ኢያሱ 12 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 12:1-24

የተሸነፉ ነገሥታት ስም ዝርዝር

1እንግዲህ እስራኤላውያን ድል ያደረጓቸውና ከዮርዳኖስ ማዶ በስተ ምሥራቅ የሚገኘውን የዓረባን ክፍል በሙሉ ይዞ፣ ከአርኖን ሸለቆ እስከ አርሞንዔም ተራራ የሚዘልቀውን ግዛታቸውን የወሰዱባቸው ነገሥታት እነዚህ ናቸው፤

2መቀመጫውን በሐሴቦን አድርጎ የገዛው የአሞራውያን ንጉሥ ሴዎን፣

ከአርኖን ሸለቆ ዳርቻ ላይ ካለችው ከአሮዔር ማለት ከሸለቆው መካከል አንሥቶ፣ የአሞናውያን ወሰን እስከ ሆነው እስከ ያቦቅ ወንዝ ድረስ ገዝቷል፤ ይህም የገለዓድን እኩሌታ ይጨምራል።

3እንዲሁም ከኪኔሬት ባሕር12፥3 “ገሊላ” ናት። እስከ ሙት12፥3 የሙት ባሕር፣ የጨው ባሕርም ይባላል። ባሕር ያለውን ምሥራቃዊውን ዓረባ፣ እስከ ቤት የሺሞትና ከዚያም በስተ ደቡብ እስከ ፈስጋ ተራራ ግርጌ ድረስ ገዝቷል።

4መቀመጫውን በአስታሮትና በኤድራይ አድርጎ የገዛውና ከመጨረሻዎቹ ከራፋይም ዘሮች አንዱ የሆነው የባሳን ንጉሥ ዐግ፣

5የአርሞንዔምን ተራራ፣ ሰልካንን፣ ባሳንን ሁሉ እስከ ጌሹራውያንና እስከ ማዕካታውያን ድንበሮች እንዲሁም ከገለዓድ እኩሌታ እስከ ሐሴቦን ንጉሥ እስከ ሴዎን ወሰን ድረስ ገዝቷል።

6የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴና እስራኤላውያን እነዚህን ድል አደረጉ፤ የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴም ምድራቸውን ለሮቤል፣ ለጋድና ለምናሴ ነገድ እኩሌታ ርስት አድርጎ ሰጣቸው።

7እንግዲህ ኢያሱና እስራኤላውያን ከዮርዳኖስ በስተ ምዕራብ ድል ያደረጓቸው የምድሪቱ ነገሥታት እነዚህ ናቸው፤ ግዛታቸውም በሊባኖስ ሸለቆ ውስጥ ካለው ከበኣልጋድ ተነሥቶ በምዕራብ ሴይር እስካለው እስከ ሐላቅ ተራራ ይደርሳል፤ ኢያሱም የእነዚህን ነገሥታት ምድር እንደ ነገዳቸው አከፋፈል ለእስራኤላውያን በማከፋፈል ርስት አድርጎ ሰጣቸው። 8ይህም ተራራማው አገር፤ በስተ ምዕራብ ያለው የኰረብታ ግርጌ፣ ዓረባ፣ የተራራው ሸንተረሮች፣ ምድረ በዳውና ነጌብ ማለት የኬጢያውያን፣ የአሞራውያን፣ የከነዓናውያን፣ የፌርዛውያን፣ የኤዊያውያንና የኢያቡሳውያን ምድር ነው፤ ነገሥታቱም እነዚህ ናቸው፤

9የኢያሪኮ ንጉሥ፣ አንድ፤

ቤቴል አጠገብ ያለችው የጋይ ንጉሥ፣ አንድ፤

10የኢየሩሳሌም ንጉሥ፣ አንድ፤

የኬብሮን ንጉሥ፣ አንድ፤

11የየርሙት ንጉሥ፣ አንድ፤

የለኪሶ ንጉሥ፣ አንድ፤

12የዔግሎን ንጉሥ፣ አንድ፤

የጌዝር ንጉሥ፣ አንድ፤

13የዳቤር ንጉሥ፣ አንድ፤

የጌድር ንጉሥ፣ አንድ፤

14የሔርማ ንጉሥ፣ አንድ፤

የዓራድ ንጉሥ፣ አንድ፤

15የልብና ንጉሥ፣ አንድ፤

የዓዶላም ንጉሥ፣ አንድ፤

16የመቄዳ ንጉሥ፤ አንድ፤

የቤቴል ንጉሥ፣ አንድ፤

17የታጱዋ ንጉሥ፣ አንድ፤

የኦፌር ንጉሥ፣ አንድ፤

18የአፌቅ ንጉሥ፣ አንድ፤

የለሸሮን ንጉሥ፣ አንድ፤

19የማዶን ንጉሥ፣ አንድ፤

የሐጾር ንጉሥ፣ አንድ፤

20የሺምሮን ሚሮን ንጉሥ፣ አንድ፤

የአዚፍ ንጉሥ፣ አንድ፤

21የታዕናክ ንጉሥ፣ አንድ፤

የመጊዶ ንጉሥ፣ አንድ፤

22የቃዴስ ንጉሥ፣ አንድ፤

በቀርሜሎስ የሚገኘው የዮቅንዓም ንጉሥ፣ አንድ፤

23በዶር ኰረብታ12፥23 ወይም፣ “ናፎት ዳር” ማለት ነው። የሚገኘው የዶር ንጉሥ፣ አንድ፤

በጌልገላ የሚገኘው የጎይም ንጉሥ፣ አንድ፤

24የቲርሳ ንጉሥ፣ አንድ።

እነዚህ በድምሩ ሠላሳ አንድ ነገሥታት ናቸው።

King James Version

Joshua 12:1-24

1Now these are the kings of the land, which the children of Israel smote, and possessed their land on the other side Jordan toward the rising of the sun, from the river Arnon unto mount Hermon, and all the plain on the east: 2Sihon king of the Amorites, who dwelt in Heshbon, and ruled from Aroer, which is upon the bank of the river Arnon, and from the middle of the river, and from half Gilead, even unto the river Jabbok, which is the border of the children of Ammon; 3And from the plain to the sea of Chinneroth on the east, and unto the sea of the plain, even the salt sea on the east, the way to Beth-jeshimoth; and from the south, under Ashdoth-pisgah:12.3 the south: or, Teman12.3 Ashdoth-pisgah: or, the springs of Pisgah, or, the hill

4¶ And the coast of Og king of Bashan, which was of the remnant of the giants, that dwelt at Ashtaroth and at Edrei, 5And reigned in mount Hermon, and in Salcah, and in all Bashan, unto the border of the Geshurites and the Maachathites, and half Gilead, the border of Sihon king of Heshbon. 6Them did Moses the servant of the LORD and the children of Israel smite: and Moses the servant of the LORD gave it for a possession unto the Reubenites, and the Gadites, and the half tribe of Manasseh.

7¶ And these are the kings of the country which Joshua and the children of Israel smote on this side Jordan on the west, from Baal-gad in the valley of Lebanon even unto the mount Halak, that goeth up to Seir; which Joshua gave unto the tribes of Israel for a possession according to their divisions; 8In the mountains, and in the valleys, and in the plains, and in the springs, and in the wilderness, and in the south country; the Hittites, the Amorites, and the Canaanites, the Perizzites, the Hivites, and the Jebusites:

9¶ The king of Jericho, one; the king of Ai, which is beside Beth-el, one; 10The king of Jerusalem, one; the king of Hebron, one; 11The king of Jarmuth, one; the king of Lachish, one; 12The king of Eglon, one; the king of Gezer, one; 13The king of Debir, one; the king of Geder, one; 14The king of Hormah, one; the king of Arad, one; 15The king of Libnah, one; the king of Adullam, one; 16The king of Makkedah, one; the king of Beth-el, one; 17The king of Tappuah, one; the king of Hepher, one; 18The king of Aphek, one; the king of Lasharon, one;12.18 Lasharon: or, Sharon 19The king of Madon, one; the king of Hazor, one; 20The king of Shimron-meron, one; the king of Achshaph, one; 21The king of Taanach, one; the king of Megiddo, one; 22The king of Kedesh, one; the king of Jokneam of Carmel, one; 23The king of Dor in the coast of Dor, one; the king of the nations of Gilgal, one; 24The king of Tirzah, one: all the kings thirty and one.