ኢሳይያስ 9 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 9:1-21

ሕፃን ተወለደልን

1ነገር ግን ተጨንቀው የነበሩ ከእንግዲህ ተስፋ ቢስ አይሆኑም። በቀደመው ዘመን የዛብሎንንና የንፍታሌምን ምድር አዋረደ፤ በሚመጣው ዘመን ግን ከዮርዳኖስ ማዶ፣ በባሕር መንገድ አጠገብ ያለውን የአሕዛብን ገሊላ ያከብራል፤

2በጨለማ የሚኖር ሕዝብ

ታላቅ ብርሃን አየ፤

በሞት ጥላ9፥2 ወይም፣ በጨለማ ምድር። ምድር ለኖሩትም

ብርሃን ወጣላቸው።

3ሕዝብን አበዛህ፤

ደስታቸውንም ጨመርህ፤

ሰዎች ምርትን ሲሰበስቡ፣

ምርኮንም ሲከፋፈሉ

ደስ እንደሚላቸው ሁሉ፣

እነርሱም በፊትህ ደስ ይላቸዋል።

4ምድያም ድል በተመታ ጊዜ እንደ ሆነው፣

የከበዳቸውን ቀንበር፣

በትከሻቸው ላይ የነበረውን በትር፣

የተጨቈኑበትንም ዘንግ ሰብረህላቸዋል።

5የጦረኞች ጫማ ሁሉ፣

በደም የተለወሰ ልብስም ሁሉ፣

ለእሳት ይዳረጋል፤

ይማገዳልም።

6ሕፃን ተወልዶልናል፤

ወንድ ልጅም ተሰጥቶናል፤

አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል።

ስሙም፣ ድንቅ መካር፣9፥6 ወይም፣ ድንቅ፣ መካር።

ኀያል አምላክ፣

የዘላለም አባት፣ የሰላም ልዑል ይባላል።

7ለመንግሥቱ ስፋት፣

ለሰላሙም ብዛት ፍጻሜ የለውም፤

ከአሁን ጀምሮ እስከ ዘላለም፣

መንግሥቱን በፍትሕና በጽድቅ ይመሠርታል፤

ደግፎ በመያዝም ያጸናዋል።

በዳዊት ዙፋን ይቀመጣል፤

አገሩንም ሁሉ ይገዛል፤

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ቅናት

ይህን ያደርጋል።

የእግዚአብሔር ቍጣ በእስራኤል ላይ

8ጌታ በያዕቆብ ላይ ቃል ላከ፤

በእስራኤልም ላይ ይወድቃል።

9ሕዝቡ በሙሉ፣

ኤፍሬምና የሰማርያ ነዋሪዎች

ይህን ያውቃሉ፤

በትዕቢትና በልብ እብሪትም እንዲህ ይላሉ፤

10“ጡቦቹ ወድቀዋል፤

እኛ ግን በጥርብ ድንጋይ መልሰን እንገነባለን፤

የሾላ ዛፎቹ ተቈርጠዋል፤

እኛ ግን በዝግባ እንተካለን።”

11ነገር ግን እግዚአብሔር የረአሶንን ጠላቶች ያጠናክራል፤

በእነርሱም ላይ ያመጣባቸዋል፤

ባለጋራዎቻቸውንም ያነሣሣባቸዋል።

12ሶርያውያን ከምሥራቅ፣ ፍልስጥኤማውያን ከምዕራብ፤

አፋቸውን ከፍተው እስራኤልን ይቦጫጭቋታል።

ይህም ሁሉ ሆኖ፣ ቍጣው ገና አልበረደም፤

እጁ እንደ ተዘረጋ ነው።

13ሕዝቡ ግን ወደ ቀጣቸው ፊታቸውን አልመለሱም፤

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርንም አልፈለጉም።

14ስለዚህ እግዚአብሔር ራስንና ጅራትን፣

የዘንባባውን ቅርንጫፍና ሸንበቆውን ከእስራኤል በአንድ ቀን ይቈርጣል።

15ሽማግሌዎችና የተከበሩ ሰዎች ራስ፣

ሐሰትን የሚያስተምሩ ነቢያት ደግሞ ጅራት ናቸው።

16ይህን ሕዝብ የሚመሩት ያስቱታል፤

የሚመራውም ሕዝብ ከመንገድ ወጥቶ ይባዝናል።

17ስለዚህ ጌታ በጐበዛዝት ደስ አይሰኝም፤

አባት ለሌላቸውና ለመበለቶች አይራራም፤ ሁሉም ፈሪሀ እግዚአብሔር ያላደረበትና ክፉ አድራጊ ነው፤

የሁሉ አፍ አስጸያፊ ቃል ይናገራልና።

ይህም ሁሉ ሆኖ፣ ቍጣው ገና አልበረደም፤

እጁም እንደ ተዘረጋ ነው።

18እንግዲህ ርኩሰት እንደ እሳት ይቀጣጠላል፤

እሾኽንና ኵርንችትን ይበላል፤

ጥቅጥቅ ያለውን ደን ያነድዳል፤

ጢሱም ተትጐልጕሎ እንደ ዐምድ ይቆማል።

19በሰራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ቍጣ ምድር ትጋያለች፤

ሕዝቡም እሳት ውስጥ እንደሚጨመር

ማገዶ ይሆናል፤

ወንድሙንም ማዳን የሚችል ማንም የለም።

20በቀኝ በኩል ይጐርሳሉ፤

ነገር ግን ራባቸው አይታገሥም፤

በግራም በኩል ይበላሉ፤

ነገር ግን አይጠግቡም፤

እያንዳንዱም የገዛ ወገኑን9፥20 ወይም፣ ክንዱን ሥጋ ይበላል።

21ምናሴ ኤፍሬምን፣ ኤፍሬም ምናሴን ይበላል፤

በይሁዳም ላይ በአንድነት ይነሣሉ፤

ይህም ሁሉ ሆኖ፣ ቍጣው ገና አልበረደም፤

እጁም እንደ ተዘረጋ ነው።

Ketab El Hayat

إشعياء 9:1-21

يولد لنا ولد

1وَلَكِنْ لَنْ يُخَيِّمَ ظَلامٌ عَلَى الَّتِي تُعَانِي مِنَ الضِّيقِ، فَكَمَا أَذَلَّ اللهُ فِي الزَّمَنِ الْغَابِرِ أَرْضَ زَبُولُونَ وَنَفْتَالِي، فَإِنَّهُ فِي الزَّمَنِ الأَخِيرِ يُكْرِمُ طَرِيقَ الْبَحْرِ وَعَبْرَ الأُرْدُنِّ، جَلِيلَ الأُمَمِ. 2الشَّعْبُ السَّالِكُ فِي الظُّلْمَةِ أَبْصَرَ نُوراً عَظِيماً، وَالْمُقِيمُونَ فِي أَرْضِ ظِلالِ الْمَوْتِ أَضَاءَ عَلَيْهِمْ نُورٌ. 3كَثَّرْتَ الأُمَّةَ وَزِدْتَهَا فَرَحاً، ابْتَهَجُوا فِي حَضْرَتِكَ كَمَا يَبْتَهِجُونَ فِي أَوَانِ الْحَصَادِ وَكَمَا يَبْتَهِجُ الَّذِينَ يَتَقَاسَمُونَ الْغَنَائِمَ. 4لأَنَّكَ قَدْ حَطَّمْتَ، كَمَا فِي يَوْمِ مِدْيَانَ، نِيرَ ثِقْلِهِ وَعَصَا كَتِفِهِ وَقَضِيبَ مُسَخِّرِهِ. 5إِذْ كُلُّ سِلاحِ الْمُتَسَلِّحِ فِي الْوَغَى، وَكُلُّ رِدَاءٍ مُلَطَّخٍ بِالدِّمَاءِ، يُطْرَحُ وَقُوداً لِلنَّارِ وَيُحْرَقُ. 6لأَنَّهُ يُوْلَدُ لَنَا وَلَدٌ وَيُعْطَى لَنَا ابْنٌ يَحْمِلُ الرِّيَاسَةَ عَلَى كَتِفِهِ، وَيُدْعَى اسْمُهُ عَجِيباً، مُشِيراً، إِلَهاً قَدِيراً، أَباً أَبَدِيًّا، رَئِيسَ السَّلامِ. 7وَلا تَكُونُ نِهَايَةٌ لِنُمُوِّ رِيَاسَتِهِ وَلِلسَّلامِ اللَّذَيْنِ يَسُودَانِ عَرْشَ دَاوُدَ وَمَمْلَكَتَهُ، لِيُثَبِّتَهَا وَيَعْضُدَهَا بِالْحَقِّ وَالْبِرِّ، مِنَ الآنَ وَإِلَى الأَبَدِ. إِنَّ غَيْرَةَ الرَّبِّ الْقَدِيرِ تُتَمِّمُ هَذَا.

غضب الرب على إسرائيل

8لَقَدْ أَصْدَرَ الرَّبُّ قَضَاءَهُ عَلَى يَعْقُوبَ فَوَقَعَ فِي إِسْرَائِيلَ، 9فَيَعْلَمُ الشَّعْبُ كُلُّهُ: أَفْرَايِمُ وَسُكَّانُ السَّامِرَةِ الْقَائِلُونَ بِزَهْوٍ وَكِبْرِيَاءِ قَلْبٍ: 10«قَدْ تَسَاقَطَ اللِّبْنُ وَلَكِنَّنَا سَنَبْنِي بِحِجَارَةٍ مَنْحُوتَةٍ. قَدْ قُطِعَ الْجُمَّيْزُ وَلَكِنَّنَا نَسْتَبْدِلُهُ بِخَشَبِ الأَرْزِ!» 11ولَكِنَّ الرَّبَّ يُثِيرُ عَلَيْهِمْ خُصُومَهُمْ وَيُثِيرُ عَلَيْهِمْ أَعْدَاءَهُمْ، 12فَيَنْقَضُّ الأَرَامِيُّونَ مِنَ الشَّرْقِ، وَالْفِلِسْطِينِيُّونَ مِنَ الْغَرْبِ لِيَلْتَهِمُوا إِسْرَائِيلَ بِمِلْءِ الْفَمِ، وَمَعَ كُلِّ هَذَا فَإِنَّ غَضَبَهُ لَمْ يَرْتَدَّ، وَيَدَهُ مَا بَرِحَتْ مَمْدُودَةً لِلْعِقَابِ.

13إِنَّ الشَّعْبَ لَمْ يَرْجِعْ تَائِباً إِلَى مَنْ عَاقَبَهُ، وَلا طَلَبَ الرَّبَّ الْقَدِيرَ. 14لِذَلِكَ سَيَقْطَعُ الرَّبُّ مِنْ إِسْرَائِيلَ فِي يَوْمٍ وَاحِدٍ الرَّأْسَ وَالذَّنَبَ، النَّخْلَةَ وَالْقَصَبَةَ. 15إِنَّ الشَّيْخَ وَالْوَجِيهَ هُوَ الرَّأْسُ، وَالنَّبِيَّ الَّذِي يُلَقِّنُ الْكَذِبَ هُوَ الذَّنَبُ 16فَمُرْشِدُو هَذَا الشَّعْبِ يُضِلُّونَهُ، وَالْمُرْشَدُونَ يُبْتَلَعُونَ. 17لِذَلِكَ لَا يُسَرُّ الرَّبُّ بِشُبَّانِهِمْ، وَلا يَتَرَأَّفُ عَلَى أَيْتَامِهِمْ وَأَرَامِلِهِمْ، لأَنَّ جَمِيعَهُمْ مُنَافِقُونَ وَفَاعِلُو شَرٍّ، كُلُّ فَمٍ يَنْطِقُ بِالْحَمَاقَةِ، وَمَعَ كُلِّ هَذَا فَإِنَّ غَضَبَهُ لَمْ يَرْتَدْ، وَمَا بَرِحَتْ يَدُهُ مَمْدُودَةً لِلْعِقَابِ.

18لأَنَّ الفُجُورَ يَحْرِقُ كَالنَّارِ فَتَلْتَهِمُ الشَّوْكَ وَالْحَسَكَ بَلْ تُشْعِلُ أَجَمَاتِ الغَابَةِ فَتَتَصَاعَدُ مِنْهَا سُحُبُ الدُّخَانِ. 19إِنَّ الأَرْضَ تَحْتَرِقُ بِغَضَبِ الرَّبِّ الْقَدِيرِ، وَالشَّعْبَ كَوَقُودٍ لِلنَّارِ. لَا يَرْحَمُ وَاحِدٌ أَخَاهُ. 20يَلْتَهِمُونَ ذَاتَ الْيَمِينِ وَلَكِنْ يَظَلُّونَ جِيَاعاً، وَيَفْتَرِسُونَ ذَاتَ الشِّمَالِ وَلا يَشْبَعُونَ. كُلُّ وَاحِدٍ مِنْهُمْ يَأْكُلُ لَحْمَ أَخِيهِ. 21مَنَسَّى ضِدَّ أَفْرَايِمَ، وَأَفْرَايِمُ ضِدَّ مَنَسَّى، وَلَكِنَّهُمَا يَتَّحِدَانِ ضِدَّ يَهُوذَا. مِنْ أَجْلِ ذَلِكَ كُلِّهِ لَمْ يَرْتَدَّ غَضَبُهُ، وَمَا بَرِحَتْ يَدُهُ مَمْدُودَةً لِلْعِقَابِ!