ኢሳይያስ 57 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 57:1-21

1ጻድቅ ይሞታል፤

ይህን ግን ማንም ልብ አይልም፤

ለእግዚአብሔር ያደሩ ሰዎች ይወሰዳሉ፤

ጻድቃን ከክፉ ይድኑ ዘንድ፣

መወሰዳቸውን፣

ማንም አያስተውልም።

2በቅንነት የሚሄዱ፣

ሰላም ይሆንላቸዋል፤

መኝታቸው ላይ ያርፋሉ።

3“እናንት የአስማተኛዪቱ ልጆች ግን፣

እናንት የአመንዝራውና የጋለሞታዪቱ ዘር፤ እናንት፣ ወዲህ ኑ፤

4የምትሣለቁት በማን ላይ ነው?

የምታሽሟጥጡት ማንን ነው?

ምላሳችሁንስ አውጥታችሁ የምታሾፉት በማን ላይ ነው?

እናንት የዐመፀኞች ልጆች፣

የሐሰተኞች ዘር አይደላችሁምን?

5በባሉጥ ዛፎች መካከል፣

ቅጠሉ በተንዠረገገ ዛፍ ሥር በዝሙት የምትቃጠሉ፣

በሸለቆዎች፣ በዐለት ስንጣቂዎችም ውስጥ

ልጆቻችሁን የምትሠዉ አይደላችሁምን?

6በሸለቆው በሚገኙት ለስላሳ ድንጋዮች

ውስጥ ያሉት ጣዖቶች የአንቺ ናቸው፤

እነርሱም ዕጣ ፈንታዎችሽ ናቸው፤

ርግጥ ነው፣ በእነርሱ ላይ የመጠጥ ቍርባን አፍስሰሻል፤

የእህል ቍርባንም አቅርበሻል፤

ታዲያ፣ ስለ እነዚህ ነገሮች ዝም እላለሁን?

7ዐልጋሽን ከፍ ባለውና በረጅሙ ኰረብታ ላይ አነጠፍሽ፤

በዚያም መሥዋዕትሽን ልታቀርቢ ወጣሽ።

8ከመዝጊያሽና ከመቃንሽ ጀርባ፣

የጣዖት ምስሎችሽን ሰቀልሽ፤

እኔን ትተሽ መኝታሽን ገላለጥሽ፤

በላይም ወጥተሽ በጣም ገለጥሽው፤

መኝታቸውን ከወደድሽላቸው ጋር ስምምነት አደረግሽ፤

ዕርቃናቸውንም አየሽ።

9የወይራ ዘይት ይዘሽ፣

ሽቶ በላዩ ጨምረሽ ወደ ሞሎክ57፥9 ወይም ወደ ንጉሡ ሄድሽ፤

መልእክተኞችሽን57፥9 ወይም፣ ጣዖቶችሽን ወደ ሩቅ አገር ላክሽ፤

እስከ ራሱ እስከ ሲኦልም ዘለቅሽ።

10በመንገድ ብዛት ደከምሽ፤

ነገር ግን ‘ተስፋ የለውም’ አላልሽም፤

የጕልበት መታደስ አገኘሽ፤

ስለዚህም አልዛልሽም።

11“እኔን የዋሸሽኝ፤

ማንን ፈርተሽ፣ ማንንስ ሠግተሽ ነው?

እኔን ያላስታወስሽው፣

ይህንም በልብሽ ያላኖርሽው፣

እኔን ያልፈራሽው፣

ዝም ስላልሁ አይደለምን?

12ጽድቅሽንና ሥራሽን አጋልጣለሁ፤

እነርሱም አይጠቅሙሽም።

13ለርዳታ በምትጮኺበት ጊዜ፣

የሰበሰብሻቸው ጣዖቶች እስቲ ያድኑሽ!

ነፋስ ጠራርጎ ይወስዳቸዋል፤

ሽውሽውታም ይበትናቸዋል።

እኔን መጠጊያው ያደረገ ሰው ግን፣

ምድሪቱን ይወርሳል፤

የተቀደሰ ተራራዬንም ገንዘቡ ያደርገዋል።”

ልባቸው ለተሰበረ መጽናናት

14እንዲህ ይባላል፤

“አብጁ፤ አብጁ፤ መንገድ አዘጋጁ፤

ከሕዝቤ መንገድ ዕንቅፋት አስወግዱ።”

15ከፍ ከፍ ያለውና ልዕልና ያለው እርሱ፣

ስሙም ቅዱስ የሆነው፣ ለዘላለም የሚኖረው እንዲህ ይላል፤

“የተዋረዱትን መንፈሳቸውን ለማነሣሣት፣

የተሰበረ ልብ ያላቸውን ለማነቃቃት፣

ከፍ ባለውና በቅዱሱ ስፍራ እኖራለሁ፤

የተሰበረ ልብ ካለውና በመንፈሱ ከተዋረደው ጋር እሆናለሁ።

16የሰው መንፈስ በፊቴ እንዳይዝል፣

የፈጠርሁትም ሰው እስትንፋስ እንዳይቆም፣

ለዘላለም አልወቅሥም፤

ሁልጊዜም አልቈጣም።

17ኀጢአት ስለ ሞላበት ስግብግብነቱ ተቈጣሁት፤

ቀጣሁት፤ ፊቴንም በቍጣ ከእርሱ ሸሸግሁ፤

ያም ሆኖ በገዛ መንገዱ ገፋበት።

18መንገዶቹን አይቻለሁ፤ ቢሆንም እፈውሰዋለሁ፤

እመራዋለሁ፤ ለእርሱና ስለ እርሱ ለሚያለቅሱትም

መጽናናትን እመልሳለሁ፤

19በእስራኤል አልቃሾች ከንፈር ላይ ምስጋና እፈጥራለሁ።

በቅርብና በሩቅ ላሉት ሰላም፣ ሰላም ይሁን፤

እኔ እፈውሳቸዋለሁ” ይላል እግዚአብሔር

20ክፉዎች ግን ማዕበሉ ጭቃና ጕድፍ እንደሚያወጣ፣

ጸጥ ማለት እንደማይችል፣

እንደሚናወጥ ባሕር ናቸው።

21አምላኬ፣ “ለክፉዎች ሰላም የላቸውም” ይላል።

Ketab El Hayat

إشعياء 57:1-21

1هَلَكَ الصِّدِّيقُ فَلَمْ يَتَأَمَّلْ أَحَدٌ فِي نَفْسِهِ وَيَعْتَبِرْ، وَمَاتَ الأَتْقِيَاءُ وَلَمْ يُدْرِكْ أَحَدٌ أَنَّ الصِّدِّيقَ قَدْ أُخِذَ تَفَادِياً لِلْكَارِثَةِ. 2وَالسَّالِكُونَ بِالاسْتِقَامَةِ يَنْعَمُونَ بِالسَّلامِ، وَفِي مَضَاجِعِهِمْ يَسْتَرِيحُونَ.

3أَمَّا أَنْتُمْ يَا أَبْنَاءَ السَّاحِرَةِ، يَا نَسْلَ الْفَاسِقِ وَالْعَاهِرَةِ، فَادْنُوا مِنْ هُنَا. 4بِمَنْ تَسْخَرُونَ؟ وَعَلَى مَنْ تَفْغَرُونَ أَشْدَاقَكُمْ وَاسِعَةً وَتَدْلَعُونَ أَلْسِنَتَكُمْ؟ أَلَسْتُمْ أَنْتُمْ أَبْنَاءَ الْخُطَاةِ وَالْمُنَافِقِينَ؟ 5أَيُّهَا الْمُتَوَهِّجُونَ شَهْوَةً بَيْنَ أَشْجَارِ الْبَلُّوطِ، وَتَحْتَ كُلِّ شَجَرَةٍ خَضْرَاءَ، يَا مَنْ تَذْبَحُونَ أَوْلادَكُمْ فِي الأَوْدِيَةِ تَحْتَ شُقُوقِ الصُّخُورِ. 6إِنَّ نَصِيبَكُمْ هُوَ أَصْنَامُكُمْ مِنْ حَصَى الْوَادِي الْمَلْسَاءِ. هِيَ قُرْعَتُكُمْ، وَلَهَا سَكَبْتُمْ سَكِيبَ تَقْدِمَاتِكُمْ، وَأَصْعَدْتُمْ قَرَابِينَكُمْ، فَهَلْ أَرْضَى عَنْ هَذِهِ الأُمُورِ؟ 7نَصَبْتُمْ مَضَاجِعَ زِنَاكُمْ عَلَى جَبَلٍ شَامِخٍ مُرْتَفِعٍ، وَإِلَى هُنَاكَ صَعِدْتُمْ لِتُقَرِّبُوا ذَبَائِحَكُمْ، 8وَخَلْفَ الْبَابِ وَقَوَائِمِهِ أَقَمْتُمْ أَصْنَامَكُمْ، وَإِذْ هَجَرْتُمُونِي كَشَفْتُمْ عَنْ مَضَاجِعِكُمْ وَعَلَّوْتُمُوهَا وَوَسَّعْتُمُوهَا، وَأَبْرَمْتُمْ مَعَ أَصْنَامِكُمْ عَهْدَ زِنىً لأَنَّكُمْ أَحْبَبْتُمْ مَضَاجِعَهُمْ، وَتَأَمَّلْتُمْ فِي عُرْيِهِمْ. 9ارْتَحَلْتُمْ إِلَى مُولَكَ مُحَمَّلِينَ بِالدُّهْنِ، وَبِكَثْرَةِ الأَطْيَابِ، وَأَرْسَلْتُمْ سُفَرَاءَكُمْ إِلَى أَرْضٍ بَعِيدَةٍ، وَانْحَدَرْتُمْ حَتَّى إِلَى الْهَاوِيَةِ. 10أَصَابَكُمُ الإِعْيَاءُ مِنْ طُولِ الْمَسِيرِ، وَلَمْ تَقُولُوا: «يَئِسْنَا» بَلْ تَجَدَّدَتْ قُوَاكُمْ وَلَمْ تَخُورُوا. 11مِمَّنْ خِفْتُمْ وَارْتَعَبْتُمْ حَتَّى كَذِبْتُمْ وَلَمْ تَذْكُرُونِي أَوْ تُفَكِّرُوا فِيَّ؟ هَلِ اعْتَصَمْتُ بِالسَّكِينَةِ زَمَناً طَوِيلاً حَتَّى لَمْ تَعُودُوا تَخَافُونَنِي؟ 12سَأَتَحَدَّثُ عَنْ بِرِّكُمْ وَأَعْمَالِكُمْ، وَلَكِنَّهَا لَنْ تُجْدِيَكُمْ نَفْعاً.

13عِنْدَمَا تَسْتَغِيثُونَ، فَلْتُنْقِذْكُمْ مَجْمُوعَاتُ أَصْنَامِكُمْ! إِنَّ الرِّيحَ تَحْمِلُهَا جَمِيعاً، وَنَفْخَةٌ تَطْرَحُهَا بَعِيداً. أَمَّا مَنْ يَلُوذُ بِي فَإِنَّهُ يَرِثُ الأَرْضَ وَيَمْلِكُ جَبَلَ قُدْسِي.

تعزية التائب

14وَيُقَالُ آنَئِذٍ: مَهِّدُوا! مَهِّدُوا السَّبِيلَ، أَزِيلُوا كُلَّ مَعْثَرَةٍ مِنْ طَرِيقِ شَعْبِي. 15لأَنَّهُ هَكَذَا يَقُولُ الْعَلِيُّ السَّامِي، الْمُقِيمُ فِي الأَبَدِ، الَّذِي يُدْعَى اسْمُهُ الْقُدُّوسَ: إِنَّنِي أَسْكُنُ فِي الْعُلَى وَفِي الْمَوْضِعِ الْمُقَدَّسِ، وَأُقِيمُ مَعَ الْمُنْسَحِقِ، وَذَوِي الرُّوحِ الْمُتَوَاضِعَةِ، لأُحْيِيَ أَرْوَاحَ الْمُتَوَاضِعِينَ، وَأُنْعِشَ قُلُوبَ الْمُنْسَحِقِينَ. 16لأَنَّنِي لَا أُخَاصِمُ إِلَى الأَبَدِ، وَلا أَظَلُّ عَلَى الدَّوَامِ غَاضِباً، لِئَلَّا تَبِيدَ أَمَامِي رُوحُ الإِنْسَانِ الَّتِي خَلَقْتُهَا. 17قَدْ غَضِبْتُ عَلَى إِسْرَائِيلَ مِنْ جَرَّاءِ جَشَعِهِ، وَعَاقَبْتُهُ وَحَجَبْتُ عَنْهُ وَجْهِي سَخَطاً، وَلَكِنَّهُ أَوْغَلَ فِي عِصْيَانِهِ وَرَاءَ غِوَايَةِ قَلْبِهِ. 18لَقَدْ رَأَيْتُ طُرُقَهُ الْمَكْتُوبَةَ، إِنَّمَا سَأُقَوِّمُهُ وَأَقُودُهُ وَأَرُدُّ لَهُ وَلِنَائِحِيهِ الطُّمَأْنِينَةَ 19وَأَسْتَبْدِلُ نُوَاحَهُ بِالْحَمْدِ، يَقُولُ الرَّبُّ؛ فَيَكُونُ سَلامٌ لِلْقَرِيبِ وَالْبَعِيدِ لأَنَّنِي سَأَشْفِيهِ. 20أَمَّا الأَشْرَارُ فَهُمْ كَالْبَحْرِ الْهَائِجِ الَّذِي لَا يَهْدَأُ، تَقْذِفُ مِيَاهُهُ الْقَذَرَ وَالطِّينَ 21إِذْ لَيْسَ سَلامٌ لِلأَشْرَارِ، قَالَ إِلَهِي.