ኢሳይያስ 61 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 61:1-11

የተወደደው የእግዚአብሔር ዓመት

1የጌታ የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ላይ ነው፤

ለድኾች የምሥራች እንድሰብክ፣

እግዚአብሔር ቀብቶኛል።

ልባቸው የተሰበረውን እንድጠግን፣

ለምርኮኞች ነጻነትን፣

ለእስረኞች መፈታትን እንዳውጅ61፥1 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን፣ ዕውራንን ከጨለማ አወጣቸው ዘንድ ይላል። ልኮኛል፤

2የተወደደውን የእግዚአብሔርን ዓመት፣

የአምላካችንንም የበቀል ቀን እንዳውጅ፣

የሚያለቅሱትን ሁሉ እንዳጽናና ልኮኛል፤

3በጽዮን ያዘኑትን እንዳረጋጋ፣

በዐመድ ፈንታ፣

የውበት አክሊል እንድደፋላቸው፣

በልቅሶ ፈንታ፣

የደስታ ዘይት በራሳቸው ላይ እንዳፈስስላቸው፣

በትካዜ መንፈስ ፈንታ፣

የምስጋና መጐናጸፊያ እንድደርብላቸው ልኮኛል፤

እነርሱም የክብሩ መግለጫ እንዲሆኑ፣

እግዚአብሔር የተከላቸው፣

የጽድቅ ዛፎች ተብለው ይጠራሉ።

4የጥንት ፍርስራሾችን መልሰው ይሠራሉ፤

በቀድሞ ጊዜ የወደሙትን መልሰው ያቆማሉ፤

ከብዙ ትውልድ በፊት የወደሙትን

ፍርስራሽ ከተሞች እንደ ገና ይሠራሉ።

5መጻተኞች የበግ መንጎቻችሁን ያግዳሉ፤

ባዕዳን በዕርሻችሁና በወይን ተክል ቦታችሁ ላይ ይሠሩላችኋል።

6እናንተም የእግዚአብሔር ካህናት ተብላችሁ ትጠራላችሁ፤

የአምላካችን ባሮች ትባላላችሁ፤

የመንግሥታትን ሀብት ትመገባላችሁ፤

በብልጽግናቸውም ትኰራላችሁ።

7ሕዝቤ በኀፍረታቸው ፈንታ፣

ዕጥፍ ይቀበላሉ፤

በውርደታቸው ፈንታ፣

በርስታቸው ደስ ይላቸዋል፤

የምድራቸውንም ዕጥፍ ርስት ይወርሳሉ፤

ዘላለማዊ ደስታም የእነርሱ ይሆናል።

8“እኔ እግዚአብሔር ፍትሕን ስለምወድድ፣

ዝርፊያንና በደልን እጠላለሁ፤

በታማኝነቴም የሚገባቸውን እሰጣቸዋለሁ፤

ከእነርሱም ጋር የዘላለም ኪዳን አደርጋለሁ።

9ዘሮቻቸው በመንግሥታት፣

ልጆቻቸውም በሕዝቦች ዘንድ የታወቁ ይሆናሉ፤

የሚያዩአቸውም ሁሉ፣

እግዚአብሔር የባረካቸው ሕዝብ እንደ ሆኑ ያውቃሉ።”

10በእግዚአብሔር እጅግ ደስ ይለኛል፤

ነፍሴ በአምላኬ ሐሤት ታደርጋለች፤

ሙሽራ ራሱን እንደሚያሳምር፣

ሙሽራዪቱም በዕንቈቿ እንደምታጌጥ፣

የድነትን ልብስ አልብሶኛል፤

የጽድቅንም መጐናጸፊያ ደርቦልኛል።

11ምድር ቡቃያ እንደምታበቅል፣

የተክል ቦታ ችግኝ እንደሚያፈላ፣

ጌታ እግዚአብሔርም በመንግሥታት ሁሉ ፊት፣

ጽድቅንና ምስጋናን ያበቅላል።

New International Version – UK

Isaiah 61:1-11

The year of the Lord’s favour

1The Spirit of the Sovereign Lord is on me,

because the Lord has anointed me

to proclaim good news to the poor.

He has sent me to bind up the broken-hearted,

to proclaim freedom for the captives

and release from darkness for the prisoners,61:1 Hebrew; Septuagint the blind

2to proclaim the year of the Lord’s favour

and the day of vengeance of our God,

to comfort all who mourn,

3and provide for those who grieve in Zion –

to bestow on them a crown of beauty

instead of ashes,

the oil of joy

instead of mourning,

and a garment of praise

instead of a spirit of despair.

They will be called oaks of righteousness,

a planting of the Lord

for the display of his splendour.

4They will rebuild the ancient ruins

and restore the places long devastated;

they will renew the ruined cities

that have been devastated for generations.

5Strangers will shepherd your flocks;

foreigners will work your fields and vineyards.

6And you will be called priests of the Lord,

you will be named ministers of our God.

You will feed on the wealth of nations,

and in their riches you will boast.

7Instead of your shame

you will receive a double portion,

and instead of disgrace

you will rejoice in your inheritance.

And so you will inherit a double portion in your land,

and everlasting joy will be yours.

8‘For I, the Lord, love justice;

I hate robbery and wrongdoing.

In my faithfulness I will reward my people

and make an everlasting covenant with them.

9Their descendants will be known among the nations

and their offspring among the peoples.

All who see them will acknowledge

that they are a people the Lord has blessed.’

10I delight greatly in the Lord;

my soul rejoices in my God.

For he has clothed me with garments of salvation

and arrayed me in a robe of his righteousness,

as a bridegroom adorns his head like a priest,

and as a bride adorns herself with her jewels.

11For as the soil makes the young plant come up

and a garden causes seeds to grow,

so the Sovereign Lord will make righteousness

and praise spring up before all nations.