ኢያሱ 18 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 18:1-28

የቀሪው ምድር መከፋፈል

1መላው የእስራኤላውያን ማኅበር በሴሎ ተሰበሰቡ፣ የመገናኛውንም ድንኳን እዚያው ተከሉ፤ ምድሪቱም ጸጥ ብላ ተገዛችላቸው። 2ዳሩ ግን ርስት ገና ያልተሰጣቸው ሰባት የእስራኤል ነገዶች ነበሩ።

3ስለዚህ ኢያሱ እስራኤላውያንን እንዲህ አላቸው፤ “የአባቶቻችሁ አምላክ እግዚአብሔር የሰጣችሁን ምድር ለመውረስ ቸል የምትሉት እስከ መቼ ነው? 4አሁንም ከእያንዳንዱ ነገድ ሦስት ሦስት ሰው ምረጡ፤ እኔም ምድሪቱን ተዘዋውረው እንዲያጠኑና እያንዳንዱም ነገድ መውረስ የሚገባውን ድርሻ ዝርዝር መግለጫ ጽፈው እንዲያመጡ እልካቸዋለሁ፤ ከዚያም ወደ እኔ ይመለሳሉ። 5ምድሪቱንም ሰባት ቦታ ይከፍሏታል፤ ይሁዳ በደቡብ፣ የዮሴፍ ዘሮች በሰሜን በኩል የተመደበላቸውን ርስት ይዘው ይኖራሉ። 6የሰባቱን የመሬት ክፍፍል ዝርዝር መግለጫ ጽፋችሁ ወደ እኔ ታመጡና በአምላካችን በእግዚአብሔር ፊት ዕጣ እጥልላችኋለሁ። 7ሌዋውያኑ ግን ለእግዚአብሔር የሚሰጡት የክህነት አገልግሎት ርስታቸው ስለሆነ በእናንተ መካከል ድርሻ አይኖራቸውም። ጋድ፣ ሮቤልና የምናሴ ነገድ እኩሌታም የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴ በምሥራቅ ዮርዳኖስ የሰጣቸውን ርስት ቀደም አድርገው ወስደዋል።”

8ሰዎቹ የምድሪቱን ሁኔታ ለማጥናትና ለመመዝገብ ጕዞ ሲጀምሩ ኢያሱ፣ “ሄዳችሁ የምድሪቱን ሁኔታ አጥኑና በዝርዝር ከጻፋችሁ በኋላ ወደ እኔ ተመለሱ፤ እኔም እዚሁ ሴሎ በእግዚአብሔር ፊት ዕጣ እጥልላችኋለሁ” አላቸው። 9ስለዚህም ሰዎቹ ሄደው ምድሪቱን ተዘዋውረው አዩ፤ ከነ ከተሞቿም ሰባት ቦታ ከፍለው በጥቅልል ብራና ላይ በዝርዝር ጻፉ፤ ከዚያም በሴሎ ሰፈር ወዳለው ወደ ኢያሱ ተመለሱ።

10ኢያሱም በሴሎ በእግዚአብሔር ፊት ዕጣ ጣለላቸው፤ ምድሪቱንም እንደየነገዱ ደልድሎ ለእስራኤላውያን አከፋፈላቸው።

ለብንያም ነገድ የተመደበው ድርሻ

11ለብንያም ነገድ የሆነው የመጀመሪያው ዕጣ በየጐሣ በየጐሣው ወጣ። በዕጣ የደረሳቸውም ምድር የሚገኘው በይሁዳና በዮሴፍ ነገዶች ርስት መካከል ሲሆን እንደሚከተለው ነው፤

12በሰሜን ያለው ድንበራቸው ከዮርዳኖስ ይነሣና የኢያሪኮን ሰሜናዊ ተረተር ዐልፎ፣ በስተ ምዕራብ ወዳለው ኰረብታማ ምድር በማምራት፣ እስከ ቤትአዌን ምድረ በዳ ይዘልቃል። 13ከዚያ ደግሞ ወደ ደቡብ ሎዛ ማለት ወደ ቤቴል ተረተር ይሻገርና በታችኛው ቤትሖሮን በስተ ደቡብ ባለው ተራራ በኩል አድርጎ ወደ አጣሮት አዳር ይወርዳል።

14በስተ ደቡብ ያለው ድንበር ከቤትሖሮን ትይዩ ካለው ኰረብታ ተነሥቶ፣ በምዕራብ በኩል ወደ ደቡብ በመታጠፍ፣ የይሁዳ ነገድ ከተማ ወደ ሆነችው ወደ ቂርያትበኣል ማለት ወደ ቂርያትይዓሪም ያልፋል፤ ይህ እንግዲህ በምዕራብ በኩል ያለው ድንበር ነው።

15በስተ ደቡብ ያለው ድንበር ደግሞ በምዕራብ በኩል ከቂርያትይዓሪም ጥግ ይነሣና እስከ ነፍቶ ውሃ ምንጭ ይዘልቃል፤ 16ይኸው ድንበር ከራፋይም ሸለቆ በስተ ሰሜን ባለው በሄኖም ሸለቆ ትይዩ ቍልቍል ወደ ኰረብታው ግርጌ ይወርዳል፤ ከዚያም ከኢያቡሳውያን ከተማ በደቡብ በኩል ባለው ተረተር አድርጎ ወደ ሄኖም ሸለቆ በመውረድ እስከ ዓይንሮጌል ይዘልቃል። 17ደግሞም ወደ ሰሜን ይታጠፍና በቤትሳሚስ በኩል አድርጎ እስከ ጌሊሎት ይዘልቃል፤ ከዚያም በአዱሚም መተላለፊያ ትይዩ እስካለው እስከ ሮቤል ልጅ እስከ ቦሀን ድንጋይ ይወርዳል። 18ወደ ቤትዓረባ ሰሜናዊ ተረተር በመቀጠል ቍልቍል ወደ ዓረባ ይወርዳል። 19ከዚያም ሰሜናዊውን የቤትሖግላንን ተረተር ዐልፎ ይሄድና በስተ ደቡብ የዮርዳኖስ ወንዝ እስከሚገባበት እስከ ሙት የባሕር ወሽመጥ ይዘልቃል፤ ይህም ደቡባዊ ድንበሩ ነው።

20በምሥራቅ በኩል ያለው ድንበር፣ ራሱ የዮርዳኖስ ወንዝ ነው።

ይህ እንግዲህ የብንያም ነገድ ጐሣዎች በርስትነት የወረሷት ምድር ዳር ድንበሮቿ ሁሉ እነዚህ ነበሩ።

21የብንያም ነገድ በየጐሣቸው የያዟቸው ከተሞች እነዚህ ናቸው፤

ኢያሪኮ፣ ቤትሖግላ፣ ዓመቀጺጽ፣ 22ቤትዓረባ፣ ዘማራይም፣ ቤቴል፣ 23ዓዊም፣ ፋራ፣ ኤፍራታ፣ 24ክፊርዓሞናይ፣ ዖፍኒ እንዲሁም ጋባ ናቸው፤ እነዚህም ከነ መንደሮቻቸው ዐሥራ ሁለት ከተሞች ናቸው።

25ገባዖን፣ ራማ፣ ብኤሮት፣ 26ምጽጳ፣ ከፊራ፣ አሞቂ፣ 27ሬቄም፣ ይርጵኤል፣ ተርአላ፣ 28ጼላ፣ ኤሌፍ፣ የኢያቡሳውያን ከተማ ኢየሩሳሌም፣ ጊብዓ እንዲሁም ቂርያት ነበሩ፤ እነዚህም ከነ መንደሮቻቸው ዐሥራ አራት ከተሞች ናቸው።

እንግዲህ የብንያም ነገድ በየጐሣቸው የወረሱት ይህ ነበር።

New International Reader’s Version

Joshua 18:1-28

The Rest of the Land Is Divided Up

1The whole community of Israel gathered together at Shiloh. They set up the tent of meeting there. The country was brought under their control. 2But there were still seven tribes in Israel who had not yet received their shares of land.

3So Joshua spoke to the Israelites. He said, “The Lord, the God of your people, has given you this land. How long will you wait before you begin to take it over? 4Appoint three men from each tribe. I’ll send them to map out the land. Then they’ll write a report about its features. The report will point out the share of land each tribe will receive. Then the men will return to me. 5You must divide the land up into seven shares. Judah must remain in its territory in the south. The people in Joseph’s family line must remain in their territory in the north. 6Write reports about the features of those seven shares of land. Bring them here to me. Then I’ll cast lots for you in the sight of the Lord our God. 7But the Levites don’t get any share of your land. That’s because their share is to serve the Lord as priests. The tribes of Gad and Reuben and half of the tribe of Manasseh have already received their shares. They are on the east side of the Jordan River. Moses, the servant of the Lord, gave their shares to them.”

8The men started out on their way to map out the land. Joshua directed them, “Go and map out the land. Write a report about its features. Then return to me. I’ll cast lots for you here at Shiloh in the sight of the Lord.” 9So the men left and went through the land. They wrote a report about its features on a scroll. It showed how they divided up the land into seven shares. It listed the towns in each share. The men returned to Joshua in the camp at Shiloh.

10Then Joshua cast lots for them in Shiloh in the sight of the Lord. There he gave out a share of land to each of the remaining tribes in Israel.

Land Is Given to Benjamin

11The first lot drawn out was for the tribe of Benjamin, according to its family groups. The territory they were given was located between the tribes of the people of Judah and the people of Joseph. Here are the borders of Benjamin’s territory.

12On the north side their border started at the Jordan River. It went past the north slope of Jericho. Then it headed west into the central hill country. It came to an end at the Desert of Beth Aven. 13From there the border crossed to the south slope of Bethel. Then it went down to Ataroth Addar on the hill south of Lower Beth Horon.

14From the hill that faces Beth Horon on the south the border turned south. Then the border went along the west side of the hill. It came to an end at Kiriath Jearim. That town belongs to the people of Judah. That was the border on the west.

15The border on the south side started at the west edge of Kiriath Jearim. It came to an end at the springs of Nephtoah. 16It went down to the foot of the hill that faces the Valley of Ben Hinnom. The hill is north of the Valley of Rephaim. The border continued down the Hinnom Valley. It went along the south slope of Jerusalem, where the people of Jebus live. It continued on to En Rogel. 17Then it curved north. It went to En Shemesh. It continued on to Geliloth. Geliloth faces the Pass of Adummim. The border ran down to the Stone of Bohan, the son of Reuben. 18It continued to the north slope of Beth Arabah. It went on down into the Arabah Valley. 19From there it went to the north slope of Beth Hoglah. It came to an end at the north bay of the Dead Sea. That’s where the Jordan River flows into the Dead Sea. That was the border on the south.

20The Jordan River formed the border on the east side.

Those were the borders that marked out on all sides the land the family groups of Benjamin received as their share.

21Here is a list of towns given to the tribe of Benjamin, according to its family groups.

Jericho, Beth Hoglah, Emek Keziz, 22Beth Arabah, Zemaraim, Bethel, 23Avvim, Parah, Ophrah, 24Kephar Ammoni, Ophni and Geba. The total number of towns and their villages was 12.

25Here is another list of towns given to Benjamin.

Gibeon, Ramah, Beeroth, 26Mizpah, Kephirah, Mozah, 27Rekem, Irpeel, Taralah, 28Zelah, Haeleph, Jerusalem, Gibeah and Kiriath. The total number of towns and their villages was 14.

That was the share of land the family groups of Benjamin received.