ኢያሱ 12 – NASV & OL

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 12:1-24

የተሸነፉ ነገሥታት ስም ዝርዝር

1እንግዲህ እስራኤላውያን ድል ያደረጓቸውና ከዮርዳኖስ ማዶ በስተ ምሥራቅ የሚገኘውን የዓረባን ክፍል በሙሉ ይዞ፣ ከአርኖን ሸለቆ እስከ አርሞንዔም ተራራ የሚዘልቀውን ግዛታቸውን የወሰዱባቸው ነገሥታት እነዚህ ናቸው፤

2መቀመጫውን በሐሴቦን አድርጎ የገዛው የአሞራውያን ንጉሥ ሴዎን፣

ከአርኖን ሸለቆ ዳርቻ ላይ ካለችው ከአሮዔር ማለት ከሸለቆው መካከል አንሥቶ፣ የአሞናውያን ወሰን እስከ ሆነው እስከ ያቦቅ ወንዝ ድረስ ገዝቷል፤ ይህም የገለዓድን እኩሌታ ይጨምራል።

3እንዲሁም ከኪኔሬት ባሕር12፥3 “ገሊላ” ናት። እስከ ሙት12፥3 የሙት ባሕር፣ የጨው ባሕርም ይባላል። ባሕር ያለውን ምሥራቃዊውን ዓረባ፣ እስከ ቤት የሺሞትና ከዚያም በስተ ደቡብ እስከ ፈስጋ ተራራ ግርጌ ድረስ ገዝቷል።

4መቀመጫውን በአስታሮትና በኤድራይ አድርጎ የገዛውና ከመጨረሻዎቹ ከራፋይም ዘሮች አንዱ የሆነው የባሳን ንጉሥ ዐግ፣

5የአርሞንዔምን ተራራ፣ ሰልካንን፣ ባሳንን ሁሉ እስከ ጌሹራውያንና እስከ ማዕካታውያን ድንበሮች እንዲሁም ከገለዓድ እኩሌታ እስከ ሐሴቦን ንጉሥ እስከ ሴዎን ወሰን ድረስ ገዝቷል።

6የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴና እስራኤላውያን እነዚህን ድል አደረጉ፤ የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴም ምድራቸውን ለሮቤል፣ ለጋድና ለምናሴ ነገድ እኩሌታ ርስት አድርጎ ሰጣቸው።

7እንግዲህ ኢያሱና እስራኤላውያን ከዮርዳኖስ በስተ ምዕራብ ድል ያደረጓቸው የምድሪቱ ነገሥታት እነዚህ ናቸው፤ ግዛታቸውም በሊባኖስ ሸለቆ ውስጥ ካለው ከበኣልጋድ ተነሥቶ በምዕራብ ሴይር እስካለው እስከ ሐላቅ ተራራ ይደርሳል፤ ኢያሱም የእነዚህን ነገሥታት ምድር እንደ ነገዳቸው አከፋፈል ለእስራኤላውያን በማከፋፈል ርስት አድርጎ ሰጣቸው። 8ይህም ተራራማው አገር፤ በስተ ምዕራብ ያለው የኰረብታ ግርጌ፣ ዓረባ፣ የተራራው ሸንተረሮች፣ ምድረ በዳውና ነጌብ ማለት የኬጢያውያን፣ የአሞራውያን፣ የከነዓናውያን፣ የፌርዛውያን፣ የኤዊያውያንና የኢያቡሳውያን ምድር ነው፤ ነገሥታቱም እነዚህ ናቸው፤

9የኢያሪኮ ንጉሥ፣ አንድ፤

ቤቴል አጠገብ ያለችው የጋይ ንጉሥ፣ አንድ፤

10የኢየሩሳሌም ንጉሥ፣ አንድ፤

የኬብሮን ንጉሥ፣ አንድ፤

11የየርሙት ንጉሥ፣ አንድ፤

የለኪሶ ንጉሥ፣ አንድ፤

12የዔግሎን ንጉሥ፣ አንድ፤

የጌዝር ንጉሥ፣ አንድ፤

13የዳቤር ንጉሥ፣ አንድ፤

የጌድር ንጉሥ፣ አንድ፤

14የሔርማ ንጉሥ፣ አንድ፤

የዓራድ ንጉሥ፣ አንድ፤

15የልብና ንጉሥ፣ አንድ፤

የዓዶላም ንጉሥ፣ አንድ፤

16የመቄዳ ንጉሥ፤ አንድ፤

የቤቴል ንጉሥ፣ አንድ፤

17የታጱዋ ንጉሥ፣ አንድ፤

የኦፌር ንጉሥ፣ አንድ፤

18የአፌቅ ንጉሥ፣ አንድ፤

የለሸሮን ንጉሥ፣ አንድ፤

19የማዶን ንጉሥ፣ አንድ፤

የሐጾር ንጉሥ፣ አንድ፤

20የሺምሮን ሚሮን ንጉሥ፣ አንድ፤

የአዚፍ ንጉሥ፣ አንድ፤

21የታዕናክ ንጉሥ፣ አንድ፤

የመጊዶ ንጉሥ፣ አንድ፤

22የቃዴስ ንጉሥ፣ አንድ፤

በቀርሜሎስ የሚገኘው የዮቅንዓም ንጉሥ፣ አንድ፤

23በዶር ኰረብታ12፥23 ወይም፣ “ናፎት ዳር” ማለት ነው። የሚገኘው የዶር ንጉሥ፣ አንድ፤

በጌልገላ የሚገኘው የጎይም ንጉሥ፣ አንድ፤

24የቲርሳ ንጉሥ፣ አንድ።

እነዚህ በድምሩ ሠላሳ አንድ ነገሥታት ናቸው።

O Livro

Josué 12:1-24

A lista dos reis derrotados

1Esta é a lista dos reis da margem oriental do rio Jordão, cujas cidades foram destruídas pelos israelitas; uma área que ia desde o vale do rio Arnom até ao monte Hermon, incluindo as cidades do deserto oriental.

2Um deles era o rei Siom dos amorreus, que vivia em Hesbom. O seu reino cobria o território que tinha por limite, dum lado Aroer, mesmo na extremidade do vale de Arnom, e a meio da depressão cavada pelo rio Arnom, e do outro lado o rio Jaboque até metade de Gileade, que servia de fronteira com os amonitas. 3Portanto, inclui desde a planície até ao mar da Galileia, do lado oriental, até ao mar da planície, o mar Salgado, estendendo-se em direção a Bete-Jesimote, a sul, até às encostas do monte Pisga.

4Outro era o rei Ogue de Basã, o último dos refaítas, que vivia em Astarote e Edrei. 5Era ele quem governava aquele território que se estendia do monte Hermon a norte, até Salca no monte Basã, a oriente; a ocidente ia até aos limites dos reinos de Gesur e Maacá. O seu reino cobria também uma área a sul, que incluía a metade norte de Gileade, onde a fronteira tocava os limites do reino de Siom rei de Hesbom. 6Moisés e o povo de Israel tinham destruído esses povos e a terra tinha sido dada à tribo de Rúben, à tribo de Gad e à meia tribo de Manassés.

7Foram ainda os seguintes reinos que Josué, comandando o exército de Israel, destruiu a ocidente do Jordão. (Essa terra que fica entre Baal-Gad no vale do Líbano e o monte Halaque, a ocidente do monte Seir, foi dada por Josué às outras tribos de Israel. 8Essa área incluía a zona das colinas, as planuras, o Arabá, as vertentes na montanha, o deserto da Judeia e o Negueve. Os povos que lá viviam eram os hititas, os amorreus, os cananeus, os perizeus, os heveus e os jebuseus.)

9Eram os reis das seguintes cidades:

Jericó,

Ai perto de Betel,

10Jerusalém,

Hebrom,

11Jarmute,

Laquis,

12Eglom,

Gezer,

13Debir,

Geder,

14Horma,

Arade,

15Libna,

Adulão,

16Maqueda,

Betel,

17Tapua,

Hefer,

18Afeque,

Lasarom,

19Madom,

Hazor,

20Simrom-Merom,

Acsafe,

21Taanaque,

Megido,

22Quedes,

Jocneão no Carmelo,

23Dor em Nafate-Dor,

Goiim em Gilgal,

24e Tirza.

Ao todo, trinta e um reis que foram aniquilados e as suas cidades destruídas.