ኢሳይያስ 63 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 63:1-19

እግዚአብሔር የሚቤዥበትና የሚበቀልበት ቀን

1ይህ ከኤዶም፣

ቀይ የተነከረ መጐናጸፊያ ለብሶ ከባሶራ የሚመጣ ማን ነው?

ይህ ክብርን የተጐናጸፈ፣

በኀይሉ ታላቅነት እየተራመደ የሚመጣውስ ማን ነው?

“በጽድቅ የምናገር፣

ለማዳንም ኀይል ያለኝ እኔው ነኝ።”

2መጐናጸፊያህ፣ ለምን በወይን መጭመቂያ፣

ወይን እንደሚረግጡ ሰዎች ልብስ ቀላ?

3“እኔ በመጭመቂያው ወይኑን ብቻዬን ረገጥሁ፤

ከመንግሥታት ማንም ከእኔ ጋር አልነበረም፤

በቍጣዬ ረገጥኋቸው፤

በመዓቴም ጨፈለቅኋቸው፤

ደማቸው በመጐናጸፊያዬ ላይ ተረጭቷል፤

ልብሴንም በክዬዋለሁ።

4የበቀል ቀን በልቤ አለ፤

የምቤዥበትም ዓመት ደርሷል።

5ተመለከትሁ፤ የሚረዳ ግን አልነበረም፤

የሚያግዝ ባለመኖሩም ተገረምሁ፤

ስለዚህ የገዛ ክንዴ ድነትን አመጣልኝ፤

የገዛ ቍጣዬም አጸናኝ፤

6መንግሥታትን በቍጣዬ ረጋገጥሁ፤

በመዓቴም አሰከርኋቸው፤

ደማቸውንም በምድር ላይ አፈሰስሁ።”

ውዳሴና ጸሎት

7የእግዚአብሔርን ቸርነት፣

እግዚአብሔር ስላደረገልን ሁሉ፣

ስለሚመሰገንበት ሥራው፣

እንደ ፍቅሩና እንደ ቸርነቱ መጠን፣

ለእስራኤል ቤት ያደረገውን፣

አዎን፣ ስላደረገው መልካም ነገር እናገራለሁ።

8እርሱም፣ “ርግጥ ነው፤ እነርሱ ሕዝቤ ናቸው፤

የማይዋሹኝ ወንዶች ልጆቼ ናቸው” አለ።

ስለዚህም አዳኝ ሆነላቸው።

9በጭንቃቸው ሁሉ ተጨነቀ፤

የፊቱም መልአክ አዳናቸው፤

በፍቅሩና በምሕረቱ ዋጃቸው፤

በቀደመው ዘመን ሁሉ አነሣቸው፤

ተሸከማቸውም።

10እነርሱ ግን ዐመፁ፤

ቅዱስ መንፈሱንም አሳዘኑ፤

ስለዚህ ተመልሶ ጠላት ሆናቸው፤

እርሱ ራሱ ተዋጋቸው።

11ከዚያም ሕዝቡ የጥንቱን ዘመን፣

የሙሴንና የሕዝቡን ጊዜ እንዲህ በማለት አስታወሱ፤

የበጎቹን እረኛ፣

ከባሕሩ ያወጣቸው እርሱ የት አለ?

ቅዱስ መንፈሱንም፣

በመካከላቸው ያኖረ እርሱ የት አለ?

12የከበረው ኀያል ክንድ፣

በሙሴ ቀኝ እጅ ላይ እንዲያርፍ አደረገ፤

ለራሱ የዘላለም ዝና እንዲሆንለት፣

ውሆችን በፊታቸው ከፈለ።

13ፈረስ በምድረ በዳ እንደሚያልፍ ሁሉ፣

እነርሱንም በጥልቁ ውስጥ አሳልፎ መራቸው፤

ስለዚህም አልተሰናከሉም፤

14ወደ ሸለቆ እንደሚወርድ የከብት መንጋ፣

በእግዚአብሔር መንፈስ ዕረፍት ተሰጣቸው።

ሕዝብህን በዚህ ሁኔታ የመራሃቸው፣

ስምህን የከበረ ለማድረግ ነው።

15ከተቀደሰው፣ ከተከበረውና ከፍ ካለው ዙፋንህ፣

ከሰማይ ወደ ታች ተመልከት፤

ኀይልህና ቅናትህ የት አለ?

ገርነትህና ርኅራኄህ ከእኛ ርቀዋል።

16አብርሃም ባያውቀን፣

እስራኤልም ባያስታውሰን እንኳ፣

አንተ እኮ አባታችን ነህ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ አባታችን ነህ፤

ከጥንትም ቢሆን ስምህ “ቤዛችን” ነው።

17እግዚአብሔር ሆይ፤ ከመንገድህ እንድንወጣ፣

ልባችንን በማደንደን ለምን እንዳንፈራህ አደረግኸን?

ስለ ባሮችህ ስትል፣

ስለ ርስትህ ነገዶች ስትል እባክህ ተመለስ።

18ለጥቂት ጊዜ ሕዝብህ የተቀደሰውን ስፍራ ወርሶ ነበር፤

አሁን ግን ጠላቶቻችን መቅደስህን ረገጡት።

19እኛ እኮ ጥንትም የአንተው ነን፤

እነርሱን ግን አንተ አላገዝሃቸውም፤

በስምህም አልተጠሩም።63፥19 ወይም፣ አንተ እንዳልገዛሃቸው እንመስላለን፣ ልክ በአንተ ስም እንዳልተጠሩት

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以赛亚书 63:1-19

主报应列国

1这位身披红衣、

穿着华丽、充满力量、

以东波斯拉阔步而来的是谁呢?

“是宣告公义、

有拯救大能的我。”

2你的衣服为何是红色的,

好像榨酒池中踩踏葡萄者的衣服?

3“我独自在榨酒池踩踏,

万民中无人跟我在一起。

我在愤怒中踩踏他们,

在烈怒中践踏他们;

他们的血溅到我的衣服上,

染红了我的衣服。

4我心中定了报仇的日子,

我救赎我子民之年已经来临。

5我环顾四周,惊讶地看见无人帮助,无人扶持。

于是,在烈怒的推动下,

我用臂膀独自拯救。

6我在愤怒中践踏万民,

让他们饱尝我的烈怒,

把他们的血倒在地上。”

颂赞与祷告

7因耶和华为我们所做的一切,

我要述说祂的慈爱和祂可歌可颂的作为,

述说祂本着怜悯和大爱赐给以色列人的厚恩。

8祂说:“他们的确是我的子民,

不会背叛我。”

因此,祂做他们的救主。

9祂苦他们所苦,

亲自63:9 亲自”希伯来文是“祂面前的天使”。拯救他们。

祂本着慈爱和怜悯救赎了他们,

自古以来一直扶持、照顾他们。

10他们却叛逆,使祂的圣灵忧伤。

于是,祂与他们为敌,

亲自攻击他们。

11后来,他们想起古时候,

想起了摩西和他的百姓,便问,

带领百姓及其牧者摩西从海里出来的那位在哪里?

将自己的圣灵降在他们中间的那位在哪里?

12用荣耀的臂膀扶持摩西

在他们面前把海水分开,

使自己威名永存的那位在哪里?

13带领他们经过大海,

犹如马行平川不会失脚的那位在哪里?

14耶和华的灵使他们得到安歇,

犹如牲畜下到山谷。

耶和华啊,你就是这样引领你的子民,

以树立自己荣耀的名。

15求你从天上垂顾,

从你圣洁、荣耀的居所垂看。

你的热忱和大能在哪里呢?

难道你不再眷爱、怜悯我们吗?

16虽然亚伯拉罕不认识我们,

以色列不承认我们,

但你是我们的父亲。

耶和华啊,你是我们的父亲,

你自古以来就是我们的救赎主。

17耶和华啊!你为何使我们偏离你的路,

使我们硬着心不敬畏你呢?

求你为了你的仆人,

你的产业——以色列各支派而改变心意!

18你的圣民曾短暂地拥有你的圣所,

如今它已被我们的敌人踏平。

19我们如此沦落,

好像从未被你治理过,

从来不属于你。