ኢያሱ 10 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 10:1-43

ፀሓይ ቆመች

1የኢየሩሳሌም ንጉሥ አዶኒጼዴቅ፣ ኢያሱ ጋይን ይዞ እንደ ደመሰሳት10፥1 የዕብራይስጡ ቃል በዚህም ሆነ በቍጥር 28፡35፡37፡39 እና 40 ላይ ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠት ማለት ነው።፣ እንደዚሁም በኢያሪኮና በንጉሥዋ ላይ ያደረገውን ሁሉ፣ በጋይና በንጉሥዋ ላይ ማድረጉን፣ የገባዖን ሰዎችም ከእስራኤል ጋር የሰላም ውል አድርገው በአጠገባቸው መኖራቸውን ሰማ። 2በዚህም እርሱና ሕዝቡ ደነገጡ፤ ምክንያቱም ገባዖን እንደ ነገሥታቱ ከተማ ሁሉ ታላቅ ከተማ፣ በስፋቷም ከጋይ የምትበልጥ፣ ሰዎቿም ብርቱ ተዋጊዎች ነበሩ። 3ስለዚህ የኢየሩሳሌም ንጉሥ አዶኒጼዴቅ፣ ሆሃም ወደ ተባለው የኬብሮን ንጉሥ ጲርአም ወደተባለው የየርሙት ንጉሥ፣ ያፊዓ ወደ ተባለው የለኪሶ ንጉሥና ዳቤር ወደተባለው የዔግሎን ንጉሥ በመላክ፣ 4“ወደዚህ ወጥታችሁ አግዙኝ፤ ከኢያሱና ከእስራኤላውያን ጋር ሰላምን መሥርታለችና ገባዖንን እንምታ” አላቸው።

5ከዚያም አምስቱ የአሞራውያን ነገሥታት ማለት የኢየሩሳሌም ንጉሥ፣ የኬብሮን ንጉሥ፣ የያርሙት ንጉሥ፣ የለኪሶ ንጉሥና የዔግሎን ንጉሥ ያላቸውን አስተባብረው፣ ሰራዊታቸውንም ሁሉ ይዘው በመውጣት ገባዖንን ወጓት።

6የገባዖንም ሰዎች በጌልገላ ወደ ሰፈረው ወደ ኢያሱ፣ “በተራራማው አገር የሚኖሩ የአሞራውያን ነገሥታት ኀይላቸውን አስተባብረው ተሰልፈውብናል፤ እኛን ባሮችህን አትተወን፤ ርዳን፤ ፈጥነህ በመድረስም አድነን” ሲሉ ላኩበት።

7ስለዚህ ኢያሱ ምርጥ የሆኑትን ተዋጊዎች ሁሉ ጨምሮ ሰራዊቱን በሙሉ ይዞ ከጌልገላ ወጣ። 8እግዚአብሔርም ኢያሱን፣ “አትፍራቸው፤ ሁሉንም አሳልፌ በእጅህ ሰጥቻቸዋለሁ፤ አንዳቸውም እንኳ ሊቋቋሙህ አይችሉም” አለው።

9ኢያሱ ከጌልገላ ሌሊቱን ሁሉ ሲገሠግሥ ዐድሮ ድንገት ወረራቸው። 10እግዚአብሔርም የአሞራውያንን ነገሥታት በእስራኤል ፊት አሸበራቸው፤ በገባዖን እጅግ መታቸው፤ ወደ ቤትሖሮን በሚያስወጣውም መንገድ ሽቅብ ተከተላቸው፤ እስከ ዓዜቅና እስከ መቄዳም ድረስ አሳድዶ መታቸው። 11ከቤትሖሮን ወደ ዓዜቃ ቍልቍል በሚወስደው መንገድ ላይ፣ ከእስራኤላውያን ፊት በሚሸሹበት ጊዜ፣ እግዚአብሔር ከሰማይ ትልልቅ የበረዶ ድንጋይ አወረደባቸው፤ በእስራኤላውያን ሰይፍ ካለቁት ይልቅ በወረደው የበረዶ ድንጋይ ያለቁት በልጠው ተገኙ።

12እግዚአብሔር አሞራውያንን ለእስራኤል አሳልፎ በሰጠባት ዕለት፣ ኢያሱ እግዚአብሔርን በእስራኤል ፊት እንዲህ አለው፤

“ፀሓይ ሆይ፤ በገባዖን ላይ ቁሚ፤

ጨረቃም ሆይ፤ በኤሎን ሸለቆ ላይ ቀጥ በዪ።”

13ስለዚህ ሕዝቡ ጠላቶቹን እስኪበቀል

ድረስ10፥13 ወይም ሕዝቡ እስኪያሸንፍ ድረስ፣ ፀሓይ ባለችበት ቆመች፤

ጨረቃም አልተንቀሳቀሰችም።

ይህም በያሻር መጽሐፍ ተጽፎ ይገኛል።

ፀሓይ በሰማዩ መካከል ቆመች፤ ለመጥለቅም ሙሉ ቀን ፈጀባት። 14እግዚአብሔር የሰውን ቃል የሰማበት እንደዚያ ያለ ዕለት ከዚያ በፊትም ሆነ ከዚያ በኋላ አልነበረም፤ እግዚአብሔር ለእስራኤል ተዋግቶ ነበርና።

15ከዚያም ኢያሱ ከመላው እስራኤል ጋር ጌልገላ ወዳለው ሰፈር ተመለሰ።

አምስቱ የአሞራውያን ነገሥታት ተገደሉ

16በዚህ ጊዜ አምስቱ የአሞራውያን ነገሥታት ሸሽተው በመቄዳ ዋሻ ተደብቀው ነበር። 17ኢያሱም አምስቱ ነገሥታት በመቄዳ ዋሻ ውስጥ ተደብቀው መገኘታቸውን ሰማ፤ 18እንዲህም አለ፤ “ትልልቅ ድንጋዮች ወደ ዋሻው አፍ አንከባሉ፤ ጠባቂ ሰዎችንም በዚያ አቁሙ፤ 19ጠላቶቻችሁን አሳድዷቸው እንጂ ችላ አትበሉ፤ ከበስተ ኋላ ሆናችሁም አደጋ ጣሉባቸው፤ ወደ ከተሞቻቸው እንዳይገቡ ከልክሏቸው፤ እነሆ፤ እግዚአብሔር አምላካችሁ በእጃችሁ አሳልፎ ሰጥቷቸዋልና።”

20ስለዚህ ኢያሱና እስራኤላውያን እስከ መጨረሻው ደመሰሷቸው፤ የተረፉት ጥቂቶቹ ግን ወደ ተመሸጉት ከተሞቻቸው ለመድረስ ቻሉ። 21ከዚያም ሰራዊቱ ሁሉ በደኅና ተመልሶ፣ ኢያሱ ወደ ሰፈረበት ወደ መቄዳ መጣ፤ በእስራኤላውያንም ላይ አንዲት ቃል የተናገረ ሰው አልነበረም።

22ኢያሱም፤ “ዋሻውን ከፍታችሁ እነዚያን አምስቱን ነገሥታት አውጥታችሁ አምጡልኝ” አላቸው። 23እነርሱም አምስቱን ነገሥታት ማለትም የኢየሩሳሌምን ንጉሥ፣ የኬብሮንን ንጉሥ፣ የያርሙትን ንጉሥ፣ የለኪሶን ንጉሥ የዔግሎንን ንጉሥ አውጥተው አመጡለት። 24እነዚህን ነገሥታት ባመጡለትም ጊዜ፣ ኢያሱ መላውን የእስራኤልን ወንዶች ከጠራ በኋላ አብረውት የመጡትን የጦር አዛዦች፣ “ወደዚህ ቅረቡና እግሮቻችሁን በእነዚህ ነገሥታት ዐንገት ላይ አድርጉ” አላቸው፤ እነርሱም ወደ ፊት ቀርበው እግራቸውን በነገሥታቱ ዐንገት ላይ አሳረፉ።

25ኢያሱም፣ “አትፍሩ፤ አትደንግጡ፤ በርቱ፤ ጽኑ፤ እንግዲህ በምትወጓቸው ጠላቶች ሁሉ ላይ እግዚአብሔር እንደዚሁ ያደርጋልና” አላቸው። 26ከዚያም ኢያሱ ነገሥታቱን መትቶ ገደላቸው፤ በአምስትም ዛፎች ላይ ሰቀላቸው፤ ሬሳቸውም እስኪመሽ ድረስ አልወረደም ነበር።

27ፀሓይ ለመጥለቅ በማዘቅዘቅ ላይ ሳለች ኢያሱ ትእዛዝ ሰጠ፤ ከዚያም የነገሥታቱን ሬሳ ከዛፎቹ ላይ አውርደው ቀድሞ ተደብቀው ወደ ነበሩበት ዋሻ ውስጥ ጣሏቸው። በዋሻውም አፍ ትልልቅ ድንጋዮች አኖሩ፤ ድንጋዮቹም እስከ ዛሬ ድረስ በዚያ ይገኛሉ።

28በዚያች ዕለት ኢያሱ መቄዳን ያዘ፤ ከተማዪቱንና ንጉሥዋንም በሰይፍ ስለት መታ፤ አንድም ሰው ሳያስቀር በውስጧ ያለውን ሁሉ ፈጽሞ ደመሰሰ፤ በኢያሪኮ ንጉሥ ላይ ያደረገውንም ሁሉ፣ በመቄዳ ንጉሥ ላይ አደረገ።

የደቡብ ከተሞች መያዝ

29ከዚያም ኢያሱና ከእርሱ ጋር የነበሩት እስራኤላውያን በሙሉ ከመቄዳ ወደ ልብና ዐለፉ፤ ወጓትም። 30እንዲሁም እግዚአብሔር ከተማዪቱንና ንጉሥዋን በእስራኤል እጅ አሳልፎ ሰጣቸው። ኢያሱ ከተማዪቱንና በውስጧ ያለውን ሁሉ በሰይፍ ስለት አጠፋ፤ አንድም ሰው አላስተረፈም። በኢያሪኮ ንጉሥ ላይ ያደረገውንም በልብና ንጉሥ ላይ ደገመው።

31ከዚያም ኢያሱና ከእርሱ ጋር የነበሩት እስራኤላውያን በሙሉ ከልብና ወደ ለኪሶ ዐለፉ፤ ወጓትም። 32እግዚአብሔር ለኪሶን አሳልፎ ለእስራኤል ሰጠ፤ ኢያሱም በሁለተኛው ቀን ያዛት፤ በልብና እንዳደረገው ሁሉ እዚህም ከተማዪቱንና በውስጧ ያሉትን ሁሉ በሰይፍ ስለት ፈጃቸው። 33በዚህ ጊዜ የጌዝር ንጉሥ ሆራም ለኪሶን ለመርዳት መጣ፤ ኢያሱ ግን አንድ እንኳ ሳያስተርፍ ንጉሡንና ሕዝቡን መታቸው።

34ከዚያም ኢያሱና ከእርሱ ጋር የነበሩት እስራኤላውያን በሙሉ ከለኪሶ ወደ ዔግሎን ዐለፉ፤ ወጓትም። 35በዚያኑ ዕለት ያዟት፤ በሰይፍም ስለት አጠፏት፤ በለኪሶ እንዳደረጉት ሁሉ እዚህም በውስጧ የሚገኙትን ፈጽመው ደመሰሷቸው።

36ከዚያም ኢያሱና ከእርሱ ጋር የነበሩት እስራኤላውያን በሙሉ ከዔግሎን ወደ ኬብሮን ወጡ፤ ወጓትም። 37ከተማዪቱንም ከንጉሧ፣ ከመንደሮቿና በውስጧ ካሉት ጋር ሁሉ አንድም ሰው ሳያስቀሩ በሰይፍ ስለት ፈጇቸው፤ በዔግሎን እንዳደረጉት ሁሉ እዚህም ከተማዪቱንና በውስጧ ያለውን ሁሉ ፈጽመው ደመሰሱ።

38ከዚያም ኢያሱና ከእርሱ ጋር የነበሩት እስራኤላውያን በሙሉ ወደ ኋላ ተመልሰው ዳቤርን ወጓት። 39ከተማዪቱን፣ ንጉሥዋንና መንደሮቿን ይዘው በሰይፍ ስለት ፈጇቸው፤ በውስጧ ያለውንም ሁሉ አንድም ሳያስቀሩ ደመሰሱ፤ በልብናና በንጉሥዋ እንዲሁም በኬብሮን ያደረጉትን ሁሉ እዚህም በዳቤርና በንጉሥዋ ላይ ደገሙት።

40በዚህ ሁኔታም ኢያሱ ተራራማውን አገር ኔጌቭን፣ የምዕራቡን ቈላና የተራራውን ሸንተረሮች ጨምሮ ምድሪቱን በሙሉ ከነገሥታቷ ጋር ያዘ። የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ባዘዘውም መሠረት፣ እስትንፋስ ያላቸውን ሁሉ ፈጽሞ ደመሰሰ፤ ማንንም በሕይወት አላስቀረም። 41ኢያሱም ከቃዴስ በርኔ እስከ ጋዛ እንዲሁም የጎሶምን ምድር ሁሉ እስከ ገባዖን ድረስ በሙሉ ያዘ። 42ኢያሱ እነዚህን ሁሉ ነገሥታትና ምድራቸውን ያሸነፈው በአንድ ዘመቻ ብቻ ነበር፤ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ተዋግቶላቸዋልና።

43ከዚህ በኋላ ኢያሱ ከመላው እስራኤላውያን ጋር ጌልገላ ወዳለው ሰፈር ተመለሰ።

Thai New Contemporary Bible

โยชูวา 10:1-43

ดวงอาทิตย์หยุดนิ่ง

1เมื่อกษัตริย์อาโดนีเซเดคแห่งเยรูซาเล็มได้ยินเรื่องราวที่โยชูวาเข้ายึดและทำลายล้างเมืองอัยให้หมดสิ้นและฆ่ากษัตริย์ของเมืองนั้น เช่นเดียวกับที่ได้ทำลายเมืองเยรีโคและกษัตริย์ของเมืองนั้น และเรื่องที่ชาวเมืองกิเบโอนได้ทำสัญญาไมตรีกับอิสราเอลและอาศัยอยู่ใกล้พวกเขาแล้ว 2เขากับประชาชนของเขาก็หวั่นวิตกยิ่งนัก เพราะกิเบโอนเป็นเมืองสำคัญเท่ากับนครหลวงทั้งหลาย และใหญ่กว่าเมืองอัย ชายทั้งปวงก็ล้วนแต่เป็นนักรบแกล้วกล้า 3ดังนั้นกษัตริย์อาโดนีเซเดคแห่งเยรูซาเล็ม จึงส่งคนไปพบกษัตริย์อื่นๆ คือ กษัตริย์โฮฮัมแห่งเฮโบรน กษัตริย์ปิรามแห่งยารมูท กษัตริย์ยาเฟียแห่งลาคีช และกษัตริย์เดบีร์แห่งเอกโลน และขอร้องว่า 4“โปรดมาช่วยเราโจมตีกิเบโอน เพราะพวกเขาได้ไปทำสัญญาไมตรีกับโยชูวาและชนอิสราเอล”

5กษัตริย์ทั้งห้าของชาวอาโมไรต์คือ กษัตริย์แห่งเยรูซาเล็ม เฮโบรน ยารมูท ลาคีช และเอกโลน จึงรวมกำลังกัน และเคลื่อนทัพออกมาบุกโจมตีกิเบโอน

6ชาวกิเบโอนจึงส่งข่าวมาถึงโยชูวาที่ค่ายพักในกิลกาลว่า “ขออย่าทอดทิ้งผู้รับใช้ของท่าน โปรดมาช่วยพวกเราโดยเร็ว โปรดช่วยพวกเราด้วย เพราะกษัตริย์ทั้งปวงของชาวอาโมไรต์จากแถบเทือกเขาได้รวมกำลังกันมาโจมตีเราแล้ว”

7โยชูวากับกองกำลังทั้งหมดรวมทั้งนักรบชั้นยอดทั้งปวงจึงยกทัพออกจากกิลกาลไปช่วยกิเบโอน 8องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโยชูวาว่า “อย่ากลัวพวกเขาเลย เรามอบคนเหล่านี้ไว้ในมือของเจ้าแล้ว จะไม่มีใครยืนหยัดต่อสู้เจ้าได้”

9โยชูวากับพวกเดินทางตลอดคืนจากกิลกาล เข้าจู่โจมกองทัพของศัตรู โดยที่ฝ่ายนั้นไม่ทันรู้ตัว 10องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงกระทำให้พวกเขาแตกตื่นต่อหน้าอิสราเอล ซึ่งได้รับชัยชนะยิ่งใหญ่ที่กิเบโอน อิสราเอลตามฆ่าพวกเขาตลอดทางขึ้นไปเบธโฮโรนถึงอาเซคาห์และมักเคดาห์ 11ขณะที่ศัตรูวิ่งหนีมาตามทางจากเบธโฮโรนไปยังอาเซคาห์ องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงทำลายพวกเขาด้วยลูกเห็บขนาดใหญ่จากท้องฟ้า คนตายเพราะลูกเห็บมากยิ่งกว่าด้วยคมดาบของชาวอิสราเอล

12ในวันที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงกระทำให้ชาวอาโมไรต์พ่ายแพ้อิสราเอล โยชูวากราบทูลองค์พระผู้เป็นเจ้าต่อหน้าอิสราเอลว่า

“ขอให้ดวงอาทิตย์หยุดนิ่งอยู่เหนือกิเบโอน

ขอให้ดวงจันทร์หยุดอยู่กับที่เหนือหุบเขาอัยยาโลน”

13ดังนั้นดวงอาทิตย์ก็หยุดนิ่ง

และดวงจันทร์หยุดโคจร

ตราบจนชนชาตินั้นแก้แค้นศัตรูราบคาบ10:13 หรือมีชัยเหนือศัตรู

ดังที่มีบันทึกไว้ในหนังสือของยาชาร์

ดวงอาทิตย์ค้างอยู่กลางท้องฟ้าและไม่ได้ตกดินเป็นเวลาหนึ่งวันเต็ม 14ไม่เคยมีวันแบบนั้นมาก่อน และจะไม่มีวันแบบนั้นอีกเลย ที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงฟังคำอธิษฐานของมนุษย์อย่างนั้น องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงต่อสู้เพื่ออิสราเอลอย่างแน่นอน!

15แล้วโยชูวากับอิสราเอลทั้งปวงก็กลับมายังค่ายพักที่กิลกาล

กษัตริย์อาโมไรต์ทั้งห้าถูกฆ่า

16ฝ่ายกษัตริย์ทั้งห้าองค์หลบหนีไปซ่อนตัวอยู่ในถ้ำที่มักเคดาห์ 17เมื่อโยชูวาได้รับรายงานว่าพบกษัตริย์ทั้งห้าซ่อนตัวอยู่ในถ้ำที่มักเคดาห์ 18เขาจึงสั่งว่า “จงกลิ้งหินก้อนใหญ่ปิดปากถ้ำและวางทหารเฝ้าไว้ 19แต่อย่ารามือ! จงตามล่าศัตรู ตีขนาบจากด้านหลัง อย่าปล่อยให้พวกเขากลับเข้าเมืองได้ เพราะพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านทรงมอบพวกเขาไว้ในมือของท่านแล้ว”

20โยชูวากับชนอิสราเอลจึงทำลายล้างพวกเขาหมดสิ้น ประหารเกือบทุกคน มีไม่กี่คนที่หนีไปถึงเมืองป้อมปราการของตน 21ทั้งกองทัพกลับมาหาโยชูวายังค่ายพักที่มักเคดาห์อย่างปลอดภัยทุกคน หลังจากนั้นไม่มีผู้ใดกล้าเอ่ยปากว่าชาวอิสราเอลอีกเลย

22โยชูวาสั่งว่า “จงเปิดปากถ้ำและนำตัวกษัตริย์ทั้งห้าออกมาหาเรา” 23ดังนั้นพวกเขาจึงนำกษัตริย์ทั้งห้าออกมาจากถ้ำ คือกษัตริย์แห่งเยรูซาเล็ม เฮโบรน ยารมูท ลาคีช และเอกโลน 24เมื่อพวกเขานำเหล่ากษัตริย์มาหาโยชูวา โยชูวาเรียกประชุมชายชาวอิสราเอลทั้งหมดและสั่งแม่ทัพนายกองที่มากับตนว่า “จงเหยียบคอกษัตริย์เหล่านี้” พวกเขาก็ก้าวออกมาเหยียบคอกษัตริย์ทั้งห้านั้น

25โยชูวากล่าวกับพวกเขาว่า “อย่ากลัวหรือท้อใจเลย จงเข้มแข็งและกล้าหาญเถิด องค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงกระทำเช่นนี้ต่อศัตรูทั้งปวงที่ท่านจะต่อสู้ด้วย” 26แล้วโยชูวาก็ประหารกษัตริย์ทั้งห้าและแขวนไว้บนต้นไม้ห้าต้นจนถึงเวลาเย็น

27เมื่อดวงอาทิตย์ตกดิน โยชูวาสั่งให้ปลดร่างของกษัตริย์ทั้งห้านั้นลงจากต้นไม้ มาโยนทิ้งในถ้ำที่พวกเขาเคยหลบซ่อนตัว แล้วให้สุมก้อนหินเป็นกองพะเนินตรงปากถ้ำ ซึ่งยังคงอยู่ที่นั่นตราบจนทุกวันนี้

มีชัยเหนือเมืองทางใต้

28ในวันนั้นโยชูวาเข้ายึดเมืองมักเคดาห์ ฆ่ากษัตริย์ด้วยดาบและทำลายล้างทุกคนในเมืองนั้นจนหมดสิ้น ทั่วทั้งเมืองไม่มีผู้ใดรอดชีวิตอยู่ แล้วโยชูวาก็ทำต่อกษัตริย์แห่งมักเคดาห์เหมือนที่ได้ทำต่อกษัตริย์แห่งเยรีโค

29แล้วโยชูวากับชาวอิสราเอลทั้งปวงจึงเคลื่อนพลออกจากมักเคดาห์เพื่อไปโจมตีลิบนาห์ 30ที่นั่นก็เช่นเดียวกัน องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงมอบเมืองนั้นและกษัตริย์ไว้ในมืออิสราเอล ชาวเมืองทุกคนถูกประหารหมดสิ้นไม่เหลือรอดสักคนเดียว แล้วโยชูวาก็ทำต่อกษัตริย์ของเมืองนั้นเหมือนที่ได้ทำต่อกษัตริย์เยรีโค 31จากลิบนาห์ โยชูวากับอิสราเอลทั้งปวงเข้าโจมตีลาคีช 32องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงมอบลาคีชแก่อิสราเอล ในวันที่สองโยชูวายึดเมืองได้ เขาทำลายเมืองนั้นและฆ่าฟันชาวเมืองทุกคนเช่นเดียวกับที่ลิบนาห์ 33ระหว่างการเข้าโจมตีลาคีช กษัตริย์โฮรามแห่งเกเซอร์ยกทัพมาช่วยป้องกันเมือง แต่พ่ายแพ้โยชูวากับกองทัพและถูกฆ่าตายหมด

34จากลาคีชโยชูวากับอิสราเอลทั้งปวงบุกเข้าโจมตีเมืองเอกโลน 35พวกเขายึดเมืองได้ในวันนั้นเองและฆ่าฟันด้วยดาบ และทำลายล้างทุกคนในเมืองนั้นจนหมดสิ้นเหมือนที่ได้ทำต่อลาคีช

36จากเอกโลนโยชูวากับอิสราเอลทั้งปวงบุกเข้าโจมตีเมืองเฮโบรน 37เข้ายึดเมืองและหมู่บ้านโดยรอบ เขาฆ่ากษัตริย์และชาวเมืองทั้งหมดด้วยดาบ ไม่มีเหลือรอดแม้สักคนเดียว พวกเขาทำลายล้างเมืองและทุกคนจนหมดสิ้นเช่นเดียวกับที่ได้ทำต่อเอกโลน

38แล้วโยชูวากับอิสราเอลทั้งปวงกลับลงไปโจมตีเดบีร์ 39พวกเขาเข้ายึดเมืองพร้อมทั้งหมู่บ้านต่างๆ ฆ่าฟันกษัตริย์และชาวเมืองทุกคนด้วยดาบ พวกเขาทำลายล้างทุกคนจนหมดสิ้นเหมือนที่ได้ทำต่อลิบนาห์และเฮโบรน ไม่มีเหลือรอดสักคนเดียว

40เป็นอันว่าโยชูวาพิชิตดินแดนแถบนั้นทั้งหมด ไม่ว่าแถบเทือกเขาเนเกบ เชิงเขาด้านตะวันตก ลาดเขา ตลอดจนกษัตริย์ทั้งปวง ไม่มีเหลือรอดแม้สักคนเดียว โยชูวาทำลายล้างทุกสิ่งที่มีลมหายใจตามที่พระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลทรงบัญชาไว้ 41โยชูวาปราบหมดตั้งแต่คาเดชบารเนียจนจดกาซา และจากเขตแดนโกเชนทั้งหมดจนถึงกิเบโอน 42โยชูวารบชนะกษัตริย์ต่างๆ และดินแดนของเขาทั้งหมดในคราวเดียวกัน เพราะพระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลทรงสู้รบเพื่ออิสราเอล

43แล้วโยชูวากับอิสราเอลทั้งปวงกลับคืนสู่ค่ายพักในกิลกาล