ኢሳይያስ 56 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 56:1-12

ለሌሎች የተሰጠ ድነት

1እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ፍትሕን ጠብቁ፤

መልካሙን አድርጉ፤

ማዳኔ በቅርብ ነው፤

ጽድቄም ፈጥኖ ይገለጣልና።

2ሰንበትን ሳያረክስ የሚያከብር፣

ክፉን ከማድረግ እጁን የሚሰበስብ፣ የሚገታ፣

እነዚህን የሚፈጽም ሰው የተባረከ ነው።”

3ወደ እግዚአብሔር የተጠጋ መጻተኛ፣

“እግዚአብሔር በርግጥ ከሕዝቡ ይለየኛል” አይበል፤

ጃንደረባም፣

“እኔ ደረቅ ዛፍ ነኝ” አይበል።

4እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ሰንበቶቼን ለሚያከብሩ ጃንደረቦች፣

ደስ የሚያሰኘኝን ለሚመርጡ፣

ቃል ኪዳኔን፣ ለሚጠብቁ

5በቤተ መቅደሴና በቅጥሮቼ ውስጥ፣

ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች የበለጠ፣

መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤

ለዘላለም፣

የማይጠፋ ስም እሰጣቸዋለሁ።

6እርሱን ለማገልገል፣

ራሳቸውን ከእግዚአብሔር ጋር ያቈራኙ መጻተኞች፣

የእግዚአብሔርን ስም በመውደድ፣

እርሱንም በማምለክ፣

ሰንበትን ሳያረክሱ የሚያከብሩትን ሁሉ፣

ቃል ኪዳኔንም የሚጠብቁትን፣

7ወደ ተቀደሰው ተራራዬ አመጣቸዋለሁ፤

በጸሎት ቤቴም ውስጥ ደስ አሰኛቸዋለሁ።

የሚቃጠል መሥዋዕታቸውንና ሌሎች መሥዋዕቶቻቸውን፣

በመሠዊያዬ ቢሠዉ እቀበላቸዋለሁ፤

ቤቴ፣ ለሕዝቦች ሁሉ

የጸሎት ቤት ተብሎ ይጠራልና።”

8የተበተኑትን እስራኤል የሚሰበስብ፣

ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ከተሰበሰቡት በተጨማሪ፣

ሌሎችን እንደ ገና እሰበስባለሁ።”

በክፉዎች ላይ የእግዚአብሔር ወቀሣ

9እናንት የምድር አራዊት ሁሉ ኑ፤

እናንት የዱር አራዊት ሁሉ ኑና በጥርሳቸሁ ቦጫጭቁ።

10የእስራኤል ጠባቂዎች ዕውሮች ናቸው፤

ዕውቀት የላቸውም፤

ሁሉም ድምፅ የለሽ ውሾች ናቸው፤

መጮኽ አይችሉም፤

ተጋድመው ያልማሉ፤

እንቅልፋሞች ናቸው።

11እጅግ ሲበዛ ሆዳም ውሾች ናቸው፤

ጠገብሁን አያውቁም፤

የማያስተውሉ እረኞች ናቸው፤

ሁሉም በየራሳቸው መንገድ ሄዱ፤

እያንዳንዳቸውም የግል ጥቅማቸውን ፈለጉ።

12እርስ በርሳቸውም፣ “ኑና የወይን ጠጅ እንገባበዝ፤

እስክንሰክር እንጠጣ፤

ነገም ያው እንደ ዛሬ፣

ምናልባትም የተሻለ ቀን ይሆንልናል” ይባባላሉ።

New International Version

Isaiah 56:1-12

Salvation for Others

1This is what the Lord says:

“Maintain justice

and do what is right,

for my salvation is close at hand

and my righteousness will soon be revealed.

2Blessed is the one who does this—

the person who holds it fast,

who keeps the Sabbath without desecrating it,

and keeps their hands from doing any evil.”

3Let no foreigner who is bound to the Lord say,

“The Lord will surely exclude me from his people.”

And let no eunuch complain,

“I am only a dry tree.”

4For this is what the Lord says:

“To the eunuchs who keep my Sabbaths,

who choose what pleases me

and hold fast to my covenant—

5to them I will give within my temple and its walls

a memorial and a name

better than sons and daughters;

I will give them an everlasting name

that will endure forever.

6And foreigners who bind themselves to the Lord

to minister to him,

to love the name of the Lord,

and to be his servants,

all who keep the Sabbath without desecrating it

and who hold fast to my covenant—

7these I will bring to my holy mountain

and give them joy in my house of prayer.

Their burnt offerings and sacrifices

will be accepted on my altar;

for my house will be called

a house of prayer for all nations.”

8The Sovereign Lord declares—

he who gathers the exiles of Israel:

“I will gather still others to them

besides those already gathered.”

God’s Accusation Against the Wicked

9Come, all you beasts of the field,

come and devour, all you beasts of the forest!

10Israel’s watchmen are blind,

they all lack knowledge;

they are all mute dogs,

they cannot bark;

they lie around and dream,

they love to sleep.

11They are dogs with mighty appetites;

they never have enough.

They are shepherds who lack understanding;

they all turn to their own way,

they seek their own gain.

12“Come,” each one cries, “let me get wine!

Let us drink our fill of beer!

And tomorrow will be like today,

or even far better.”