ኢያሱ 12 – NASV & CARS

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 12:1-24

የተሸነፉ ነገሥታት ስም ዝርዝር

1እንግዲህ እስራኤላውያን ድል ያደረጓቸውና ከዮርዳኖስ ማዶ በስተ ምሥራቅ የሚገኘውን የዓረባን ክፍል በሙሉ ይዞ፣ ከአርኖን ሸለቆ እስከ አርሞንዔም ተራራ የሚዘልቀውን ግዛታቸውን የወሰዱባቸው ነገሥታት እነዚህ ናቸው፤

2መቀመጫውን በሐሴቦን አድርጎ የገዛው የአሞራውያን ንጉሥ ሴዎን፣

ከአርኖን ሸለቆ ዳርቻ ላይ ካለችው ከአሮዔር ማለት ከሸለቆው መካከል አንሥቶ፣ የአሞናውያን ወሰን እስከ ሆነው እስከ ያቦቅ ወንዝ ድረስ ገዝቷል፤ ይህም የገለዓድን እኩሌታ ይጨምራል።

3እንዲሁም ከኪኔሬት ባሕር12፥3 “ገሊላ” ናት። እስከ ሙት12፥3 የሙት ባሕር፣ የጨው ባሕርም ይባላል። ባሕር ያለውን ምሥራቃዊውን ዓረባ፣ እስከ ቤት የሺሞትና ከዚያም በስተ ደቡብ እስከ ፈስጋ ተራራ ግርጌ ድረስ ገዝቷል።

4መቀመጫውን በአስታሮትና በኤድራይ አድርጎ የገዛውና ከመጨረሻዎቹ ከራፋይም ዘሮች አንዱ የሆነው የባሳን ንጉሥ ዐግ፣

5የአርሞንዔምን ተራራ፣ ሰልካንን፣ ባሳንን ሁሉ እስከ ጌሹራውያንና እስከ ማዕካታውያን ድንበሮች እንዲሁም ከገለዓድ እኩሌታ እስከ ሐሴቦን ንጉሥ እስከ ሴዎን ወሰን ድረስ ገዝቷል።

6የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴና እስራኤላውያን እነዚህን ድል አደረጉ፤ የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴም ምድራቸውን ለሮቤል፣ ለጋድና ለምናሴ ነገድ እኩሌታ ርስት አድርጎ ሰጣቸው።

7እንግዲህ ኢያሱና እስራኤላውያን ከዮርዳኖስ በስተ ምዕራብ ድል ያደረጓቸው የምድሪቱ ነገሥታት እነዚህ ናቸው፤ ግዛታቸውም በሊባኖስ ሸለቆ ውስጥ ካለው ከበኣልጋድ ተነሥቶ በምዕራብ ሴይር እስካለው እስከ ሐላቅ ተራራ ይደርሳል፤ ኢያሱም የእነዚህን ነገሥታት ምድር እንደ ነገዳቸው አከፋፈል ለእስራኤላውያን በማከፋፈል ርስት አድርጎ ሰጣቸው። 8ይህም ተራራማው አገር፤ በስተ ምዕራብ ያለው የኰረብታ ግርጌ፣ ዓረባ፣ የተራራው ሸንተረሮች፣ ምድረ በዳውና ነጌብ ማለት የኬጢያውያን፣ የአሞራውያን፣ የከነዓናውያን፣ የፌርዛውያን፣ የኤዊያውያንና የኢያቡሳውያን ምድር ነው፤ ነገሥታቱም እነዚህ ናቸው፤

9የኢያሪኮ ንጉሥ፣ አንድ፤

ቤቴል አጠገብ ያለችው የጋይ ንጉሥ፣ አንድ፤

10የኢየሩሳሌም ንጉሥ፣ አንድ፤

የኬብሮን ንጉሥ፣ አንድ፤

11የየርሙት ንጉሥ፣ አንድ፤

የለኪሶ ንጉሥ፣ አንድ፤

12የዔግሎን ንጉሥ፣ አንድ፤

የጌዝር ንጉሥ፣ አንድ፤

13የዳቤር ንጉሥ፣ አንድ፤

የጌድር ንጉሥ፣ አንድ፤

14የሔርማ ንጉሥ፣ አንድ፤

የዓራድ ንጉሥ፣ አንድ፤

15የልብና ንጉሥ፣ አንድ፤

የዓዶላም ንጉሥ፣ አንድ፤

16የመቄዳ ንጉሥ፤ አንድ፤

የቤቴል ንጉሥ፣ አንድ፤

17የታጱዋ ንጉሥ፣ አንድ፤

የኦፌር ንጉሥ፣ አንድ፤

18የአፌቅ ንጉሥ፣ አንድ፤

የለሸሮን ንጉሥ፣ አንድ፤

19የማዶን ንጉሥ፣ አንድ፤

የሐጾር ንጉሥ፣ አንድ፤

20የሺምሮን ሚሮን ንጉሥ፣ አንድ፤

የአዚፍ ንጉሥ፣ አንድ፤

21የታዕናክ ንጉሥ፣ አንድ፤

የመጊዶ ንጉሥ፣ አንድ፤

22የቃዴስ ንጉሥ፣ አንድ፤

በቀርሜሎስ የሚገኘው የዮቅንዓም ንጉሥ፣ አንድ፤

23በዶር ኰረብታ12፥23 ወይም፣ “ናፎት ዳር” ማለት ነው። የሚገኘው የዶር ንጉሥ፣ አንድ፤

በጌልገላ የሚገኘው የጎይም ንጉሥ፣ አንድ፤

24የቲርሳ ንጉሥ፣ አንድ።

እነዚህ በድምሩ ሠላሳ አንድ ነገሥታት ናቸው።

Священное Писание

Иешуа 12:1-24

Список побеждённых царей

1Вот цари, которых победили исраильтяне, и чьи земли они взяли к востоку от Иордана, от реки Арнон до горы Хермон, со всей восточной частью Иорданской долины:

2Сигон, царь аморреев, живший в Хешбоне. Он властвовал от Ароера, что на берегу реки Арнон, и от середины долины до реки Иаббок, границы аммонитян, – это половина Галаада. 3Ещё он владел Иорданской долиной к востоку от Генисаретского озера до Мёртвого моря12:3 Букв.: «до моря Аравы, Солёного моря»., к востоку по дороге к Бет-Иешимоту, а потом к югу под склонами Фасги.

4Ог, царь Башана, один из последних рефаитов, живший в Аштароте и Эдреи. 5Он властвовал над горой Хермон, Салехой, и всем Башаном до границы жителей Гешура и Маахи, и над половиной Галаада до границы Сигона, царя Хешбона.

6Муса, раб Вечного, и исраильтяне разбили их. Муса, раб Вечного, отдал их землю во владение родам Рувима, Гада и половине рода Манассы.

7Вот цари земли, которых Иешуа разбил к западу от Иордана, от Баал-Гада в Ливанской долине до горы Халак, которая высится к Сеиру (их земли Иешуа отдал в наследие родам Исраила по их родовым разделениям – 8нагорья, западные предгорья, Иорданскую долину, горные склоны, пустыню и Негев – земли хеттов, аморреев, хананеев, перизеев, хивеев и иевусеев):

9царь Иерихона одинцарь Гая (что рядом с Вефилем) один10царь Иерусалима одинцарь Хеврона один11царь Иармута одинцарь Лахиша один12царь Эглона одинцарь Гезера один13царь Девира одинцарь Гедера один14царь Хормы одинцарь Арада один15царь Ливны одинцарь Адуллама один16царь Маккеды одинцарь Вефиля один17царь Таппуаха одинцарь Хефера один18царь Афека одинцарь Лашарона один19царь Мадона одинцарь Хацора один20царь Шимрон-Мерона одинцарь Ахшафа один21царь Таанаха одинцарь Мегиддо один22царь Кедеша одинцарь Иокнеама (что при Кармиле) один23царь Дора (что при возвышенностях Дора12:23 Или: «при Нафот-Доре».) одинцарь народов Галилеи12:23 Или: «Гоима в Гилгале». один24царь Тирцы один

Всего – тридцать один царь.