ኢሳይያስ 8 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 8:1-22

አሦር የእግዚአብሔር መሣሪያ

1እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ፤ “ትልቅ ሰሌዳ ወስደህ፣ ‘ማኸር-ሻላል-ሃሽ-ባዝ’8፥1 በዚህና በቍጥር 3 ላይ፣ ማኸር-ሻላል-ሃሽ-ባዝ ማለት፣ ምርኮ ፈጠነ፤ ብዝበዛ ቸኰለ ማለት ነው። ብለህ በተለመደው በሰው ፊደል ጻፍበት። 2እኔም፣ ካህኑን ኡሪያንንና የበራክዩን ልጅ ዘካርያስን ታማኝ ምስክሮቼ እንዲሆኑ እጠራቸዋለሁ።”

3እኔም ወደ ነቢዪቱ ሄድሁ፤ እርሷም ፀነሰች፤ ወንድ ልጅም ወለደች። እግዚአብሔርም፣ እንዲህ አለኝ፤ “ስሙን ማኸር-ሻላል-ሃሽ-ባዝ ብለህ ጥራው። 4ሕፃኑም፣ ‘አባባ’ ወይም ‘እማማ’ ብሎ መጥራት ከመቻሉ በፊት፣ የደማስቆ ሀብትና የሰማርያ ምርኮ በአሦር ንጉሥ ይወሰዳል።”

5እግዚአብሔርም እንደ ገና እንዲህ ሲል ተናገረኝ፤

6“ይህ ሕዝብ በጸጥታ የሚፈስሰውን

የሰሊሆምን ውሆች ትቶ፣

በረአሶንና

በሮሜልዩ ልጅ ተደስቷልና።

7ስለዚህ ጌታ ታላቁንና ብርቱውን

የጐርፍ ውሃ8፥7 የኤፍራጥስ ወንዝ ነው።

የአሦርን ንጉሥ ከነግርማ ሞገሱ ሁሉ ያመጣባቸዋል።

ውሃውም ከቦዩ ዐልፎ ተርፎ

በወንዙ ዳር ያለውን ምድር ሁሉ ያጥለቀልቃል፤

8እየጠራረገ ወደ ይሁዳ ይወርዳል፤

እያጥለቀለቀ ያልፋል፤

እስከ ዐንገትም ይደርሳል፤

ዐማኑኤል8፥8 ዐማኑኤል ማለት፣ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው። ሆይ፤

የተዘረጉ ክንፎቹ ምድርህን ከዳር እስከ

ዳር ይሸፍናሉ።”

9እናንተ አሕዛብ፣ ፎክሩ8፥9 ወይም፣ የከፋውን ነገር አድርጉ፤ ነገር ግን ደንግጡ።

በሩቅ አገር ያላችሁ አድምጡ፤

ለጦርነትም ተዘጋጁ፤ ነገር ግን ደንግጡ፤

ለጦርነትም ተዘጋጁ፤ ነገር ግን ደንግጡ፤

10ተመካከሩ፤ ግን አይሳካም፤

ዕቅድ አውጡ፤ ሆኖም አይጸናም፤

እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነውና።8፥10 ዕብራይስጡ፣ ዐማኑኤል ይላል።

እግዚአብሔርን ፍሩ

11እግዚአብሔር ብርቱ እጁን በላዬ አድርጎ የእነዚህን ሰዎች መንገድ እንዳልከተል አስጠነቀቀኝ፤ እንዲህም አለኝ፤

12“እነዚህ ሰዎች፣ ‘አድማ’ ብለው የሚጠሩትን፣

ማንኛውንም ነገር፣ ‘አድማ’ አትበሉ፤8፥12 ወይም ለስምምነት አትጥሩ፤ እነዚህ ሰዎች ሁልጊዜ ለስምምነት ይጠራሉ

እነርሱ የሚፈሩትን አትፍሩ፤

አትሸበሩለትም።

13ልትቀድሱ የሚገባው የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርን ብቻ ነው፤

ልትፈሩት የሚገባው እርሱን ነው፤

ልትንቀጠቀጡለት የሚገባውም እርሱ ነው።

14እርሱም መቅደስ ይሆናል፤

ለሁለቱ የእስራኤል ቤት ግን

የሚያደናቅፍ ድንጋይ፣

የሚያሰናክልም ዐለት ይሆንባቸዋል፤

ለኢየሩሳሌም ሕዝብም

ወጥመድና አሽክላ ይሆናል።

15ከእነርሱ ብዙዎች ይሰናከላሉ፤

ይወድቃሉ፤ ይሰበራሉ፤

ወጥመድ ይገባሉ፤ ይያዛሉም።”

16ምስክርነቱን አሽገው፤

ሕጉንም በደቀ መዛሙርቴ መካከል አትመው።

17ፊቱን ከያዕቆብ ቤት የሸሸገውን

እግዚአብሔርን እጠብቃለሁ፤

እርሱንም ተስፋ አደርጋለሁ።

18እነሆ፤ እኔና እግዚአብሔር የሰጠኝ ልጆች በጽዮን ተራራ ከሚኖረው ከሰራዊት ጌታ ከእግዚአብሔር ለእስራኤል ምልክትና ድንቅ ነን።

19ሰዎች፣ የሚያነበንቡትንና የሚያንሾካሽኩትን ሟርተኞችንና መናፍስት ጠሪዎችን ጠይቁ ቢሏችሁ፣ ሕዝቡ አምላኩን መጠየቅ አይገባውምን? በሕያዋን ምትክ ሙታንን መጠየቅ ለምን አስፈለገ? 20ወደ ሕጉና ወደ ምስክር ቃሉ ሂዱ! እነርሱም እንዲህ ያለውን ቃል ባይናገሩ የንጋት ብርሃን አይበራላቸውም። 21ተጨንቀውና ተርበው በምድሪቱ ላይ ይንከራተታሉ፤ ክፉኛ ሲራቡም ይቈጣሉ፤ ወደ ላይ እየተመለከቱ ንጉሣቸውንና አምላካቸውን ይራገማሉ። 22ከዚያም ወደ ምድር ይመለከታሉ፣ የሚያዩትም ጭንቀት፣ ጨለማና የሚያስፈራም ጭጋግ ብቻ ነው፤ ወደ ድቅድቅ ጨለማም ይጣላሉ።

Japanese Contemporary Bible

イザヤ書 8:1-22

8

しるしとしてのイザヤとイザヤの息子

1神はまた、私に命じました。

「大きな看板を作り、やがて授かる子どもの名を、だれもが読めるように書きなさい。名前はマヘル・シャラル・ハシュ・バズ。『敵はまもなく滅びる』という意味だ。」 2私は祭司ウリヤとエベレクヤの子ゼカリヤに頼んで、証人になってもらいました。まだ子どもの生まれないうちに、確かに私がこのことを書いた、と証言してもらうためです。 3やがて妻はみごもり、男の子を産みました。その時、主の声が響いてきました。「この子をマヘル・シャラル・ハシュ・バズと呼べ。 4この名は、この子が『お父さん』『お母さん』と言うようになるまでの数年のうちに、アッシリヤ王がダマスコ(シリヤ)とサマリヤ(イスラエル)を侵略し、金銀財宝を奪い去ることを予告している。」

5主はさらに続けました。

6「エルサレムの住民は、

わたしが親身に世話をしたのに見向きもせず、

レツィン王とペカ王が、

助けに来てくれないかと、やっきになっている。

7-8だからわたしは彼らの上に、

ユーフラテス川の大洪水をもたらそう。

アッシリヤ王が大軍を率いて彼らに襲いかかる。

ああ、インマヌエル。

この洪水は、おまえたちユダ王国に堰を切ったように

流れ込み、端から端まで水浸しにする。」

9-10シリヤもイスラエルもほかの国々も、

悪の限りを尽くしてみるがよい。

だが、そんな計画が成功するはずはない。

必ず計画倒れになる。

さあ敵どもよ、私の言うことを聞け。

私たちに戦争をしかけてみよ。そして滅ぶがいい。

参謀を呼び集め、緻密な作戦を立て、

抜かりなく攻撃準備を整えよ。

そして滅ぶがいい。私たちには神がついている。

11主はきびしく命じました。

「どんなことがあっても、

シリヤとイスラエルに降伏しようという計画に乗るな。

12神に忠実であることで同胞から

裏切り者呼ばわりされるのを恐れるな。

人々はシリヤとイスラエルが攻めて来るというので

恐れているが、あなたはあわてふためいてはならない。

13天の軍勢の主のほかは、だれをも恐れてはならない。

わたしだけを恐れていれば、

誰ひとりとして怖くないはずだ。

14-15おまえの安全は、わたしが保証する。

ところがイスラエルとユダは、

わたしの守りを拒んだために、

救いの岩につまずき、倒れて下敷きになった。

わたしが彼らとともにいたことが

かえって彼らに危害を及ぼすことになった。

16これからわたしのしようとしていることを

残らず書き留め、将来のために封をしておけ。

神を敬う者に託して、

のちの時代の神を敬う者らに渡してもらうのだ。」

17主は今姿を隠していますが、

私は主の助けを信じて、ひたすら待ち望みます。

主だけが私の希望です。

18私の名も、神が授けてくれた子どもたちの名も、

みな天の軍勢の主の計画を暗示しています。

イザヤというのは「神はご自分の民を救う」、

シェアル・ヤシュブは「残りの民が帰って来る」、

マヘル・シャラル・ハシュ・バズは

「敵はまもなく滅びる」という意味です。

暗闇が光となる

19だというのに、なぜあなたがたは魔術師や霊媒師などに相談し、将来どんなことが起こるかを知ろうとするのですか。彼らのささやきや呪文を聞いてはなりません。そもそも生きている者が、死んだ人間から将来のことを聞き出せるものでしょうか。知りたかったら、どうして神に直接尋ねないのですか。

20神はこのように語ります。「魔術師どものことばを、神のことばと比較してみよ。彼らの言うことは、わたしの言うことと違うが、それは彼らがわたしの使者ではないからだ。彼らには真理の光などない。 21わたしの民は捕虜となり、飢えて弱り果て、つまずきよろけながら連れ去られる。空腹のあまりうわ言をいい、天に向かってこぶしを振り、王と神をのろう。 22どこを見ても、目につくものは苦しみと悩みと暗たんとした絶望だけだ。こうして彼らは暗闇の中に追いやられる。」