ኢሳይያስ 52 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 52:1-15

1ጽዮን ሆይ፤ ተነሺ፤ ተነሺ፤

ኀይልን ልበሺ፤

ቅድስቲቱ ከተማ፤ ኢየሩሳሌም ሆይ!

የክብር ልብስሽን ልበሺ፤

ያልተገረዘ የረከሰም

ከእንግዲህ ወደ አንቺ አይገባም።

2ትቢያሽን አራግፊ፤

ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ተነሺ በዙፋንሽ ላይ ተቀመጪ፤

ምርኮኛዪቱ የጽዮን ልጅ ሆይ፤

የዐንገትሽን የእስራት ሰንሰለት አውልቀሽ ጣዪ።

3እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ያለ ዋጋ ተሸጣችሁ ነበር፤

ያለ ገንዘብ ትቤዣላችሁ።”

4ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“በመጀመሪያ ሕዝቤ ይኖር ዘንድ ወደ ግብፅ ወረደ፤

በኋላም አሦር ያለ ምክንያት አስጨንቆ ገዛው።

5“አሁን እዚህ ምን አለኝ?” ይላል እግዚአብሔር

“ሕዝቤ ያለ ምክንያት ተወስዷል፤

የገዟቸው ተሣልቀውባቸዋል”52፥5 የሙት ባሕር ጥቅሎችና ቩልጌት ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ የማሶሬቱ ቅጅ ግን፣ ሙሾ ይላል።

ይላል እግዚአብሔር

“ቀኑን ሙሉ፣

ስሜ ያለ ማቋረጥ ይሰደባል።

6ስለዚህ ሕዝቤ ስሜን ያውቃል፤

በዚያ ቀንም፣

አስቀድሜ የተናገርሁ እኔ መሆኔን ይረዳል፤

እነሆ፤ እኔው ነኝ።”

7በተራሮች ላይ የቆሙ፣

የምሥራች ይዘው የሚመጡ እግሮች፣

ሰላምን የሚናገሩ፣

መልካም ዜና የሚያበሥሩ፣

ድነትን የሚያውጁ፣

ጽዮንንም፣

“አምላክሽ ነግሧል” የሚሉ እንዴት ያማሩ ናቸው።

8ስሚ፤ ጠባቂዎችሽ ድምፃቸውን ከፍ አድርገዋል፤

በአንድነት በእልልታ ይዘምራሉ።

እግዚአብሔር ወደ ጽዮን ሲመለስ፣

በዐይኖቻቸው ያያሉ።

9እናንት የኢየሩሳሌም ፍርስራሾች፣

በአንድነት በእልልታ ዘምሩ፤

እግዚአብሔር ሕዝቡን አጽናንቷል፤

ኢየሩሳሌምንም ተቤዥቷልና።

10እግዚአብሔር በመንግሥታት ሁሉ ፊት፣

የተቀደሰ ክንዱን ይገልጣል፤

በምድር ዳርቻዎች ያሉ ሁሉ፣

የአምላካችንን ማዳን ያያሉ።

11እናንት የእግዚአብሔርን ዕቃ የምትሸከሙ፣

ተለዩ፤ ተለዩ፤ ከዚያ ውጡ፤

ርኩስ ነገር አትንኩ፤

ከዚያ ውጡ ንጹሓንም ሁኑ።

12ሆኖም በችኰላ አትወጡም፤

ሸሽታችሁም አትሄዱም፤

እግዚአብሔር ፊት ፊታችሁ ይሄዳል፤

የእስራኤል አምላክ ደጀን ይሆናችኋል።

የባሪያው ሥቃይና ክብር

13እነሆ፤ ባሪያዬ የሚያከናውነው በማስተዋል ነው፤52፥13 ወይም ባሪያዬ ይበለጽጋል

ገናና ይሆናል፤ ከፍ ከፍ ይላል፤ እጅግ ይከብራልም።

14ብዙዎች በእርሱ52፥14 ዕብራይስጡ፣ በአንተ ይላል። እስኪደነግጡ ድረስ፣

መልኩ ከማንም ሰው ተለየ፤

ከሰው ልጆችም ሁሉ ይልቅ ተጐሳቈለ።

15ስለዚህ ብዙ መንግሥታትን ያስደንቃል፤

በእርሱ ምክንያት ነገሥታት አፋቸውን ይይዛሉ፤

ያልተነገራቸውን ያያሉ፤

ያልሰሙትን ያስተውላሉ።

King James Version

Isaiah 52:1-15

1Awake, awake; put on thy strength, O Zion; put on thy beautiful garments, O Jerusalem, the holy city: for henceforth there shall no more come into thee the uncircumcised and the unclean. 2Shake thyself from the dust; arise, and sit down, O Jerusalem: loose thyself from the bands of thy neck, O captive daughter of Zion. 3For thus saith the LORD, Ye have sold yourselves for nought; and ye shall be redeemed without money. 4For thus saith the Lord GOD, My people went down aforetime into Egypt to sojourn there; and the Assyrian oppressed them without cause. 5Now therefore, what have I here, saith the LORD, that my people is taken away for nought? they that rule over them make them to howl, saith the LORD; and my name continually every day is blasphemed. 6Therefore my people shall know my name: therefore they shall know in that day that I am he that doth speak: behold, it is I.

7¶ How beautiful upon the mountains are the feet of him that bringeth good tidings, that publisheth peace; that bringeth good tidings of good, that publisheth salvation; that saith unto Zion, Thy God reigneth! 8Thy watchmen shall lift up the voice; with the voice together shall they sing: for they shall see eye to eye, when the LORD shall bring again Zion.

9¶ Break forth into joy, sing together, ye waste places of Jerusalem: for the LORD hath comforted his people, he hath redeemed Jerusalem. 10The LORD hath made bare his holy arm in the eyes of all the nations; and all the ends of the earth shall see the salvation of our God.

11¶ Depart ye, depart ye, go ye out from thence, touch no unclean thing; go ye out of the midst of her; be ye clean, that bear the vessels of the LORD. 12For ye shall not go out with haste, nor go by flight: for the LORD will go before you; and the God of Israel will be your rereward.52.12 be…: Heb. gather you up

13¶ Behold, my servant shall deal prudently, he shall be exalted and extolled, and be very high.52.13 deal…: or, prosper 14As many were astonied at thee; his visage was so marred more than any man, and his form more than the sons of men: 15So shall he sprinkle many nations; the kings shall shut their mouths at him: for that which had not been told them shall they see; and that which they had not heard shall they consider.