ኢሳይያስ 62 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 62:1-12

አዲሱ የጽዮን ስም

1ጽድቋ እንደ ማለዳ ወጋገን እስኪፈነጥቅ፣

ድነቷ እንደሚያንጸባርቅ ፋና እስኪታይ፣

ስለ ጽዮን ዝም አልልም፤

ስለ ኢየሩሳሌምም ጸጥ አልልም።

2መንግሥታት ጽድቅሽን፣

ነገሥታት ክብርሽን ያያሉ፤

የእግዚአብሔር አፍ በሚያወጣልሽ፣

በአዲስ ስም ትጠሪያለሽ።

3በእግዚአብሔር እጅ የክብር አክሊል፣

በአምላክሽም እጅ የመንግሥት ዘውድ ትሆኛለሽ።

4ከእንግዲህ፣ “የተተወች” ብለው አይጠሩሽም፤

ምድርሽም፣ “የተፈታች” አትባልም፤

ነገር ግን፣ “ደስታዬ በእርሷ” ትባያለሽ፤

ምድርሽም፣ “ባለ ባል” ትባላለች፤

እግዚአብሔር በአንቺ ደስ ይለዋል፤

ምድርሽም ባለ ባል ትሆናለች።

5ጕልማሳ ድንግሊቱን እንደሚያገባ፣

ልጆችሽ62፥5 ወይም፣ ግንበኞችሽ እንዲሁ ያገቡሻል፤

ሙሽራ በሙሽራዪቱ ደስ እንደሚለው፣

አምላክሽም በአንቺ ደስ ይለዋል።

6ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ዘብ ጠባቂዎችን በቅጥሮችሽ ላይ አቁሜአለሁ፤

ቀንም ሆነ ሌሊት ፈጽሞ አይታክቱም።

እናንት ወደ እግዚአብሔር አቤት፣ አቤት የምትሉ፤

ፈጽሞ አትረፉ፤

7ኢየሩሳሌምን እስኪያጸናት፣

የምድርም ምስጋና እስኪያደርጋት ዕረፍት አትስጡት።

8እግዚአብሔር በቀኝ እጁ፣

በኀያል ክንዱም እንዲህ ሲል ምሏል፤

“ከእንግዲህ እህልሽን፣

ለጠላቶችሽ መብል እንዲሆን አልሰጥም፤

ከእንግዲህ የደከምሽበትን፣

አዲስ የወይን ጠጅ ባዕዳን አይጠጡትም።

9ነገር ግን መከሩን የሰበሰቡ ይበሉታል፤

እግዚአብሔርንም ያመሰግናሉ፤

የወይኑን ፍሬ የለቀሙም በመቅደሴ

አደባባዮች ይጠጡታል።”

10ዕለፉ፤ በበሮቹ በኩል ዕለፉ፤

ለሕዝቡ መንገድ አዘጋጁ፤

አስተካክሉ፤ ጐዳናውን አስተካክሉ፤

ድንጋዩን አስወግዱ፤

ለመንግሥታትም ምልክት አሳዩ።

11እግዚአብሔር እስከ ምድር ዳርቻ፣

እንዲህ ሲል ዐውጇል፤

“ለጽዮን ሴት ልጅ፣

‘እነሆ፤ አዳኝሽ መጥቷል፤

ዋጋሽ በእጁ አለ፤

ዕድል ፈንታሽም ከእርሱ ጋር ነው’ በሏት።”

12እነርሱም ቅዱስ ሕዝብ፣

እግዚአብሔር የተቤዣቸው ተብለው ይጠራሉ፤

አንቺም የምትፈለግ፣

ከእንግዲህም የማትተው ከተማ ትባያለሽ።

New International Version

Isaiah 62:1-12

Zion’s New Name

1For Zion’s sake I will not keep silent,

for Jerusalem’s sake I will not remain quiet,

till her vindication shines out like the dawn,

her salvation like a blazing torch.

2The nations will see your vindication,

and all kings your glory;

you will be called by a new name

that the mouth of the Lord will bestow.

3You will be a crown of splendor in the Lord’s hand,

a royal diadem in the hand of your God.

4No longer will they call you Deserted,

or name your land Desolate.

But you will be called Hephzibah,62:4 Hephzibah means my delight is in her.

and your land Beulah62:4 Beulah means married.;

for the Lord will take delight in you,

and your land will be married.

5As a young man marries a young woman,

so will your Builder marry you;

as a bridegroom rejoices over his bride,

so will your God rejoice over you.

6I have posted watchmen on your walls, Jerusalem;

they will never be silent day or night.

You who call on the Lord,

give yourselves no rest,

7and give him no rest till he establishes Jerusalem

and makes her the praise of the earth.

8The Lord has sworn by his right hand

and by his mighty arm:

“Never again will I give your grain

as food for your enemies,

and never again will foreigners drink the new wine

for which you have toiled;

9but those who harvest it will eat it

and praise the Lord,

and those who gather the grapes will drink it

in the courts of my sanctuary.”

10Pass through, pass through the gates!

Prepare the way for the people.

Build up, build up the highway!

Remove the stones.

Raise a banner for the nations.

11The Lord has made proclamation

to the ends of the earth:

“Say to Daughter Zion,

‘See, your Savior comes!

See, his reward is with him,

and his recompense accompanies him.’ ”

12They will be called the Holy People,

the Redeemed of the Lord;

and you will be called Sought After,

the City No Longer Deserted.