ኢሳይያስ 52 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 52:1-15

1ጽዮን ሆይ፤ ተነሺ፤ ተነሺ፤

ኀይልን ልበሺ፤

ቅድስቲቱ ከተማ፤ ኢየሩሳሌም ሆይ!

የክብር ልብስሽን ልበሺ፤

ያልተገረዘ የረከሰም

ከእንግዲህ ወደ አንቺ አይገባም።

2ትቢያሽን አራግፊ፤

ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ተነሺ በዙፋንሽ ላይ ተቀመጪ፤

ምርኮኛዪቱ የጽዮን ልጅ ሆይ፤

የዐንገትሽን የእስራት ሰንሰለት አውልቀሽ ጣዪ።

3እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ያለ ዋጋ ተሸጣችሁ ነበር፤

ያለ ገንዘብ ትቤዣላችሁ።”

4ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“በመጀመሪያ ሕዝቤ ይኖር ዘንድ ወደ ግብፅ ወረደ፤

በኋላም አሦር ያለ ምክንያት አስጨንቆ ገዛው።

5“አሁን እዚህ ምን አለኝ?” ይላል እግዚአብሔር

“ሕዝቤ ያለ ምክንያት ተወስዷል፤

የገዟቸው ተሣልቀውባቸዋል”52፥5 የሙት ባሕር ጥቅሎችና ቩልጌት ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ የማሶሬቱ ቅጅ ግን፣ ሙሾ ይላል።

ይላል እግዚአብሔር

“ቀኑን ሙሉ፣

ስሜ ያለ ማቋረጥ ይሰደባል።

6ስለዚህ ሕዝቤ ስሜን ያውቃል፤

በዚያ ቀንም፣

አስቀድሜ የተናገርሁ እኔ መሆኔን ይረዳል፤

እነሆ፤ እኔው ነኝ።”

7በተራሮች ላይ የቆሙ፣

የምሥራች ይዘው የሚመጡ እግሮች፣

ሰላምን የሚናገሩ፣

መልካም ዜና የሚያበሥሩ፣

ድነትን የሚያውጁ፣

ጽዮንንም፣

“አምላክሽ ነግሧል” የሚሉ እንዴት ያማሩ ናቸው።

8ስሚ፤ ጠባቂዎችሽ ድምፃቸውን ከፍ አድርገዋል፤

በአንድነት በእልልታ ይዘምራሉ።

እግዚአብሔር ወደ ጽዮን ሲመለስ፣

በዐይኖቻቸው ያያሉ።

9እናንት የኢየሩሳሌም ፍርስራሾች፣

በአንድነት በእልልታ ዘምሩ፤

እግዚአብሔር ሕዝቡን አጽናንቷል፤

ኢየሩሳሌምንም ተቤዥቷልና።

10እግዚአብሔር በመንግሥታት ሁሉ ፊት፣

የተቀደሰ ክንዱን ይገልጣል፤

በምድር ዳርቻዎች ያሉ ሁሉ፣

የአምላካችንን ማዳን ያያሉ።

11እናንት የእግዚአብሔርን ዕቃ የምትሸከሙ፣

ተለዩ፤ ተለዩ፤ ከዚያ ውጡ፤

ርኩስ ነገር አትንኩ፤

ከዚያ ውጡ ንጹሓንም ሁኑ።

12ሆኖም በችኰላ አትወጡም፤

ሸሽታችሁም አትሄዱም፤

እግዚአብሔር ፊት ፊታችሁ ይሄዳል፤

የእስራኤል አምላክ ደጀን ይሆናችኋል።

የባሪያው ሥቃይና ክብር

13እነሆ፤ ባሪያዬ የሚያከናውነው በማስተዋል ነው፤52፥13 ወይም ባሪያዬ ይበለጽጋል

ገናና ይሆናል፤ ከፍ ከፍ ይላል፤ እጅግ ይከብራልም።

14ብዙዎች በእርሱ52፥14 ዕብራይስጡ፣ በአንተ ይላል። እስኪደነግጡ ድረስ፣

መልኩ ከማንም ሰው ተለየ፤

ከሰው ልጆችም ሁሉ ይልቅ ተጐሳቈለ።

15ስለዚህ ብዙ መንግሥታትን ያስደንቃል፤

በእርሱ ምክንያት ነገሥታት አፋቸውን ይይዛሉ፤

ያልተነገራቸውን ያያሉ፤

ያልሰሙትን ያስተውላሉ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以賽亞書 52:1-15

錫安必獲救

1錫安啊,醒來吧,醒來吧,展示你的能力!

聖城耶路撒冷啊,

穿上你華美的衣服!

從今以後,

未受割禮和不潔淨的人必不得進入你的城門。

2耶路撒冷啊,抖掉身上的灰塵,

起來坐到寶座上!

被擄的錫安城啊,

卸去你頸上的鎖鏈!

3耶和華說:「你們被賣未得分文,你們被贖回也不需分文。」 4主耶和華說:「起先我的子民到埃及寄居,後來亞述人無緣無故地欺壓他們。」 5耶和華說:「我這裡還有什麼呢?我的子民白白地被擄去,轄制他們的人咆哮大叫,我的名整天被褻瀆。 6然而,我的子民終會認識我的名。到那日,他們就會知道是我對他們說,『我在這裡。』」

7那穿山越嶺之人的腳蹤是何等佳美!

他帶來佳音,報告平安,

傳遞喜訊,宣佈救恩,

錫安說:「你的上帝做王了。」

8聽啊,你的守望者都一同高聲歡呼,

因為耶和華回到錫安的時候,

他們必親眼看見。

9耶路撒冷的荒場啊,

你們要一同歡呼歌唱,

因為耶和華安慰了祂的子民,

救贖了耶路撒冷

10耶和華要向萬國展現祂神聖的大能,

普天下將看見我們上帝的救恩。

11離開吧,離開吧,

離開巴比倫吧!

不要碰不潔淨的東西。

你們抬耶和華器具的人啊,

要從那裡出來,要潔淨自己。

12你們不必匆忙離開,

也不用奔逃,

因為耶和華必走在你們前面,

以色列的上帝必作你們的後盾。

13看啊,我的僕人必成功,

受到擁戴、仰慕和尊崇。

14許多人看見祂就詫異,

祂的面容被毀、身體被殘害得不成人樣。

15祂必洗淨許多國家,

君王必因祂而閉口無言。

因為他們將看見未曾聽過的事,

明白聞所未聞的事。