ኢሳይያስ 55 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 55:1-13

ጥሪ ለተጠሙ

1እናንት የተጠማችሁ ሁሉ ኑ፤

እናንት ገንዘብ የሌላችሁ፣

ወደ ውሆች ኑ፤

ኑና ግዙ፤ ብሉም፤

ኑና ያለ ገንዘብ፣ ያለ ዋጋ፣

የወይን ጠጅና ወተት ግዙ።

2ገንዘባችሁን እንጀራ ባልሆነ ነገር ላይ ለምን ታጠፋላችሁ?

በማያጠግብስ ነገር ላይ ለምን ጕልበታችሁን ትጨርሳላችሁ?

ስሙ፤ እኔን ስሙኝ፤ መልካም የሆነውንም ብሉ፤

ነፍሳችሁም በጥሩ ምግብ ትደሰታለች።

3ጆሯችሁን ከፍታችሁ ወደ እኔ ቅረቡ፤

ነፍሳችሁም እንድትኖር አድምጡኝ።

ለዳዊት በገባሁት በጽኑ ፍቅሬ፣

ከእናንተም ጋር የዘላለም ኪዳን አደርጋለሁ።

4እነሆ፤ እርሱን ለሕዝቦች ምስክር፣

መሪ፣ የጦር አዝማችም አድርጌዋለሁ።

5እነሆ፤ የማታውቃቸውን መንግሥታት ትጠራለህ፤

የማያወቁህ መንግሥታት በፍጥነት ወደ አንተ ይመጣሉ፤

ምክንያቱም እግዚአብሔር አምላክህ፣

የእስራኤል ቅዱስ፣

በክብሩ ከፍ ከፍ አድርጎሃል።

6እግዚአብሔር በሚገኝበት ጊዜ ፈልጉት፤

ቀርቦም ሳለ ጥሩት።

7ክፉ ሰው መንገዱን፣

በደለኛም ሐሳቡን ይተው።

ወደ እግዚአብሔር ይመለስ፤ እርሱም ምሕረት ያደርግለታል፤

ወደ አምላካችን ይመለስ፤ ይቅርታው ብዙ ነውና።

8“ሐሳቤ እንደ ሐሳባችሁ፣

መንገዴ እንደ መንገዳችሁ አይደለምና”

ይላል እግዚአብሔር

9“ሰማያት ከምድር ከፍ እንደሚሉ፣

መንገዴ ከመንገዳችሁ፣

ሐሳቤም ከሐሳባችሁ እንዲሁ ከፍ ያለ ነው።

10ዝናምና በረዶ ከሰማይ ወርዶ፣

ምድርን በማራስ፣

እንድታበቅልና እንድታፈራ

ለዘሪው ዘር፣

ለበላተኛም እንጀራ እንድትሰጥ ሳያደርግ፣

ወደ ላይ እንደማይመለስ ሁሉ፣

11ከአፌ የሚወጣውም ቃሌ፣

በከንቱ ወደ እኔ አይመለስም፤

ነገር ግን የምሻውን ያከናውናል፤

የተላከበትንም ዐላማ ይፈጽማል።

12በደስታ ትወጣላችሁ፤

በሰላምም ትሸኛላችሁ፤

ተራሮችና ኰረብቶች፣

በፊታችሁ በእልልታ ይዘምራሉ፤

የሜዳ ዛፎች ሁሉ፣

ያጨበጭባሉ።

13በእሾኽ ፈንታ የጥድ ዛፍ፣

በኵርንችት ፈንታ ባርሰነት ይበቅላል።

ይህም የእግዚአብሔር መታሰቢያ፣

ሊጠፋ የማይችል፣

የዘላለም ምልክት ይሆናል።”

Ketab El Hayat

إشعياء 55:1-13

دعوة العطاش

1تَعَالَوْا أَيُّهَا الْعِطَاشُ جَمِيعاً إِلَى الْمِيَاهِ، وَهَلُمُّوا أَيُّهَا الْمُعْدَمُونَ مِنَ الْفِضَّةِ، ابْتَاعُوا وَكُلُوا، ابْتَاعُوا خَمْراً وَلَبَناً مَجَّاناً مِنْ غَيْرِ فِضَّةٍ. 2لِمَاذَا تُنْفِقُونَ الْفِضَّةَ عَلَى مَا لَيْسَ بِخُبْزٍ، وَتَتْعَبُونَ لِغَيْرِ شَبَعٍ؟ أَحْسِنُوا الاسْتِمَاعَ إِلَيَّ، وَكُلُوا الشَّهِيَّ وَلْتَتَمَتَّعْ أَنْفُسُكُمْ بِالدَّسَمِ. 3أَرْهِفُوا السَّمْعَ وَتَعَالَوْا إِلَيَّ؛ أَصْغُوا فَتَحْيَا نُفُوسُكُمْ، وَأُعَاهِدَكُمْ عَهْداً أَبَدِيًّا، هِيَ مَرَاحِمُ دَاوُدَ الثَّابِتَةُ الأَمِينَةُ 4هَا أَنَا قَدْ جَعَلْتُهُ شَاهِداً لِلشُّعُوبِ زَعِيماً وَقَائِداً لِلأُمَمِ. 5انْظُرْ، إِنَّكَ تَدْعُو أُمَماً لَا تَعْرِفُهَا، وَتَسْعَى إِلَيْكَ أُمَمٌ لَمْ تَعْرِفْكَ، بِفَضْلِ الرَّبِّ إِلَهِكَ، وَمِنْ أَجْلِ قُدُّوسِ إِسْرَائِيلَ، لأَنَّهُ قَدْ مَجَّدَكَ.

6اطْلُبُوا الرَّبَّ مَادَامَ مَوْجُوداً، ادْعُوهُ وَهُوَ قَرِيبٌ. 7لِيَتْرُكِ الشِّرِّيرُ طَرِيقَهُ وَالأَثِيمُ أَفْكَارَهُ، وَلْيَتُبْ إِلَى الرَّبِّ فَيَرْحَمَهُ، وَلْيَرْجِعْ إِلَى إِلَهِنَا لأَنَّهُ يُكْثِرُ الْغُفْرَانَ. 8لأَنَّ أَفْكَارِي لَيْسَتْ مُمَاثِلَةً لأَفْكَارِكُمْ، وَلا طُرُقَكُمْ مِثْلُ طُرُقِي، يَقُولُ الرَّبُّ. 9فَكَمَا ارْتَفَعَتِ السَّمَاوَاتُ عَنِ الأَرْضِ، كَذَلِكَ ارْتَفَعَتْ طُرُقِي عَنْ طُرُقِكُمْ، وَأَفْكَارِي عَنْ أَفْكَارِكُمْ. 10وَكَمَا تَهْطِلُ الأَمْطَارُ وَيَنْهَمِرُ الثَّلْجُ مِنَ السَّمَاءِ، وَلا تَرْجِعُ إِلَى هُنَاكَ، بَلْ تُرْوِي الْحُقُولَ وَالأَشْجَارَ، وَتَجْعَلُ الْبُذُورَ تُنْبِتُ وَتَنْمُو وَتُثْمِرُ زَرْعاً لِلزَّارِعِ وَخُبْزاً لِلْجِيَاعِ، 11هَكَذَا تَكُونُ كَلِمَتِي الَّتِي تَصْدُرُ عَنِّي مُثْمِرَةً دَائِماً، وَتُحَقِّقُ مَا أَرْغَبُ فِيهِ وَتُفْلِحُ بِمَا أَعْهَدُ بِهِ إِلَيْهَا. 12لأَنَّكُمْ سَتَتْرُكُونَ بَابِلَ بِفَرَحٍ وَسَلامٍ فَتَتَرَنَّمُ الْجِبَالُ وَالتِّلالُ أَمَامَكُمْ بَهْجَةً وَتُصَفِّقُ أَشْجَارُ الْحَقْلِ بِأَيْدِيهَا غِبْطَةً، 13وَحَيْثُ كَانَ الشَّوْكُ وَالْقُرَّاصُ، تَنْمُو أَشْجَارُ السَّرْوِ وَالآسِ: فَيَكُونُ ذَلِكَ تَخْلِيداً لاسْمِ الرَّبِّ وَعَلامَةً أَبَدِيَّةً لَا تُمْحَى.