ኢሳይያስ 60 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 60:1-22

የጽዮን ክብር

1“ብርሃንሽ መጥቷልና ተነሺ አብሪ፤

የእግዚአብሔርም ክብር ወጥቶልሻል።

2እነሆ፤ ጨለማ ምድርን፣

ድቅድቅ ጨለማም ሕዝቦችን ይሸፍናል፤

ነገር ግን እግዚአብሔር ወጥቶልሻል፤

ክብሩንም ይገልጥልሻል።

3ሕዝቦች ወደ ብርሃንሽ፣

ነገሥታትም ወደ ንጋትሽ ጸዳል ይመጣሉ።

4“ቀና በዪ፤ ዙሪያሽን ተመልከቺ፤

ሁሉም ተሰብስበው ወደ አንቺ ይመጣሉ፤

ወንዶች ልጆችሽ ከሩቅ፣

ሴቶች ልጆችሽም በዕቅፍ ወደ አንቺ ይመጣሉ።

5ከዚያም ታያለሽ፤ ታብረቀርቂያለሽ፤

ልብሽ ይዘልላል፤ በደስታም ይሞላል።

በባሕሮች ያለው ሀብት ወደ አንቺ ይመጣል፤

የነገሥታትም ብልጽግና የአንቺ ይሆናል።

6የግመል መንጋ፣

የምድያምና የጌፌር ግልገል ግመሎች

ምድርሽን ይሞላሉ፤

ወርቅና ዕጣን ይዘው፣

የእግዚአብሔርን ምስጋና እያወጁ፣

ሁሉም ከሳባ ይመጣሉ።

7የቄዳር የበግ መንጋ ሁሉ ወደ አንቺ ይሰበሰባል፤

የነባዮት አውራ በጎች ያገለግሉሻል።

እነዚህም በመሠዊያዬ ላይ ተቀባይነት የሚኖራቸው መሥዋዕቶች ይሆናሉ፤

እኔም የክብር መቅደሴን ግርማ አጐናጽፈዋለሁ።

8“ርግቦች ወደ ጐጇቸው እንደሚበርሩ፣

እንደ ደመና የሚጓዙ እነዚህ እነማን ናቸው?

9በርግጥ ደሴቶች እኔን ተስፋ ያደርጋሉ፤

እርሱ ክብሩን ስላጐናጸፈሽ፣

ለእስራኤል ቅዱስ፣

ለእግዚአብሔር አምላክሽ ክብር፣

ከሩቅ ወንዶች ልጆችሽን፣

ከነብራቸውና ከነወርቃቸው ለማምጣት፣

የተርሴስ መርከቦች60፥9 ወይም፣ የንግድ መርከቦች ቀድመው ይወጣሉ።

10“ባዕዳን ቅጥሮችሽን ይሠራሉ፤

ነገሥታቶቻቸው ያገለግሉሻል፤

በቍጣዬ ብመታሽም፣

ርኅራኄዬን በፍቅር አሳይሻለሁ።

11በሮችሽ ምንጊዜም የተከፈቱ ይሆናሉ፤

ቀንም ሆነ ሌሊት ከቶ አይዘጉም፤

ይህም ሰዎች የመንግሥታትን ብልጽግና ወደ አንቺ እንዲያመጡ፣

ነገሥታታቸውም በድል ወደ አንቺ እንዲገቡ ነው።

12ለአንቺ የማይገዛ ሕዝብና መንግሥት ይጠፋል፤

ፈጽሞም ይደመሰሳል።

13“የመቅደሴን ቦታ ለማስጌጥ፣

የሊባኖስ ክብር፣

ጥዱ፣ አስታውና ባርሰነቱ በአንድነት ወደ አንቺ ይመጣሉ፤

እግሬ የሚያርፍበትንም ስፍራ አከብራለሁ።

14የአስጨናቂዎችሽ ወንዶች ልጆች እየሰገዱ ወደ አንቺ ይመጣሉ፤

የናቁሽም ሁሉ እግርሽ ላይ ይደፋሉ፤

የእግዚአብሔር ከተማ፣

የእስራኤል ቅዱስ ገንዘብ የሆንሽው ጽዮን ብለው ይጠሩሻል።

15“የተተውሽና የተጠላሽ፣

ማንም ሰው የማያልፍብሽ ብትሆኝም እንኳ፣

እኔ የዘላለም ትምክሕት፣

የትውልድም ሁሉ ደስታ አደርግሻለሁ።

16የመንግሥታትን ወተት ትጠጪያለሽ፤

የነገሥታትንም ጡት ትጠቢያለሽ፤

ከዚያም እኔ እግዚአብሔር አዳኝሽ፣

ቤዛሽም እኔ የያዕቆብ ኀያል እንደ ሆንሁ ታውቂያለሽ።

17በናስ ፈንታ ወርቅ፣

በብረትም ፈንታ ብር አመጣልሻለሁ።

ሰላምን ገዥሽ፣

ጽድቅንም አለቃሽ አደርጋለሁ።

18ከእንግዲህ በምድርሽ ሁከት፣

በጠረፎችሽም ጥፋትና መፈራረስ አይሰማም፤

ነገር ግን ቅጥሮችሽን ድነት፣

በሮችሽንም ምስጋና ብለሽ ትጠሪያቸዋለሽ።

19ከእንግዲህ በቀን የፀሓይ ብርሃን አያስፈልግሽም፤

በሌሊትም የጨረቃ ብርሃን አያበራልሽም፤

እግዚአብሔር የዘላለም ብርሃን፣

አምላክሽም ክብርሽ ይሆናልና።

20ፀሓይሽ ከእንግዲህ አትጠልቅም፤

ጨረቃሽም ብርሃን መስጠቷን አታቋርጥም፤

እግዚአብሔር የዘላለም ብርሃንሽ ይሆናል፤

የሐዘንሽም ቀን ያከትማል።

21ሕዝብሽም ሁሉ ጻድቃን ይሆናሉ፤

ምድሪቱንም ለዘላለም ይወርሳሉ፤

ለክብሬ መግለጫ ይሆኑ ዘንድ፣

የእጆቼ ሥራ፣

እኔ የተከልኋቸው ቍጥቋጦች ናቸው።

22ከአንቺ ታናሽ የሆነው ሺሕ፣

ከሁሉም የመጨረሻው ታናሽ ኀያል መንግሥት ይሆናል፤

እኔ እግዚአብሔር ነኝ፤

ጊዜውም ሲደርስ ይህን በፍጥነት አደርጋለሁ።”

New International Version

Isaiah 60:1-22

The Glory of Zion

1“Arise, shine, for your light has come,

and the glory of the Lord rises upon you.

2See, darkness covers the earth

and thick darkness is over the peoples,

but the Lord rises upon you

and his glory appears over you.

3Nations will come to your light,

and kings to the brightness of your dawn.

4“Lift up your eyes and look about you:

All assemble and come to you;

your sons come from afar,

and your daughters are carried on the hip.

5Then you will look and be radiant,

your heart will throb and swell with joy;

the wealth on the seas will be brought to you,

to you the riches of the nations will come.

6Herds of camels will cover your land,

young camels of Midian and Ephah.

And all from Sheba will come,

bearing gold and incense

and proclaiming the praise of the Lord.

7All Kedar’s flocks will be gathered to you,

the rams of Nebaioth will serve you;

they will be accepted as offerings on my altar,

and I will adorn my glorious temple.

8“Who are these that fly along like clouds,

like doves to their nests?

9Surely the islands look to me;

in the lead are the ships of Tarshish,60:9 Or the trading ships

bringing your children from afar,

with their silver and gold,

to the honor of the Lord your God,

the Holy One of Israel,

for he has endowed you with splendor.

10“Foreigners will rebuild your walls,

and their kings will serve you.

Though in anger I struck you,

in favor I will show you compassion.

11Your gates will always stand open,

they will never be shut, day or night,

so that people may bring you the wealth of the nations—

their kings led in triumphal procession.

12For the nation or kingdom that will not serve you will perish;

it will be utterly ruined.

13“The glory of Lebanon will come to you,

the juniper, the fir and the cypress together,

to adorn my sanctuary;

and I will glorify the place for my feet.

14The children of your oppressors will come bowing before you;

all who despise you will bow down at your feet

and will call you the City of the Lord,

Zion of the Holy One of Israel.

15“Although you have been forsaken and hated,

with no one traveling through,

I will make you the everlasting pride

and the joy of all generations.

16You will drink the milk of nations

and be nursed at royal breasts.

Then you will know that I, the Lord, am your Savior,

your Redeemer, the Mighty One of Jacob.

17Instead of bronze I will bring you gold,

and silver in place of iron.

Instead of wood I will bring you bronze,

and iron in place of stones.

I will make peace your governor

and well-being your ruler.

18No longer will violence be heard in your land,

nor ruin or destruction within your borders,

but you will call your walls Salvation

and your gates Praise.

19The sun will no more be your light by day,

nor will the brightness of the moon shine on you,

for the Lord will be your everlasting light,

and your God will be your glory.

20Your sun will never set again,

and your moon will wane no more;

the Lord will be your everlasting light,

and your days of sorrow will end.

21Then all your people will be righteous

and they will possess the land forever.

They are the shoot I have planted,

the work of my hands,

for the display of my splendor.

22The least of you will become a thousand,

the smallest a mighty nation.

I am the Lord;

in its time I will do this swiftly.”