof were at Jordan: 34And then the coast turneth westward to Aznoth-tabor, and goeth out from thence to Hukkok, and reacheth to Zebulun on the south side, and reacheth to Asher on the west side, and to Judah upon Jordan toward the sunrising. 35And the fenced cities are Ziddim, Zer, and Hammath, Rakkath, and Chinnereth, 36And Adamah, and Ramah, and Hazor, 37And Kedesh, and Edrei, and En-hazor, 38And Iron, and Migdal-el, Horem, and Beth-anath, and Beth-shemesh; nineteen cities with their villages. 39This is the inheritance of the tribe of the children of Naphtali according to their families, the cities and their villages.

40And the seventh lot came out for the tribe of the children of Dan according to their families. 41And the coast of their inheritance was Zorah, and Eshtaol, and Ir-shemesh, 42And Shaalabbin, and Ajalon, and Jethlah, 43And Elon, and Thimnathah, and Ekron, 44And Eltekeh, and Gibbethon, and Baalath, 45And Jehud, and Bene-berak, and Gath-rimmon, 46And Me-jarkon, and Rakkon, with the border before Japho.19.46 before: or, over against19.46 Japho: or, Joppa 47And the coast of the children of Dan went out too little for them: therefore the children of Dan went up to fight against Leshem, and took it, and smote it with the edge of the sword, and possessed it, and dwelt therein, and called Leshem, Dan, after the name of Dan their father. 48This is the inheritance of the tribe of the children of Dan according to their families, these cities with their villages.

49¶ When they had made an end of dividing the land for inheritance by their coasts, the children of Israel gave an inheritance to Joshua the son of Nun among them: 50According to the word of the LORD they gave him the city which he asked, even Timnath-serah in mount Ephraim: and he built the city, and dwelt therein. 51These are the inheritances, which Eleazar the priest, and Joshua the son of Nun, and the heads of the fathers of the tribes of the children of Israel, divided for an inheritance by lot in Shiloh before the LORD, at the door of the tabernacle of the congregation. So they made an end of dividing the country.