ኢያሱ 15 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 15:1-63

ለይሁዳ ነገድ የተመደበው ድርሻ

15፥15-19 ተጓ ምብ – መሳ 1፥11-15

1ለይሁዳ ነገድ በየጐሣቸው በዕጣ የተመደበው ድርሻ እስከ ኤዶም ምድር የሚወርድ ሲሆን፣ በስተ ደቡብ መጨረሻ እስከ ጺን ምድረ በዳ ድረስ ይዘልቃል።

2የደቡብ ወሰናቸው፣ ከጨው ባሕር15፥2 በዚህና በቍጥር 5 ላይ የሙት ባሕር ማለት ነው። ደቡባዊ ጫፍ ካለው የባሕር ወሽመጥ ይነሣል፤ 3ከዚያም የአቅረቢምን መተላለፊያ በማቋረጥ በጺን በኩል እስከ ቃዴስ በርኔ ደቡባዊ ክፍል ይደርሳል፤ ደግሞም ሐጽሮንን ዐልፎ ወደ አዳር ይወጣና ወደ ቀርቃ ይታጠፋል፤ 4በአድሞን በኩል አድርጎም ወደ ግብፅ ደረቅ ወንዝ ይገባና መቆሚያው ባሕሩ ይሆናል። እንግዲህ በደቡብ በኩል ያለው ወሰናቸው15፥4 ዕብራይስጡ ወስናችሁ ይላል። ይህ ነው።

5በምሥራቅ በኩል ያለው ወሰናቸው ደግሞ የጨው ባሕር ሲሆን፣ ይህም የዮርዳኖስ ወንዝ እስከሚሠርግበት ይደርሳል።

በሰሜን በኩል ያለው ወሰንም የዮርዳኖስ ወንዝ ከሚሠርግበት የባሕር ወሽመጥ ይነሣና 6ሽቅብ ወደ ቤትሖግላ ይወጣል፤ ከዚያም በሰሜናዊው ቤትዓረባ በኩል አድርጎ የሮቤል ልጅ የቦሀን ድንጋይ እስካለበት ይደርሳል። 7ከዚያም ድንበሩ ከአኮር ሸለቆ ወደ ዳቤር ይወጣና ከወንዙ በስተ ደቡብ ባለው በአዱሚም መተላለፊያ ፊት ለፊት አድርጎ በስተ ሰሜን ወደ ጌልገላ ይታጠፋል፤ በዓይንሳሚስ ምንጭ በኩል ዐልፎም ወደ ዓይንሮጌል ይወጣል። 8እንደዚሁም የሄኖምን ልጅ ሸለቆ ዐልፎ ይሄድና የኢያቡሳውያን ከተማ እስከ ሆነችው እስከ ኢየሩሳሌም ደቡባዊ ተረተር በመዝለቅ፣ በራፋይም ሸለቆ ሰሜን ጫፍ በኩል አድርጎ ከሄኖም ሸለቆ በስተ ምዕራብ ካለው ኰረብታ ዐናት ላይ ይደርሳል። 9ከዚያም በመቀጠል ከተራራው ዐናት ተነሥቶ ወደ ኔፍቶ ምንጮች በማምራት፣ በዔፍሮን ተራራ ላይ ያሉትን ከተሞች ዐልፎ ይወጣና ቂርያትይዓሪም ተብሎ ወደሚጠራው ወደ በኣላ ቍልቍል ይወርዳል። 10ከዚያም ከበኣላ በምዕራብ በኩል አድርጎ ወደ ሴይር ይታጠፍና ክሳሎን ተብሎ በሚጠራው በይዓሪም ኰረብታ ሰሜናዊ ተረተር ዐልፎ ቍልቍል ወደ ቤትሳሚስ በመውረድ ወደ ተምና ይሻገራል። 11ደግሞም በአቃሮን ሰሜናዊ ተረተር አድርጎ ወደ ሽክሮን ይታጠፍና በበኣላ ተራራ ላይ ዐልፎ እስከ የብኒኤል ይደርሳል፤ ከዚህ በኋላ ወሰኑ ባሕሩ ላይ ይቆማል።

12የምድሪቱ ምዕራባዊ ወሰን የታላቁ ባሕር15፥12 በዚህና በቍጥር 47 ላይ የተጠቀሰው የሜድትራንያን ባሕር ነው። ጠረፍ ነው።

እንግዲህ በየጐሣው የተደለደለውን የይሁዳን ሕዝብ በዙሪያው የከበቡት ወሰኖቹ እነዚሁ ናቸው።

13ኢያሱ እግዚአብሔር ባዘዘው መሠረት፣ ከይሁዳ ድርሻ ላይ ከፍሎ ኬብሮን የተባለችውን ቂርያት አርባቅን ለዮፎኒ ልጅ ለካሌብ ሰጠው፤ አርባቅም የዔናቅ አባት ነበረ። 14ካሌብም ሦስቱን የዔናቅን ዘሮች ሴሲንን፣ አኪመንንና ተላሚንን ከኬብሮን አሳደዳቸው፤ 15ከዚያም በዳቤር ሕዝብ ላይ ዘመተ፤ ዳቤር ቀድሞ ቂርያትሤፍር ትባል ነበር። 16ካሌብ፣ “ቂርያትሤፍርን ወግቶ ለሚይዝ ሰው ልጄን ዓክሳን እድርለታለሁ” አለ። 17ስለዚህ የካሌብ ወንድም የቄኔዝ ልጅ ጎቶንያል ከተማዪቱን ያዛት፤ ካሌብም ልጁን ዓክሳን ዳረለት።

18ዓክሳ ወደ ጎቶንያል በመጣች ጊዜም፣ ከአባቷ ላይ የዕርሻ መሬት እንዲለምን አጥብቃ ነገረችው።15፥18 ዕብራይስጥና አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ብዙ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ግን (መሳ 1፥14 ይመ) አጥብቆ ነገራት ያላሉ። ከአህያዋ ላይ እንደ ወረደች ካሌብ፣ “ምን እንዳደርግልሽ ትፈልጊያለሽ?” ሲል ጠየቃት።

19እርሷም፣ “እባክህ፤ በጎ ነገር አድርግልኝ፤ በኔጌብ መሬት እንደ ሰጠኸኝ ሁሉ፣ አሁንም የውሃ ምንጭ ጉድጓዶች ስጠኝ” አለችው፤ ካሌብም የላይኛውንና የታችኛውን ምንጮች ሰጣት።

20ለይሁዳ ነገድ በየጐሣቸው የተሰጣቸው ርስት ይህ ነው፤

21በኔጌብ አካባቢ በኤዶም ድንበር ላይ በወሰኑ ጫፍ የሚገኙት የይሁዳ ነገድ ደቡባዊ ከተሞች እነዚህ ነበሩ፤

ቀብስኤል፣ ዔዴር፣ ያጉር፣ 22ቂና፣ ዲሞና፣ ዓድዓዳ፣ 23ቃዴስ፣ ሐጾር፤ ዩትናን፣ 24ዚፍ፣ ጤሌም፣ በዓሎት፣ 25ሐጾርሐዳታ፣ ሐጾር የምትባለው ቂርያትሐጾር 26አማም፣ ሽማዕ፣ ሞላዳ፣ 27ሐጻርጋዳ፣ ሐሽሞን፣ ቤትጳሌጥ፣ 28ሐጸር ሹዓል፣ ቤርሳቤህ፣ ቢዝዮትያ 29በኣላ፣ ዒዪም፣ ዓጼም፣ 30ኤልቶላድ፣ ኪሲል፣ ሔርማ፣ 31ጺቅላግ፣ ማድማና፣ ሳንሳና 32ልባዎት፣ ሺልሂም፣ ዓይንና ሪሞን ናቸው፤ በአጠቃላይም ከተሞቹና መንደሮቻቸው ሃያ ዘጠኝ ናቸው።

33በምዕራቡ በኰረብታዎች ግርጌ ያሉት ደግሞ እነዚህ ናቸው፤

ኤሽታኦል፤ ጾርዓ፣ አሽና 34ዛኖዋ፣ ዓይንገኒም፣ ታጱዋ፣ ዓይናም፣ 35የርሙት፣ ዓዶላም፣ ሰኰት፣ ዓዜቃ፣ 36ሽዓራይም፣ ዓዲታይም፣ ግዴራ፣ ግዴሮታይም ናቸው፤ ከተሞቹም ከነ መንደሮቻቸው ዐሥራ አራት ናቸው።

37ጽናን፣ ሐዳሻ፣ ሚግዳልጋድ፣ 38ዲልዓን፣ ምጽጳ፣ ዮቅትኤል፣ 39ለኪሶ፣ ቦጽቃት፣ ዔግሎን፣ 40ከቦን፣ ለሕማስ፣ ኪትሊሽ፣ 41ግዴሮት፣ ቤትዳጎን፣ ናዕማና መቄዳ ናቸው፤ ከተሞቹም ከነ መንደሮቻቸው ዐሥራ ስድስት ናቸው።

42ልብና፣ ዔትር፣ ዓሻን 43ይፍታሕ፣ አሽና፣ ንጺብ፣ 44ቅዒላ፣ አክዚብና መሪሳ ናቸው፤ ከተሞቹም ከነ መንደሮቻቸው ዘጠኝ ናቸው።

45አቃሮን በዙሪያዋ ካሉ ሰፈሮችና መንደሮቿ ጋር፣ 46እንዲሁም ከአቃሮን በስተ ምዕራብ በአሽዶድ አካባቢ ያሉ ሰፈሮችና መንደሮቻቸው ሁሉ፣ 47አሽዶድ በዙሪያዋ ካሉ ሰፈሮችና መንደሮች ጋር፣ ጋዛ እስከ ግብፅ ደረቅ ወንዝና እስከ ታላቁ ባሕር ጠረፍ በመለስ ካሉት ሰፈሮቿና መንደሮቿ ጋር።

48በኰረብታማዋም አገር የሚገኙ ከተሞች ደግሞ እነዚህ ናቸው፤

ሳምር፣ የቲር፣ ሶኮ 49ደና፣ ዳቤር የምትባለው ቂርያትስና 50ዓናብ፣ ኤሽትሞዓ፣ ዓኒም፣ 51ጎሶም፣ ሖሎንና ጊሎ፤ እነዚህም ዐሥራ አንዱ ከተሞችና መንደሮቻቸው ናቸው።

52አራብ፣ ዱማ፣ ኤሽዓን፣ 53ያኒም፣ ቤትታጱዋ፣ አፌቃ 54ሑምጣ፣ ኬብሮን የተባለችው ቂርያትአርባቅና ጺዖር ናቸው፤ እነዚህም ዘጠኝ ከተሞችና መንደሮቻቸው ናቸው።

55ማዖን፣ ቀርሜሎስ፣ ዚፍ፣ ዩጣ 56ኢይዝራኤል፣ ዮቅድዓም፣ ዛኖዋሕ፣ 57ቃይን፣ ጊብዓና ተምና ናቸው፤ እነዚህም ዐሥር ከተሞችና መንደሮቻቸው ናቸው።

58ሐልሑል፣ ቤትጹር፣ ጌዶር፣ 59ማዕራት፣ ቤትዓኖትና ኤልትቆን ናቸው፤ እነዚህም ስድስት ከተሞችና መንደሮቻቸው ናቸው።

60ቂርያትይዓሪም የተባለችው ቂርያ ትበኣልና ረባት፤ እነዚህም ሁለት ከተሞችና መንደሮቻቸው ናቸው።

61በምድረ በዳው ደግሞ እነዚህ ናቸው፤

ቤትዓረባ፣ ሚዲን፣ ስካካ፣ 62ኒብሻን፣ የጨው ከተማና ዓይንጋዲ፤ እነዚህም ስድስት ከተሞችና መንደሮቻቸው ናቸው።

63ነገር ግን የይሁዳ ዘሮች በኢየሩሳሌም የሚኖሩትን ኢያቡሳውያን ከቦታቸው ሊያስለቅቋቸው አልቻሉም፤ ኢያቡሳውያንም እስከ ዛሬ ድረስ ከይሁዳ ሕዝብ ጋር በኢየሩሳሌም አብረው ይኖራሉ።

Swedish Contemporary Bible

Josua 15:1-63

Judas stam

(Dom 1:11-15)

1Judas stam fick sin del, efter sina släkter, söderut intill Edoms gräns och öknen Sin.

2Denna gräns började vid södra viken av Döda havet 3och gick utmed södra sidan av Skorpionhöjden och vidare in i öknen Sin till Hesron söder om Kadesh Barnea, sedan upp till Addar och därefter mot Karka 4och Asmon, tills den slutligen nådde Egyptens bäck och följde den till Medelhavet. Detta är deras sydgräns.

5Den östra gränsen sträckte sig utmed Döda havet till floden Jordans utlopp.

Den norra gränsen började vid viken där Jordan rinner ut i Döda havet, 6sträckte sig därifrån upp mot Bet-Hogla och fortsatte norr om Bet Haarava till Bohans, Rubens sons, sten. 7Därifrån gick gränsen upp till Devir från Akors dal i nordlig riktning mot Gelilot som ligger mitt emot Adummimshöjden söder om bäcken. Gränsen gick sedan fram till Shemeshkällan ut till Rogelkällan 8och fortsatte upp mot Hinnoms sons dal söder om Jevus höjd där Jerusalem ligger. Därefter gick gränsen upp till toppen av det berg som ligger ovanför Hinnoms dal i norra delen av Refaimdalen. 9Därifrån drogs gränsen från toppen av berget fram till Neftoachkällan och vidare till städerna i Efrons bergsbygd, innan den vände mot Baala vilket är ett annat namn för Kirjat-Jearim.

10Från Baala gick gränsen västerut mot Seirs bergsbygd och fram till Jearims bergshöjd, dvs. Kesalon, och vidare ner till Bet Shemesh förbi Timna 11till Ekrons norra sluttning där den böjde sig mot Shickeron och berget Baala, passerade Javneel och slutade vid Medelhavet.

12Detta var Judas släkters gränser.

13Josua gav en del av Judas område åt Kalev, Jefunnes son, som Herren hade befallt och han fick därför staden Kirjat-Arba, som fått sitt namn efter Anaks stamfar Arba men som också kallades Hebron.

14Kalev fördrev Anaks tre ättlingar Sheshaj, Achiman och Talmaj 15och därifrån tågade han mot invånarna i Devir som förut kallades Kirjat-Sefer.

16Kalev sa: ”Den som anfaller och intar Kirjat-Sefer ska jag ge min dotter Aksa till hustru.” 17Otniel, son till Kalevs bror Kenas, intog staden och Kalev gav sin dotter Aksa till honom. 18När hon kom till Otniel, uppmanade hon honom att be hennes far om ett stycke mark. När hon steg av15:18 Grundtextens innebörd är osäker. från sin åsna frågade Kalev henne: ”Är det något du önskar?” 19Hon svarade: ”Ge mig en gåva! Du har gett mig land i Negev, men ge mig några vattenkällor också!” Då gav Kalev henne de övre och nedre källorna.

20Judas stam fick, efter sina släkter, följande område:

21De städer och byar som låg utmed gränsen mot Edom i Negev, nämligen Kavseel, Eder, Jagur, 22Kina, Dimona, Adada, 23Kedesh, Hasor, Jitnan, 24Sif, Telem, Bealot, 25Hasor Hadatta, Keriot Hesron dvs. Hasor, 26Amam, Shema, Molada, 27Hasar Gadda, Heshmon, Bet Pelet, 28Hasar Shual, Beer Sheva med kringliggande byar, 29Baala, Ijim, Esem, 30Eltolad, Kesil, Horma, 31Siklag, Madmanna, Sansanna, 32Levaot, Shilchim, Ajin och Rimmon. Tillsammans var detta tjugonio städer med kringliggande byar.

33I Låglandet:

Eshtaol, Sora, Ashna, 34Sanoach och En-Gannim, Tappuach och Enam, 35Jarmut och Adullam, Soko och Aseka, 36Shaarajim, Aditajim, Gedera och Gederotajim. Tillsammans var detta fjorton städer med kringliggande byar.

37Vidare: Senan, Hadasha, Migdal-Gad, 38Dilan, Mispa, Jokteel, 39Lakish, Boskat, Eglon, 40Kabbon, Lachmas, Kitlish, 41Gederot, Bet-Dagon, Naama och Mackeda, sexton städer med kringliggande byar, 42Livna, Eter, Ashan, 43Jefta, Ashna, Nesiv, 44Keila, Aksiv och Maresha, nio städer med kringliggande byar 45och Ekrons alla städer och byar, 46från Ekron västerut och städerna med kringliggande byar nära Ashdod 47mot Ashdod med kringliggande byar och till Gaza med dess byar ända fram till Egyptens bäck och Medelhavet.

48I bergsbygden:

Shamir, Jattir, Soko, 49Danna, Kirjat-Sanna, dvs. Devir, 50Anav, Eshtemoa, Anim, 51Goshen, Holon och Gilo, elva städer med kringliggande byar, 52Arav, Duma, Eshan, 53Janum, Bet-Tappuach, Afeka, 54Humta, Kirjat-Arba dvs. Hebron, Sior, nio städer med kringliggande byar, 55Maon, Karmel, Sif, Jutta, 56Jisreel, Jokdeam, Sanoach, 57Kain, Giva, Timna, tio städer med omgivande orter, 58Halchul, Bet-Sur, Gedor, 59Maarat, Bet-Anot, Eltekon, sex städer med kringliggande byar,15:59 Den grekiska översättningen av Gamla testamentet (Septuaginta) har här skjutit in ytterligare elva städer: Tekoa, Efrata, dvs. Betlehem, Pegor, Etam, Kulon, Tatam, Shoresh, Kerem, Gallim, Beter och Manocho. Det sammanlagda antalet blir då 49 städer. 60Kirjat-Baal, dvs. Kirjat-Jearim, Rabba, två städer med kringliggande byar.

61I öknen:

Bet Haarava, Middin, Sekaka, 62Nivshan, Ir-Hammelach och Levo-Hamat, sex städer med kringliggande byar.

63Men Judas stam kunde inte driva ut jevuséerna som bodde i staden Jerusalem och därför bor jevuséerna bland Judas folk i Jerusalem än idag.