ኢዩኤል 2 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ኢዩኤል 2:1-32

የአንበጣ ሰራዊት

1በጽዮን መለከትን ንፉ፤

በቅዱሱ ተራራዬም የማስጠንቀቂያውን ድምፅ አሰሙ።

በምድሪቱ የሚኖሩ ሁሉ ይንቀጥቀጡ፤

የእግዚአብሔር ቀን ቀርቧልና፤

እርሱም በደጅ ነው።

2ይህም የጨለማና የጭጋግ ቀን፣

የደመናና የድቅድቅ ጨለማ ቀን ነው።

የንጋት ብርሃን በተራሮች ላይ እንደሚወጣ፣

ኀያልና ብዙ ሰራዊት ይመጣል፤

ከጥንት እንዲህ ዐይነት ከቶ አልነበረም፤

በሚመጡትም ዘመናት እንዲህ ዐይነት ከቶ አይሆንም።

3በፊታቸው፣ እሳት ይባላል፤

በኋላቸውም ነበልባል ይለበልባል፤

በፊታቸው ምድሪቱ እንደ ዔድን ገነት ናት፤

በኋላቸውም የሚቀረው ባዶ ምድረ በዳ ነው፤

ምንም አያመልጣቸውም።

4መልካቸው እንደ ፈረስ መልክ ነው፤

እንደ ጦር ፈረስም ይጋልባሉ።

5ገለባ እንደሚበላ እንደሚንጣጣ እሳት፣

ለጦርነት እንደ ተዘጋጀ ኀያል ሰራዊት፣

የሠረገሎችን ድምፅ የሚመስል ድምፅ እያሰሙ፣

በተራሮች ጫፍ ላይ ይዘልላሉ።

6በእነርሱ ፊት ሕዝቦች ይርዳሉ፤

የሁሉም ፊት ይገረጣል።

7እንደ ተዋጊዎች ድንገት አደጋ ይጥላሉ፤

እንደ ወታደሮችም ቅጥርን ይዘልላሉ፤

ከመንገዳቸውም ሳይወጡ፣

አቅጣጫ ይዘው ይጓዛሉ።

8እርስ በርሳቸው አይገፋፉም፤

እያንዳንዱ መሥመሩን ጠብቆ ይሄዳል፤

መሥመራቸውን ሳይለቁ፣

መከላከያውን ሰብረው ያልፋሉ።

9ከተማዪቱን ይወርራሉ፤

በቅጥሩም ላይ ይዘልላሉ፤

በቤቶች ላይ ዘልለው ይወጣሉ፤

እንደ ሌባም በመስኮት ይገባሉ።

10ምድር በፊታቸው ትንቀጠቀጣለች፤

ሰማይም ይናወጣል፤

ፀሓይና ጨረቃ ይጨልማሉ፤

ከዋክብትም ከእንግዲህ ወዲያ አያበሩም።

11በሰራዊቱ ፊት፣

እግዚአብሔር ያንጐደጕዳል፤

የሰራዊቱ ብዛት ስፍር ቍጥር የለውም፤

ትእዛዙንም የሚያደርግ እርሱ ኀያል ነው፤

የእግዚአብሔር ቀን ታላቅ፣

እጅግም የሚያስፈራ ነው፤

ማንስ ሊቋቋመው ይችላል?

ልባችሁን ቅደዱ

12“አሁንም ቢሆን፣

በጾም፣ በልቅሶና በሐዘን፣

በፍጹም ልባችሁ ወደ እኔ ተመለሱ” ይላል እግዚአብሔር

13ልባችሁን እንጂ፣

ልብሳችሁን አትቅደዱ፤

ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ፤

እርሱ መሓሪና ርኅሩኅ፣

ቍጣው የዘገየና ፍቅሩ የበዛ፣

ክፉ ነገር ከማምጣትም የሚታገሥ ነውና።

14በምሕረቱ ተመልሶ፣

ለአምላካችሁ ለእግዚአብሔር የሚሆነውን፣

የእህል ቍርባንና የመጠጥ ቍርባን እንዲተርፋችሁ፣

በረከቱን ይሰጣችሁ እንደ ሆነ ማን ያውቃል?

15በጽዮን መለከትን ንፉ፤

ቅዱስ ጾምን ዐውጁ፤

የተቀደሰን ጉባኤ ጥሩ።

16ሕዝቡን ሰብስቡ፤

ጉባኤውን ቀድሱ፤

ሽማግሌዎችን በአንድነት አቅርቡ፤

ሕፃናትን ሰብስቡ፤

ጡት የሚጠቡትንም አታስቀሩ፤

ሙሽራው እልፍኙን ይተው፣

ሙሽሪትም የጫጕላ ቤቷን ትተው።

17በእግዚአብሔር ፊት የሚያገለግሉ ካህናት፣

በመሠዊያውና በቤተ መቅደሱ አደባባይ መካከል ሆነው ያልቅሱ፤

እንዲህም ይበሉ፤ “እግዚአብሔር ሆይ፤ ሕዝብህን አድን፤

ርስትህን በአሕዛብ መካከል መተረቻ፣

መሣቂያና መሣለቂያም አታድርግ፤

ለምንስ በሕዝቦች መካከል፣

‘አምላካቸው ወዴት ነው?’ ይበሉን።”

የእግዚአብሔር መልስ

18እነሆ፤ እግዚአብሔር ስለ ምድሩ ይቀናል2፥18 ወይም ጌታ ቀንቷል ራርቷል

ስለ ሕዝቡም ይራራል።

19እግዚአብሔርም እንዲህ ሲል ይመልስላቸዋል2፥19 ጌታ መለሰለት

“እህል፣ አዲስ የወይን ጠጅና ዘይት፣

እስክትጠግቡ ድረስ እሰጣችኋለሁ፤

የሕዝቦች መዘባበቻ አላደርጋችሁም።

20“የሰሜንን ሰራዊት ከእናንተ አርቃለሁ፤

ፊቱን ወደ ምሥራቁ ባሕር2፥20 የሙት ባሕር ለማለት ነው።

ጀርባውንም ወደ ምዕራቡ ባሕር2፥20 የሜዲትራንያን ባሕር ለማለት ነው። በማድረግ፣

ወደ ደረቀውና ወደ ባድማው ምድር እገፋዋለሁ፤

ግማቱ ይወጣል፤

ክርፋቱም ይነሣል።”

በርግጥ እርሱ ታላቅ ነገር አድርጓል።

21ምድር ሆይ፤ አትፍሪ፤

ደስ ይበልሽ፤ ሐሤትም አድርጊ፤

በርግጥ እግዚአብሔር ታላቅ ነገር አድርጓል።

22የዱር እንስሳት ሆይ፤ አትፍሩ፤

መሰማሪያ መስኮቹ ለምልመዋልና፤

ዛፎቹ ፍሬያቸውን አፍርተዋል፤

የበለሱ ዛፍና የወይኑ ተክልም እጅግ አፍርተዋል።

23የጽዮን ሰዎች ሆይ፤ ደስ ይበላችሁ፤

በአምላካችሁ በእግዚአብሔር ሐሤት አድርጉ፤

የበልግን ዝናብ፣

በጽድቅ ሰጥቷችኋልና2፥23 ወይም ለጽድቅ መምህር

እንደ ቀድሞውም፣

የበልግንና የጸደይን ዝናብ በብዛት ልኮላችኋል።

24ዐውድማዎቹ በእህል ይሞላሉ፤

መጥመቂያ ጕድጓዶችም በአዲስ የወይን ጠጅና በዘይት ተሞልተው ያፈስሳሉ።

25“በመካከላችሁ የሰደድሁት ታላቁ ሰራዊት፣

ትልልቁ አንበጣና ትንንሹ አንበጣ፣

ሌሎች አንበጦችና የአንበጣው መንጋ2፥25 በዚህ ክፍል ስለ አንበጦች የሚገልጹት አራት የዕብራይስጥ ቃላት ትክክለኛ ትርጕም አይታወቅም። የበላውን፣

እነዚህ ሁሉ የበሏቸውን ዓመታት ዋጋ እመልስላችኋለሁ።

26እስክትጠግቡ የምትበሉት ብዙ ምግብ ይኖራችኋል፤

ድንቅ ነገሮችን ለእናንተ የሠራውን፣

የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ስም ታመሰግናላችሁ፤

ሕዝቤም ከእንግዲህ ወዲያ አያፍርም።

27ከዚያም እኔ በእስራኤል መካከል እንዳለሁ፣

እኔ አምላካችሁ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ፣

እንደ እኔም ያለ፣ ሌላ እንደሌለ ታውቃላችሁ፤

ሕዝቤም ከእንግዲህ ወዲያ አያፍርም።

የእግዚአብሔር ቀን

28“ከዚህም በኋላ፣

መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ አፈስሳለሁ፤

ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁ ትንቢት ይናገራሉ፤

ሽማግሌዎቻችሁ ሕልም ያልማሉ፤

ጕልማሶቻችሁም ራእይ ያያሉ።

29በእነዚያ ቀናት በወንዶችና በሴቶች ባሪያዎች ላይ እንኳ፣

መንፈሴን አፈስሳለሁ።

30ድንቆችን በሰማያት፣

እንዲሁም በምድር፣

ደምና እሳት፣ የጢስም ዐምድ አሳያለሁ።

31ታላቁና የሚያስፈራው የእግዚአብሔር ቀን ከመምጣቱ በፊት፣

ፀሓይ ትጨልማለች፤

ጨረቃም ወደ ደም ትለወጣለች።

32የእግዚአብሔርን ስም የሚጠራ ሁሉ፣

እርሱ ይድናል፤

እግዚአብሔርም እንዳለው፣

በጽዮን ተራራና በኢየሩሳሌም፣

መድኀኒት ይገኛል፤

ከትሩፋኑም መካከል

እግዚአብሔር የጠራቸው በዚያ ይገኛሉ።”

New International Reader’s Version

Joel 2:1-32

The Lord Sends an Army of Locusts

1Priests, blow the trumpets in Zion.

Give a warning on my holy mountain.

Let everyone who lives in the land tremble with fear.

The day of the Lord is coming.

It is very near.

2That day will be dark and sad.

It will be black and cloudy.

A huge army of locusts is coming.

They will spread across the mountains

like the sun when it rises.

There has never been an army like it.

And there will never be another

for all time to come.

3Like fire they eat up everything in their path.

Behind them it looks as if flames have burned the land.

In front of them the land is like the Garden of Eden.

Behind them it is a dry and empty desert.

Nothing escapes them.

4They look like horses.

Like war horses they charge ahead.

5They sound like chariots as they leap over the mountaintops.

They crackle like fire burning up dry weeds.

They are like a mighty army

that is ready for battle.

6When people see them, they tremble with fear.

All their faces turn pale.

7The locusts charge ahead like warriors.

They climb over walls like soldiers.

All of them march in line.

They don’t turn to the right or the left.

8They don’t bump into one another.

Each of them marches straight ahead.

They charge through everything that tries to stop them.

But they still stay in line.

9They attack a city.

They run along its wall.

They climb into houses.

They enter through windows like robbers.

10As they march forward, the earth shakes.

The heavens tremble as they approach.

The sun and moon grow dark.

And the stars stop shining.

11The Lord thunders with his mighty voice

as he leads his army.

He has so many forces they can’t even be counted.

The army that obeys his commands is mighty.

The day of the Lord is great and terrifying.

Who can live through it?

Let Your Hearts Be Broken

12The Lord announces to his people,

“Return to me with all your heart.

There is still time.

Do not eat any food.

Weep and mourn.”

13Don’t just tear your clothes to show how sad you are.

Let your hearts be broken.

Return to the Lord your God.

He is gracious.

He is tender and kind.

He is slow to get angry.

He is full of love.

He won’t bring his judgment.

He won’t destroy you.

14Who knows? He might turn toward you

and not bring his judgment.

He might even give you his blessing.

Then you can bring grain offerings and drink offerings

to the Lord your God.

15Priests, blow the trumpets in Zion.

Announce a holy fast.

Tell the people not to eat anything.

Gather them together for a special service.

16Bring them together.

Set all of them apart to me.

Bring together the elders.

Gather the children and the babies

who are still nursing.

Let the groom leave his bedroom.

Let the bride leave their marriage bed.

17Let the priests who serve the Lord weep.

Let them cry between the temple porch and the altar.

Let them say, “Lord, spare your people.

Don’t let others make fun of them.

Don’t let the nations laugh at them.

Don’t let them tease your people and say,

‘Where is their God?’ ”

The Lord Answers the Prayer of His People

18Then the Lord was concerned for his land.

He took pity on his people.

19He replied,

“I am sending you grain, olive oil and fresh wine.

It will be enough to satisfy you completely.

I will never allow other nations

to make fun of you again.

20“I will drive far away from you

the army that comes from the north.

I will send some of its forces

into a dry and empty land.

Its eastern troops will drown in the Dead Sea.

Its western troops will drown in the Mediterranean Sea.

Their dead bodies will stink.”

The Lord has done great things.

21Land of Judah, don’t be afraid.

Be glad and full of joy.

The Lord has done great things.

22Wild animals, don’t be afraid.

The desert grasslands are turning green again.

The trees are bearing their fruit.

The vines and fig trees are producing rich crops.

23People of Zion, be glad.

Be joyful because of what the Lord your God has done.

He has given you the right amount of rain in the fall.

That’s because he is faithful.

He has sent you plenty of showers.

He has sent fall and spring rains alike,

just as he did before.

24Your threshing floors will be covered with grain.

Olive oil and fresh wine will spill over

from the places where they are stored.

25The Lord says,

“I sent a great army of locusts to attack you.

They included common locusts, giant locusts,

young locusts and other locusts.

I will make up for the years

they ate your crops.

26You will have plenty to eat.

It will satisfy you completely.

Then you will praise me.

I am the Lord your God.

I have done wonderful things for you.

My people will never again be put to shame.

27You will know that I am with you in Israel.

I am the Lord your God.

There is no other God.

So my people will never again be put to shame.

The Day of the Lord Is Coming

28“After that, I will pour out my Spirit on all people.

Your sons and daughters will prophesy.

Your old men will have dreams.

Your young men will have visions.

29In those days I will pour out my Spirit

on those who serve me, men and women alike.

30I will show wonders in the heavens and on the earth.

There will be blood and fire and clouds of smoke.

31The sun will become dark.

The moon will turn red like blood.

It will happen before the great and terrible day of the Lord comes.

32Everyone who calls out to me will be saved.

On Mount Zion and in Jerusalem

some of my people will be left alive.

I have chosen them.

That is what I have promised.