ኢሳይያስ 56 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 56:1-12

ለሌሎች የተሰጠ ድነት

1እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ፍትሕን ጠብቁ፤

መልካሙን አድርጉ፤

ማዳኔ በቅርብ ነው፤

ጽድቄም ፈጥኖ ይገለጣልና።

2ሰንበትን ሳያረክስ የሚያከብር፣

ክፉን ከማድረግ እጁን የሚሰበስብ፣ የሚገታ፣

እነዚህን የሚፈጽም ሰው የተባረከ ነው።”

3ወደ እግዚአብሔር የተጠጋ መጻተኛ፣

“እግዚአብሔር በርግጥ ከሕዝቡ ይለየኛል” አይበል፤

ጃንደረባም፣

“እኔ ደረቅ ዛፍ ነኝ” አይበል።

4እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ሰንበቶቼን ለሚያከብሩ ጃንደረቦች፣

ደስ የሚያሰኘኝን ለሚመርጡ፣

ቃል ኪዳኔን፣ ለሚጠብቁ

5በቤተ መቅደሴና በቅጥሮቼ ውስጥ፣

ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች የበለጠ፣

መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤

ለዘላለም፣

የማይጠፋ ስም እሰጣቸዋለሁ።

6እርሱን ለማገልገል፣

ራሳቸውን ከእግዚአብሔር ጋር ያቈራኙ መጻተኞች፣

የእግዚአብሔርን ስም በመውደድ፣

እርሱንም በማምለክ፣

ሰንበትን ሳያረክሱ የሚያከብሩትን ሁሉ፣

ቃል ኪዳኔንም የሚጠብቁትን፣

7ወደ ተቀደሰው ተራራዬ አመጣቸዋለሁ፤

በጸሎት ቤቴም ውስጥ ደስ አሰኛቸዋለሁ።

የሚቃጠል መሥዋዕታቸውንና ሌሎች መሥዋዕቶቻቸውን፣

በመሠዊያዬ ቢሠዉ እቀበላቸዋለሁ፤

ቤቴ፣ ለሕዝቦች ሁሉ

የጸሎት ቤት ተብሎ ይጠራልና።”

8የተበተኑትን እስራኤል የሚሰበስብ፣

ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ከተሰበሰቡት በተጨማሪ፣

ሌሎችን እንደ ገና እሰበስባለሁ።”

በክፉዎች ላይ የእግዚአብሔር ወቀሣ

9እናንት የምድር አራዊት ሁሉ ኑ፤

እናንት የዱር አራዊት ሁሉ ኑና በጥርሳቸሁ ቦጫጭቁ።

10የእስራኤል ጠባቂዎች ዕውሮች ናቸው፤

ዕውቀት የላቸውም፤

ሁሉም ድምፅ የለሽ ውሾች ናቸው፤

መጮኽ አይችሉም፤

ተጋድመው ያልማሉ፤

እንቅልፋሞች ናቸው።

11እጅግ ሲበዛ ሆዳም ውሾች ናቸው፤

ጠገብሁን አያውቁም፤

የማያስተውሉ እረኞች ናቸው፤

ሁሉም በየራሳቸው መንገድ ሄዱ፤

እያንዳንዳቸውም የግል ጥቅማቸውን ፈለጉ።

12እርስ በርሳቸውም፣ “ኑና የወይን ጠጅ እንገባበዝ፤

እስክንሰክር እንጠጣ፤

ነገም ያው እንደ ዛሬ፣

ምናልባትም የተሻለ ቀን ይሆንልናል” ይባባላሉ።

King James Version

Isaiah 56:1-12

1Thus saith the LORD, Keep ye judgment, and do justice: for my salvation is near to come, and my righteousness to be revealed.56.1 judgment: or, equity 2Blessed is the man that doeth this, and the son of man that layeth hold on it; that keepeth the sabbath from polluting it, and keepeth his hand from doing any evil.

3¶ Neither let the son of the stranger, that hath joined himself to the LORD, speak, saying, The LORD hath utterly separated me from his people: neither let the eunuch say, Behold, I am a dry tree. 4For thus saith the LORD unto the eunuchs that keep my sabbaths, and choose the things that please me, and take hold of my covenant; 5Even unto them will I give in mine house and within my walls a place and a name better than of sons and of daughters: I will give them an everlasting name, that shall not be cut off. 6Also the sons of the stranger, that join themselves to the LORD, to serve him, and to love the name of the LORD, to be his servants, every one that keepeth the sabbath from polluting it, and taketh hold of my covenant; 7Even them will I bring to my holy mountain, and make them joyful in my house of prayer: their burnt offerings and their sacrifices shall be accepted upon mine altar; for mine house shall be called an house of prayer for all people. 8The Lord GOD which gathereth the outcasts of Israel saith, Yet will I gather others to him, beside those that are gathered unto him.56.8 beside…: Heb. to his gathered

9¶ All ye beasts of the field, come to devour, yea, all ye beasts in the forest. 10His watchmen are blind: they are all ignorant, they are all dumb dogs, they cannot bark; sleeping, lying down, loving to slumber.56.10 sleeping: or, dreaming, or, talking in their sleep 11Yea, they are greedy dogs which can never have enough, and they are shepherds that cannot understand: they all look to their own way, every one for his gain, from his quarter.56.11 greedy: Heb. strong of appetite56.11 can…: Heb. know not to be satisfied 12Come ye, say they, I will fetch wine, and we will fill ourselves with strong drink; and to morrow shall be as this day, and much more abundant.