ኢያሱ 18 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 18:1-28

የቀሪው ምድር መከፋፈል

1መላው የእስራኤላውያን ማኅበር በሴሎ ተሰበሰቡ፣ የመገናኛውንም ድንኳን እዚያው ተከሉ፤ ምድሪቱም ጸጥ ብላ ተገዛችላቸው። 2ዳሩ ግን ርስት ገና ያልተሰጣቸው ሰባት የእስራኤል ነገዶች ነበሩ።

3ስለዚህ ኢያሱ እስራኤላውያንን እንዲህ አላቸው፤ “የአባቶቻችሁ አምላክ እግዚአብሔር የሰጣችሁን ምድር ለመውረስ ቸል የምትሉት እስከ መቼ ነው? 4አሁንም ከእያንዳንዱ ነገድ ሦስት ሦስት ሰው ምረጡ፤ እኔም ምድሪቱን ተዘዋውረው እንዲያጠኑና እያንዳንዱም ነገድ መውረስ የሚገባውን ድርሻ ዝርዝር መግለጫ ጽፈው እንዲያመጡ እልካቸዋለሁ፤ ከዚያም ወደ እኔ ይመለሳሉ። 5ምድሪቱንም ሰባት ቦታ ይከፍሏታል፤ ይሁዳ በደቡብ፣ የዮሴፍ ዘሮች በሰሜን በኩል የተመደበላቸውን ርስት ይዘው ይኖራሉ። 6የሰባቱን የመሬት ክፍፍል ዝርዝር መግለጫ ጽፋችሁ ወደ እኔ ታመጡና በአምላካችን በእግዚአብሔር ፊት ዕጣ እጥልላችኋለሁ። 7ሌዋውያኑ ግን ለእግዚአብሔር የሚሰጡት የክህነት አገልግሎት ርስታቸው ስለሆነ በእናንተ መካከል ድርሻ አይኖራቸውም። ጋድ፣ ሮቤልና የምናሴ ነገድ እኩሌታም የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴ በምሥራቅ ዮርዳኖስ የሰጣቸውን ርስት ቀደም አድርገው ወስደዋል።”

8ሰዎቹ የምድሪቱን ሁኔታ ለማጥናትና ለመመዝገብ ጕዞ ሲጀምሩ ኢያሱ፣ “ሄዳችሁ የምድሪቱን ሁኔታ አጥኑና በዝርዝር ከጻፋችሁ በኋላ ወደ እኔ ተመለሱ፤ እኔም እዚሁ ሴሎ በእግዚአብሔር ፊት ዕጣ እጥልላችኋለሁ” አላቸው። 9ስለዚህም ሰዎቹ ሄደው ምድሪቱን ተዘዋውረው አዩ፤ ከነ ከተሞቿም ሰባት ቦታ ከፍለው በጥቅልል ብራና ላይ በዝርዝር ጻፉ፤ ከዚያም በሴሎ ሰፈር ወዳለው ወደ ኢያሱ ተመለሱ።

10ኢያሱም በሴሎ በእግዚአብሔር ፊት ዕጣ ጣለላቸው፤ ምድሪቱንም እንደየነገዱ ደልድሎ ለእስራኤላውያን አከፋፈላቸው።

ለብንያም ነገድ የተመደበው ድርሻ

11ለብንያም ነገድ የሆነው የመጀመሪያው ዕጣ በየጐሣ በየጐሣው ወጣ። በዕጣ የደረሳቸውም ምድር የሚገኘው በይሁዳና በዮሴፍ ነገዶች ርስት መካከል ሲሆን እንደሚከተለው ነው፤

12በሰሜን ያለው ድንበራቸው ከዮርዳኖስ ይነሣና የኢያሪኮን ሰሜናዊ ተረተር ዐልፎ፣ በስተ ምዕራብ ወዳለው ኰረብታማ ምድር በማምራት፣ እስከ ቤትአዌን ምድረ በዳ ይዘልቃል። 13ከዚያ ደግሞ ወደ ደቡብ ሎዛ ማለት ወደ ቤቴል ተረተር ይሻገርና በታችኛው ቤትሖሮን በስተ ደቡብ ባለው ተራራ በኩል አድርጎ ወደ አጣሮት አዳር ይወርዳል።

14በስተ ደቡብ ያለው ድንበር ከቤትሖሮን ትይዩ ካለው ኰረብታ ተነሥቶ፣ በምዕራብ በኩል ወደ ደቡብ በመታጠፍ፣ የይሁዳ ነገድ ከተማ ወደ ሆነችው ወደ ቂርያትበኣል ማለት ወደ ቂርያትይዓሪም ያልፋል፤ ይህ እንግዲህ በምዕራብ በኩል ያለው ድንበር ነው።

15በስተ ደቡብ ያለው ድንበር ደግሞ በምዕራብ በኩል ከቂርያትይዓሪም ጥግ ይነሣና እስከ ነፍቶ ውሃ ምንጭ ይዘልቃል፤ 16ይኸው ድንበር ከራፋይም ሸለቆ በስተ ሰሜን ባለው በሄኖም ሸለቆ ትይዩ ቍልቍል ወደ ኰረብታው ግርጌ ይወርዳል፤ ከዚያም ከኢያቡሳውያን ከተማ በደቡብ በኩል ባለው ተረተር አድርጎ ወደ ሄኖም ሸለቆ በመውረድ እስከ ዓይንሮጌል ይዘልቃል። 17ደግሞም ወደ ሰሜን ይታጠፍና በቤትሳሚስ በኩል አድርጎ እስከ ጌሊሎት ይዘልቃል፤ ከዚያም በአዱሚም መተላለፊያ ትይዩ እስካለው እስከ ሮቤል ልጅ እስከ ቦሀን ድንጋይ ይወርዳል። 18ወደ ቤትዓረባ ሰሜናዊ ተረተር በመቀጠል ቍልቍል ወደ ዓረባ ይወርዳል። 19ከዚያም ሰሜናዊውን የቤትሖግላንን ተረተር ዐልፎ ይሄድና በስተ ደቡብ የዮርዳኖስ ወንዝ እስከሚገባበት እስከ ሙት የባሕር ወሽመጥ ይዘልቃል፤ ይህም ደቡባዊ ድንበሩ ነው።

20በምሥራቅ በኩል ያለው ድንበር፣ ራሱ የዮርዳኖስ ወንዝ ነው።

ይህ እንግዲህ የብንያም ነገድ ጐሣዎች በርስትነት የወረሷት ምድር ዳር ድንበሮቿ ሁሉ እነዚህ ነበሩ።

21የብንያም ነገድ በየጐሣቸው የያዟቸው ከተሞች እነዚህ ናቸው፤

ኢያሪኮ፣ ቤትሖግላ፣ ዓመቀጺጽ፣ 22ቤትዓረባ፣ ዘማራይም፣ ቤቴል፣ 23ዓዊም፣ ፋራ፣ ኤፍራታ፣ 24ክፊርዓሞናይ፣ ዖፍኒ እንዲሁም ጋባ ናቸው፤ እነዚህም ከነ መንደሮቻቸው ዐሥራ ሁለት ከተሞች ናቸው።

25ገባዖን፣ ራማ፣ ብኤሮት፣ 26ምጽጳ፣ ከፊራ፣ አሞቂ፣ 27ሬቄም፣ ይርጵኤል፣ ተርአላ፣ 28ጼላ፣ ኤሌፍ፣ የኢያቡሳውያን ከተማ ኢየሩሳሌም፣ ጊብዓ እንዲሁም ቂርያት ነበሩ፤ እነዚህም ከነ መንደሮቻቸው ዐሥራ አራት ከተሞች ናቸው።

እንግዲህ የብንያም ነገድ በየጐሣቸው የወረሱት ይህ ነበር።

Bibelen på hverdagsdansk

Josvabogen 18:1-28

Fordelingen af resten af landet

1Nu da landet var under Israels kontrol, samledes folket i Shilo for at rejse åbenbaringsteltet. 2Dog var der endnu syv af stammerne, som ikke havde fået tildelt deres landområder.

3Josva spurgte dem: „Hvor længe vil I vente med at tage det land i besiddelse, som Herren, jeres Gud, har lovet jer? 4Udvælg tre mænd fra hver stamme, så vil jeg sende dem ud for at kortlægge de resterende områder, så vi kan få fastlagt de sidste stammers landegrænser. 5-6De skal opdele landet i syv områder, idet Judas stamme allerede har fået land mod syd og Josefs stammer mod nord. Så vil vi ved lodtrækning fordele disse områder mellem de sidste syv stammer. 7Levitterne får ingen jord, da de arbejder direkte for Herren. Gud selv er deres arvelod, og han vil sørge for dem. Gads stamme og Rubens stamme samt Manasses halve stamme skal heller ikke have noget jord, for de har allerede fået tildelt deres arvelod øst for Jordanfloden, som Moses lovede dem.”

8Til de udvalgte mænd sagde Josva: „Tag af sted og kortlæg hele landet, og kom så tilbage til mig med jeres skrevne rapport, så vil vi kaste lod for Herrens ansigt her i Shilo.” 9Mændene tog nu af sted, som de havde fået besked på, og opdelte området i syv territorier med en liste over byerne i de enkelte territorier. Derpå vendte de tilbage til Josva i lejren ved Shilo, 10og under den efterfølgende lodtrækning viste Herren Josva, hvordan territorierne skulle fordeles mellem stammerne.

Benjamins arvelod

11Klanerne af Benjamins stamme fik ved lodtrækning tildelt området mellem Judas og Efraims territorier.

12Nordgrænsen løb fra Jordanfloden op om Jeriko og vestpå gennem højlandet og Bet-Avens ørken. 13Den fortsatte til den sydlige skråning over for Luz, der også kaldes Betel, og gik videre til Atarot-Addar i højlandet syd for Nedre Bet-Horon. 14Vestgrænsen gik herfra mod syd og fulgte den vestlige side af højdedraget over for Bet-Horon for at ende ved landsbyen Kirjat-Ba’al, som også kaldes Kirjat-Jearim, som tilhørte Judas stamme.

15Den sydlige grænse løb fra udkanten af Kirjat-Jearim vestpå til Neftoakilden 16og ned til foden af bjerget ved Hinnoms dal i den nordlige ende af Refaims dal. Derfra gik den gennem Hinnoms dal syd om de høje, hvor jebusitterne boede, og fortsatte ned til En-Rogel. 17Fra En-Rogel løb grænsen mod nordøst til En-Shemesh, videre til Gelilot over for Adummimpasset og ned til Bohanstenen, der er opkaldt efter Rubens søn, 18videre til højdedraget nord for Bet-ha-Araba, ned i Jordandalen 19og nord om Bet-Hogla for at ende nær det sted ved Det Døde Hav, hvor Jordanfloden løber ud i søen.

20Den østlige grænse fulgte Jordanfloden. Det var Benjamins territorium.

21Benjamins stamme fik følgende byer: Jeriko, Bet-Hogla, Emek-Ketzitz, 22Bet-ha-Araba, Zemarajim, Betel, 23Avvim, Para, Ofra, 24Kefar-ha-Ammoni, Ofni og Geba, i alt 12 byer med tilhørende landsbyer. 25Desuden Gibeon, Rama, Be’erot, 26Mitzpe, Kefira, Mosa, 27Rekem, Jirpe’el, Tarala, 28Zela, Elef, Jebus, der også kaldes Jerusalem, Gibea og Kirjat-Jearim, i alt 14 byer med tilhørende landsbyer.