ኢዩኤል 1 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

ኢዩኤል 1:1-20

1ወደ ባቱኤል ልጅ ወደ ኢዩኤል የመጣው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው፤

የአንበጣ ወረራ

2እናንት ሽማግሌዎች፣ ይህን ስሙ፤

በምድሪቱም የምትኖሩ ሁላችሁ፣ አድምጡ፤

በእናንተ ዘመንም ሆነ በአባቶቻችሁ ዘመን፣

እንዲህ ዐይነት ነገር ሆኖ ያውቃልን?

3ይህን ለልጆቻችሁ ተናገሩ፤

ልጆቻችሁ ለልጆቻቸው ይንገሩ፤

ልጆቻቸውም ለሚቀጥለው ትውልድ ይንገሩ።

4ከአንበጣ መንጋ1፥4 በዚህ ክፍል፣ ስለ አንበጦች የሚገልጹት አራት የዕብራይስጥ ቃላት፣ ትክክለኛ ትርጕም አይታወቅም። የተረፈውን፣

ትልልቁ አንበጣ በላው፤

ከትልልቁ አንበጣ የተረፈውን፣

ኵብኵባ በላው፤

ከኵብኵባ የተረፈውን፣

ሌሎች አንበጦች በሉት።

5እናንት ሰካራሞች፤ ተነሡ፤ አልቅሱ፤

እናንት የወይን ጠጅ ጠጪዎች ሁሉ፤ ዋይ በሉ፤

ስለ አዲሱ የወይን ጠጅ ዋይ ብላችሁ አልቅሱ፤

አፋችሁ ላይ እንዳለ ተነጥቃችኋልና።

6ኀያልና ቍጥር ስፍር የሌለው ሕዝብ፣

ምድሬን ወሯታልና፤

ጥርሱ እንደ አንበሳ ጥርስ፣

መንጋጋውም እንደ እንስት አንበሳ መንጋጋ ነው።

7የወይን ቦታዬን ባድማ አደረገው፤

የበለስ ዛፎቼንም ቈራረጠ፤

ቅርንጫፎቻቸው ነጭ ሆነው እስኪታዩ ድረስ፣

ቅርፊታቸውን ልጦ፣

ወዲያ ጣላቸው።

8የልጅነት ዕጮኛዋን1፥8 ወይም የልጅነት ባሏ እንዳጣች ድንግል1፥8 ወይም ወጣት ሴት

ማቅ ለብሳችሁ አልቅሱ።

9የእህል ቍርባንና የመጠጥ ቍርባን፣

ከእግዚአብሔር ቤት ተቋርጧል፤

በእግዚአብሔርም ፊት የሚያገለግሉ፣

ካህናት ያለቅሳሉ።

10ዕርሻዎች ባዷቸውን ቀርተዋል፤

ምድሩም ደርቋል1፥10 ወይም መሬቱ ያዝናል

እህሉ ጠፍቷል፤

አዲሱ የወይን ጠጅ ዐልቋል፤

ዘይቱም ተሟጧል።

11እናንት ገበሬዎች፣ ዕዘኑ፤

እናንት የወይን ገበሬዎች፣ ዋይ በሉ፤

ስለ ገብሱና ስለ ስንዴው አልቅሱ፤

የዕርሻው መከር ጠፍቷልና።

12ወይኑ ደርቋል፤

የበለስ ዛፉም ጠውልጓል፤

ሮማኑ፣ ተምሩና እንኮዩ፣

የዕርሻው ዛፎች ሁሉ ደርቀዋል፤

ስለዚህ ደስታ፣

ከሰው ልጆች ርቋል።

የንስሓ ጥሪ

13ካህናት ሆይ፤ ማቅ ለብሳችሁ አልቅሱ፤

እናንተ በመሠዊያው ፊት የምታገለግሉ፣ ዋይ በሉ፤

እናንት በአምላኬ ፊት የምታገለግሉ፣

ኑ፤ ማቅ ለብሳችሁ ዕደሩ፤

የእህል ቍርባኑና የመጠጥ ቍርባኑ፣

ከአምላካችሁ ቤት ተቋርጧልና።

14ቅዱስ ጾምን ዐውጁ፤

የተቀደሰንም ጉባኤ ጥሩ፤

ሽማግሌዎችን ሰብስቡ፤

በምድሪቱ የሚኖሩትን ሁሉ፣

ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ጥሩ፤

ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ።

15ወዮ ለዚያ ቀን፤

የእግዚአብሔር ቀን ቀርቧልና፤

ሁሉን ከሚችል1፥15 ዕብራይስጡ ሻደይ ይለዋል። አምላክ እንደ ጥፋት ይመጣል።

16የሚበላ ምግብ፣

ከዐይናችን ፊት፣

ደስታና ተድላ፣

ከአምላካችን ቤት አልተቋረጠብንምን?

17ዘሩ በዐፈር ውስጥ1፥17 ለዚህ የገባው የዕብራይስጡ ቃል ትርጕም አይታወቅም።

በስብሶ ቀርቷል፤

ግምጃ ቤቶቹ ፈራርሰዋል፤

ጐተራዎቹም ተሰባብረዋል፤

እህሉ ደርቋልና።

18መንጎች እንደ ምን ጮኹ፣

ከብቶቹ ተደናግጠዋል፤

መሰማሪያ የላቸውምና፤

የበግ መንጎች እንኳ ተቸግረዋል።

19አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ፤ ወደ አንተ እጣራለሁ፤

ያልተነካውን መሰማሪያ እሳት በልቶታልና፤

የዱሩን ዛፍ ሁሉ ነበልባል አቃጥሎታል።

20የዱር አራዊት እንኳ ወደ አንተ አለኸለኹ፤

ወራጁ ውሃ ደርቋል፤

ያልተነካውንም መሰማሪያ እሳት በልቶታል።

Het Boek

Joël 1:1-20

Sprinkhanen over het land

1Joël, de zoon van Pethuël, ontving deze boodschap van de Here: 2Luister, leiders van mijn volk! Ja, laat iedereen luisteren! Hebt u ooit in uw leven of voor zover u zich uit de geschiedenis kunt herinneren, gehoord van wat Ik u nu ga vertellen? 3Vertel het in de toekomst aan uw kinderen. Geef dit vreselijke verhaal door van generatie op generatie.

4Nadat de knaagsprinkhanen uw gewassen hebben opgegeten, zullen de gewone sprinkhanen komen om de rest kaal te vreten. En na hen zullen de roofsprinkhanen komen! En daarna ook nog de veldsprinkhanen!

5Word wakker, dronkaards, want alle druiven zijn opgevreten en uw wijn is van u weggenomen. 6Een reusachtige zwerm sprinkhanen is neergestreken op het land. Het is een machtig, ontelbaar leger, met tanden zo scherp als die van een leeuw. 7Het heeft mijn wijnstok vernield en de schors van mijn vijgenboom afgestroopt. Alleen de stam en zijn naakte, witte ranken zijn nog over.

8Huil bittere tranen en trek rouwkleren aan als een bruid bij de dood van haar bruidegom. 9Wég zijn alle graanoffers en sprenkeloffers die voor de tempel van de Here waren bestemd. De priesters komen om van de honger. Luister maar naar het hulpgeroep van deze dienaren van de Here. 10De velden zijn verwoest. De aarde treurt, want al het koren is verdwenen, de jonge wijn opgedroogd en de voorraad olijfolie sterk geslonken. 11Die het land bewerken, mogen zich inderdaad verslagen voelen. Want de tarwe en de gerst, ja, de hele oogst is verloren gegaan. De wijnbouwers mogen gerust hun tranen laten vloeien. 12De wijnstokken zijn verdord, de vijgebomen stervend. De granaatappelbomen en palmen verdrogen en de appels verschrompelen aan de boom. Alle vreugde is met hen verdord.

13Priesters, trek uw rouwkleding aan. Dienaren van mijn God, ga de hele nacht huilend voor het altaar op de grond liggen. Want er zijn geen graanoffers en geen sprenkeloffers meer voor u overgebleven. 14Roep een heilige vastentijd uit. Houd een plechtige bijeenkomst. Verzamel de leiders en de hele bevolking in de tempel van de Here, uw God, en roep Hem aan.

15Pas op, die vreselijke dag van de Here komt dichterbij. De Almachtige stuurt bijna zijn verwoesting. 16Ons voedsel zal voor onze ogen verdwijnen. Alle vertoon van blijdschap en vreugde in de tempel van God zal tot het verleden behoren. 17Het zaad ligt in de grond te verschrompelen, de voorraadschuren en graanopslagplaatsen zijn leeg en het koren op het veld is verdroogd. 18Hoor het vee eens jammeren van de honger! Kudden runderen dwalen rond, maar vinden nergens een weide. Zelfs de schapen hebben zwaar te lijden. 19Here, help ons! Door de verzengende hitte zijn alle weiden vergeeld en alle bomen verschroeid. 20Zelfs de wilde dieren roepen tot U om hulp, want de beken liggen droog en alle weiden zijn verbrand.