ኢሳይያስ 56 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 56:1-12

ለሌሎች የተሰጠ ድነት

1እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ፍትሕን ጠብቁ፤

መልካሙን አድርጉ፤

ማዳኔ በቅርብ ነው፤

ጽድቄም ፈጥኖ ይገለጣልና።

2ሰንበትን ሳያረክስ የሚያከብር፣

ክፉን ከማድረግ እጁን የሚሰበስብ፣ የሚገታ፣

እነዚህን የሚፈጽም ሰው የተባረከ ነው።”

3ወደ እግዚአብሔር የተጠጋ መጻተኛ፣

“እግዚአብሔር በርግጥ ከሕዝቡ ይለየኛል” አይበል፤

ጃንደረባም፣

“እኔ ደረቅ ዛፍ ነኝ” አይበል።

4እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ሰንበቶቼን ለሚያከብሩ ጃንደረቦች፣

ደስ የሚያሰኘኝን ለሚመርጡ፣

ቃል ኪዳኔን፣ ለሚጠብቁ

5በቤተ መቅደሴና በቅጥሮቼ ውስጥ፣

ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች የበለጠ፣

መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤

ለዘላለም፣

የማይጠፋ ስም እሰጣቸዋለሁ።

6እርሱን ለማገልገል፣

ራሳቸውን ከእግዚአብሔር ጋር ያቈራኙ መጻተኞች፣

የእግዚአብሔርን ስም በመውደድ፣

እርሱንም በማምለክ፣

ሰንበትን ሳያረክሱ የሚያከብሩትን ሁሉ፣

ቃል ኪዳኔንም የሚጠብቁትን፣

7ወደ ተቀደሰው ተራራዬ አመጣቸዋለሁ፤

በጸሎት ቤቴም ውስጥ ደስ አሰኛቸዋለሁ።

የሚቃጠል መሥዋዕታቸውንና ሌሎች መሥዋዕቶቻቸውን፣

በመሠዊያዬ ቢሠዉ እቀበላቸዋለሁ፤

ቤቴ፣ ለሕዝቦች ሁሉ

የጸሎት ቤት ተብሎ ይጠራልና።”

8የተበተኑትን እስራኤል የሚሰበስብ፣

ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ከተሰበሰቡት በተጨማሪ፣

ሌሎችን እንደ ገና እሰበስባለሁ።”

በክፉዎች ላይ የእግዚአብሔር ወቀሣ

9እናንት የምድር አራዊት ሁሉ ኑ፤

እናንት የዱር አራዊት ሁሉ ኑና በጥርሳቸሁ ቦጫጭቁ።

10የእስራኤል ጠባቂዎች ዕውሮች ናቸው፤

ዕውቀት የላቸውም፤

ሁሉም ድምፅ የለሽ ውሾች ናቸው፤

መጮኽ አይችሉም፤

ተጋድመው ያልማሉ፤

እንቅልፋሞች ናቸው።

11እጅግ ሲበዛ ሆዳም ውሾች ናቸው፤

ጠገብሁን አያውቁም፤

የማያስተውሉ እረኞች ናቸው፤

ሁሉም በየራሳቸው መንገድ ሄዱ፤

እያንዳንዳቸውም የግል ጥቅማቸውን ፈለጉ።

12እርስ በርሳቸውም፣ “ኑና የወይን ጠጅ እንገባበዝ፤

እስክንሰክር እንጠጣ፤

ነገም ያው እንደ ዛሬ፣

ምናልባትም የተሻለ ቀን ይሆንልናል” ይባባላሉ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以賽亞書 56:1-12

外族人蒙拯救

1耶和華說:

「你們當堅持正義,

秉行公義,

因為我的救恩快要來臨,

我的公義快要彰顯。

2謹守而不褻瀆安息日、

不做惡事的人有福了!」

3皈依耶和華的外族人啊,

不要以為耶和華會把你和祂的子民分開,

太監也不要覺得自己只是一棵枯樹。

4因為耶和華說:

「如果太監遵守我的安息日、

做我喜悅的事、

持守我的約,

5我必在我的殿中、

牆內賜給他們紀念碑和名號,

使他們勝過有兒女的人。

我必賜給他們永遠不會被除去的名號。

6至於那些皈依耶和華、

事奉祂、愛祂的名、

做祂的僕人、

謹守而不褻瀆安息日、

持守祂的約的外族人,

7我必領他們到我的聖山,

到向我禱告的殿內,

使他們歡欣。

他們獻上的燔祭和其他祭物必蒙悅納,

因為我的殿必被稱為萬民禱告的殿。」

8招聚以色列流亡者的主耶和華說:

「除了這些被招聚回來的人以外,

我還要招聚其他人。」

以色列昏庸的首領

9田野和林中的走獸啊,

來吞吃吧!

10以色列的守望者瞎眼無知,

是不會叫的啞巴狗,

只喜歡躺下睡覺做夢。

11這些人就像貪吃的狗,

不知飽足,

又像什麼都不懂的牧人,

人人各行其是,

追求自己的利益。

12他們說:「來吧,我去拿酒,

讓我們喝個痛快!

明天會跟今天一樣,

甚至更豐盛。」