ኢሳይያስ 5 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 5:1-30

ስለ ወይን ቦታ የተነገረ ቅኔ

1ስለ ወዳጄ፣

ደግሞም ስለ ወይን ቦታው ልዘምር፤

ወዳጄ በለምለም ኰረብታ ላይ

የወይን ቦታ ነበረው።

2መሬቱን ቈፈረ፤ ድንጋይንም ለቅሞ አወጣ፤

ምርጥ የሆነውንም ወይን ተከለበት።

በመካከሉ መጠበቂያ ማማ ሠራ፤

የወይን መጭመቂያ ጕድጓድም አበጀ፤

ከዚያ መልካም ፍሬ ያፈራል ብሎ ዐሰበ፤

ነገር ግን ኮምጣጣ ፍሬ አፈራ።

3“እናንት በኢየሩሳሌም የምትኖሩና የይሁዳ ሰዎች ሆይ፤

በእኔና በወይኔ ቦታ መካከል እስቲ ፍረዱ።

4ከዚህ ካደረግሁለት በላይ ለወይኔ ቦታ ምን

ሊደረግለት ይገባ ነበር?

መልካም የወይን ፍሬ ያፈራል ብዬ

ስጠብቅ ለምን ኮምጣጣ ፍሬ አፈራ?

5እንግዲህ በወይኔ ቦታ

ምን እንደማደርግ ልንገራችሁ፤

ዐጥሩን እነቅላለሁ፤

ለጥፋት ይጋለጣል፤

ግንቡንም አፈርሳለሁ፣

መረጋገጫም ይሆናል።

6የማይኰተኰትና የማይታረም

ጠፍ መሬት አደርገዋለሁ፤

ኵርንችትና እሾኽም ይበቅልበታል፤

ዝናብም እንዳይዘንብበት

ደመናዎችን አዝዛለሁ።”

7የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔር

የወይን ቦታው የእስራኤል ቤት ነው፤

የይሁዳ ሰዎችም

የደስታው አትክልት ናቸው።

ፍትሕን ፈለገ፤ ነገር ግን ደም ማፍሰስን አየ፤

ጽድቅን ፈለገ፤ ነገር ግን የጭንቅን ጩኸት ሰማ።

ወዮታና ፍርድ

8ስፍራ ለሌሎች እስከማይተርፍ፣

ቤትን በቤት ላይ በመጨመር፣

መሬትን ከመሬት ጋር በማያያዝ፣

ለብቻችሁ በምድር ተስፋፍታችሁ ለምትኖሩ ወዮላችሁ

9የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ጆሮዬ እየሰማ እንዲህ ሲል ተናገረ፤

“ታላላቅ ቤቶች ወና ይቀራሉ፣

የሚያማምሩም ቤቶች ኗሪ ያጣሉ።

10ከሩብ ጋሻ5፥10 በዕብራይስጥ፣ ሩብ ጋሻ መሬት በዐሥር ጥማድ በሬ በአንድ ቀን የሚታረስ ነው። የወይን ቦታ አንድ የባዶስ መስፈሪያ ያህል የወይን ጭማቂ ብቻ ይገኛል፤ አንድ የቆሮስ መስፈሪያ ዘር ተዘርቶ አንድ የኢፍ መስፈሪያ እህል ብቻ ይሰጣል።”5፥10 ምናልባት አንድ ባዶስ ሀያ ሁለት ሊትር ያህል ነው። አንድ የቆሮስ መስፈሪያ መቶ ስድሳ ኪሎ ግራም ያህል ነው። አንድ የኢፍ መስፈሪያ ዐሥራ ስምንት ኪሎ ግራም ያህል ነው።

11የሚያሰክር መጠጥ ፍለጋ

ማልደው ለሚነሡ፣

እስኪያነድዳቸውም ወይን በመጠጣት

ሌሊቱን ለሚያነጉ ወዮላቸው!

12በግብዣቸው ላይ በገናና መሰንቆ፣

ከበሮና ዋሽንት እንዲሁም የወይን ጠጅ አለ፤

ነገር ግን ለእግዚአብሔር ሥራ ቦታ አልሰጡም፤

ለእጆቹም ሥራ ክብር አላሳዩም።

13ስለዚህ ሕዝቤ

ዕውቀት በማጣቱ ይማረካል፤

መኳንንቱም በራብ ይሞታሉ፤

ሕዝቡም በውሃ ጥም ይቃጠላል።

14ስለዚህ ሲኦል5፥14 በዕብራይስጡ፣ መቃብር ማለት ነው። ሆዷን አሰፋች፣

አፏንም ያለ ልክ ከፈተች፤

መኳንንቱና ሕዝቡ ከረብሸኞቻቸውና ከጨፋሪዎቻቸው ጋር

ወደዚያ ይወርዳሉ።

15ሰው ይዋረዳል፤

የሰው ልጅም ዝቅ ዝቅ ይላል፤

የእብሪተኛውም ዐይን ይሰበራል።

16የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ግን በፍትሕ ከፍ ከፍ ይላል፤

ቅዱሱም አምላክ ቅድስናውን በጽድቅ ይገልጻል።

17በጎችም በገዛ መሰማሪያቸው እንደሚሰማሩ ሆነው ይግጣሉ፤

የበግ ጠቦቶችም በባለጠጎች ፍርስራሽ ላይ ሣር ይበላሉ5፥17 በዕብራይስጡ፣ እንግዶች ይበሉታል ይለዋል።

18ኀጢአትን በማታለል ገመድ ለሚስቡ፣

በደልንም በሠረገላ ማሰሪያ ለሚጐትቱ ወዮላቸው!

19“በዐይናችን እንድናይ

እግዚአብሔር ይቸኵል፤

ሥራውንም ያፋጥን፤

የእስራኤልን ቅዱስ፣ የእርሱን ዕቅድ

እንድናውቃት ትቅረብ፤

ትምጣም” ለሚሉ ወዮላቸው!

20ክፉውን መልካም፣

መልካሙን ክፉ ለሚሉ

ብርሃኑን ጨለማ፣

ጨለማውን ብርሃን ለሚያደርጉ፣

ጣፋጩን መራራ፣

መራራውንም ጣፋጭ ለሚያደርጉ ወዮላቸው!

21ራሳቸውን እንደ ብልኅ ለሚቈጥሩ፣

በራሳቸውም አመለካከት ጥበበኛ ለሆኑ ወዮላቸው!

22የወይን ጠጅ ለመጠጣት ጀግኖች፣

የሚያሰክር መጠጥ ለመደባለቅ ብርቱ ለሆኑ ወዮላቸው!

23ጕቦን በመቀበል በደለኛን ንጹሕ ለሚያደርጉ፣

ለበደል አልባ ሰው ፍትሕን ለሚነፍጉ ወዮላቸው!

24ስለዚህ የእሳት ነበልባል ገለባን እንደሚበላ፣

ድርቆሽም በእሳት ጋይቶ እንደሚጠፋ፣

የእነርሱም ሥር እንዲሁ ይበሰብሳል፤

አበባቸውም እንደ ትቢያ ይበንናል፤

የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔርን ሕግ ንቀዋልና፤

የእስራኤል ቅዱስ የተናገረውንም ቃል አቃልለዋል።

25የእግዚአብሔር ቍጣ በሕዝቡ ላይ ነድዷል፤

እጁን አንሥቶ መትቷቸዋል፤

ተራሮች ራዱ፤

ሬሳዎችም በመንገድ ላይ እንደ ተጣለ ጥራጊ ሆኑ፤

ይህ ሁሉ ሆኖ ግን ቍጣው ገና አልተመለሰም፤

እጁም እንደ ተነሣ ነው።

26ከሩቅ ያሉትን ሕዝቦች የሚጠራበትን

ምልክት ያቆማል፤

ከምድር ዳርቻም በፉጨት ይጠራቸዋል፤

እነርሱም እየተጣደፉ በፍጥነት ይመጣሉ።

27በመካከላቸው ደካማና ስንኩል አይገኝም፤

የሚያንቀላፋና የሚተኛ አይኖርም፤

የወገባቸው መቀነት አይላላም፤

የጫማቸውም ማሰሪያ አይበጠስም።

28ፍላጻቸው የተሳለ፣

ቀስታቸውም የተደገነ ነው፤

የሠረገሎቻቸውም መንኰራኵሮች እንደ

ዐውሎ ነፋስ ናቸው።

29ጩኸታቸው እንደ አንበሳ ነው፤

እንደ አንበሳ ደቦል ያገሣሉ፤

ያደኑትንም ይዘው ይጮኻሉ፤

ተሸክመውት ይሄዳሉ፤ የሚያስጥልም የለም።

30በዚያን ቀን

እንደ ባሕር ሞገድ ይጮኹበታል፤

ማንም ወደ ምድር ቢመለከት፣

ጨለማንና መከራን ያያል፤

ብርሃን እንኳ በደመናዎች ይጋረዳል።

Thai New Contemporary Bible

อิสยาห์ 5:1-30

บทเพลงสวนองุ่น

1ข้าพเจ้าจะขับร้องบทเพลงแด่ผู้ที่เป็นที่รักของ

ข้าพเจ้า เกี่ยวกับสวนองุ่นของเขา

ที่รักของข้าพเจ้ามีสวนองุ่นแปลงหนึ่งบนไหล่

เขาอันอุดมสมบูรณ์

2เขาไถที่และกำจัดกรวดหิน

และปลูกองุ่นพันธุ์เยี่ยม

เขาสร้างหอยาม

และสกัดบ่อย่ำองุ่นไว้ด้วย

จากนั้นเขารอเก็บผลองุ่นชั้นดี

แต่กลับได้องุ่นเปรี้ยว

3“โอ ชาวเยรูซาเล็มและชาวยูดาห์

จงตัดสินความระหว่างเรากับสวนองุ่นของเรา

4เราจะทำอะไรได้อีก

เพื่อสวนองุ่นของเรา?

เราหวังผลองุ่นที่ดี

แต่ทำไมกลับได้แต่องุ่นเปรี้ยว?

5เราจะบอกให้ว่าเราจะทำอะไรกับสวนองุ่นนั้น

เราจะรื้อรั้วลงและปล่อยให้สวนนั้นถูกทำลาย

เราจะทลายกำแพงลง

และมันจะถูกเหยียบย่ำ

6เราจะทิ้งให้เริศร้าง

ไม่ลิดกิ่งหรือพรวนดินให้

ปล่อยให้หนามขึ้นรกไปหมด

เราจะสั่งเมฆไม่ให้ส่งฝน

มารดมันอีกต่อไป”

7สวนองุ่นของพระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์คือวงศ์วานอิสราเอล

ชนยูดาห์คือสวนที่ทรงปีติยินดี

พระองค์ทรงหวังให้พวกเขาออกผลเป็นความยุติธรรม แต่กลับเห็นการนองเลือด

ทรงคาดหวังความชอบธรรม แต่กลับได้ยินเสียงโหยไห้ร้องทุกข์

วิบัติและโทษทัณฑ์

8วิบัติแก่เจ้าผู้ซื้อที่ดิน

จนผู้อื่นไม่มีที่อาศัย

บ้านของเจ้าสร้างบนที่ดินผืนใหญ่

จนเจ้าสามารถอยู่ตามลำพังในดินแดนนั้น

9ข้าพเจ้าได้ยินพระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ประกาศว่า

“บ้านใหญ่ๆ จะเริศร้างอย่างแน่นอน

คฤหาสน์งดงามก็จะไร้ผู้อยู่อาศัย

10สวนองุ่นสิบๆ แอก5:10 คือ ที่ดินซึ่งวัวสิบคู่เทียมแอกไถได้ในหนึ่งวันจะผลิตเหล้าองุ่นได้เพียงบัทเดียว

เมล็ดพืชหนึ่งโฮเมอร์จะให้ผลเพียงเอฟาห์เดียว5:10 หนึ่งบัทเท่ากับ 22 ลิตร หนึ่งโฮเมอร์เท่ากับ 220 ลิตร หนึ่งเอฟาห์เท่ากับ 22 ลิตร

11วิบัติแก่บรรดาผู้ที่ลุกขึ้นแต่เช้าตรู่

เพื่อไปดื่มสุราเฉื่อยแฉะและเมาหยำเปจนดึกดื่น

12ในงานเลี้ยง เขาจัดให้มีพิณใหญ่และพิณเขาคู่

รำมะนา ขลุ่ย และเหล้าองุ่น

แต่ไม่ไยดีสิ่งที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงกระทำ

ไม่เคารพนับถือพระราชกิจของพระองค์

13ฉะนั้นประชากรของเราจะตกเป็นเชลย

เพราะขาดความเข้าใจ

พวกเจ้าใหญ่นายโตจะตายเพราะความหิวโหย

ส่วนมวลชนก็แห้งระโหยเพราะความกระหาย

14หลุมฝังศพจึงเพิ่มความอยากของมัน

และอ้าปากกว้าง

กลืนกินทั้งผู้ใหญ่ผู้น้อย

พร้อมทั้งคนที่ทะเลาะวิวาทและที่สนุกสนานเฮฮา

15มนุษย์จึงถูกทำให้ตกต่ำลง

และมนุษยชาติถูกทำให้ต่ำต้อย

ผู้หยิ่งผยองถูกปราบให้ตกต่ำ

16แต่พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์จะเป็นที่ยกย่องเทิดทูนเนื่องด้วยความยุติธรรมของพระองค์

และพระเจ้าผู้บริสุทธิ์จะสำแดงพระองค์ว่าบริสุทธิ์โดยความชอบธรรมของพระองค์

17แล้วแกะจะกินหญ้าอยู่ในทุ่งหญ้าของมันเอง

ลูกแกะจะกิน5:17 ภาษาฮีบรูว่าคนแปลกหน้าจะกินอาหารท่ามกลางซากปรักหักพังของคนร่ำรวย

18วิบัติแก่ผู้ที่ใช้เล่ห์เหลี่ยมลากดึงบาปและความชั่วร้ายไป

เหมือนใช้เชือกลากดึงเกวียน

19วิบัติแก่ผู้ที่กล่าวว่า “พระเจ้า เร็วๆ หน่อย

รีบทำการไวๆ เราจะได้เห็น มาเร็วๆ เถิด

ขอให้แผนการขององค์บริสุทธิ์แห่งอิสราเอลมาถึง

เราจะได้รู้”

20วิบัติแก่ผู้ที่เรียกชั่วว่าดี

เรียกดีว่าชั่ว

เรียกมืดว่าสว่าง ที่สว่างกลับว่ามืด

เรียกขมว่าหวาน ที่หวานกลับว่าขม

21วิบัติแก่ผู้ที่ทึกทักว่าตนเองฉลาด

และหลักแหลมในสายตาของตนเอง

22วิบัติแก่ผู้ที่อวดเก่งในเรื่องดื่มสุรา

และเป็นผู้ชนะเลิศในการผสมเหล้า

23ผู้ปล่อยตัวคนทำผิดเพื่อสินบน

และไม่ยอมให้ความยุติธรรมแก่ผู้บริสุทธิ์

24ดังนั้นรากของพวกเขาจะเน่าเปื่อย

และดอกของเขาจะปลิวไปเหมือนธุลี

เหมือนเปลวไฟเผาฟาง

เหมือนหญ้าแห้งลุกมอดไปในไฟ

เพราะเขาละทิ้งบทบัญญัติของพระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์

และลบหลู่พระวจนะขององค์บริสุทธิ์แห่งอิสราเอล

25ฉะนั้นพระพิโรธขององค์พระผู้เป็นเจ้าจึงเผาผลาญประชากรของพระองค์

พระหัตถ์ของพระองค์เงื้อขึ้นและฟาดพวกเขา

ภูเขาทั้งหลายสะเทือนสะท้าน

ซากศพเหมือนกองขยะกลางถนน

ถึงขนาดนี้แล้วพระพิโรธของพระเจ้าก็ยังไม่หันเห

พระองค์ยังคงเงื้อพระหัตถ์ค้างอยู่

26พระองค์ทรงชูธงให้สัญญาณแก่ประชาชาติไกลโพ้นทั้งหลาย

ทรงผิวพระโอษฐ์เรียกบรรดาผู้ที่อยู่สุดปลายแผ่นดินโลก

พวกเขาโลดแล่นมาอย่างรวดเร็ว!

27ไม่มีสักคนที่อ่อนล้าหรือสะดุดล้ม

ไม่มีที่ซึมเซาหรือหลับใหล

เขาคาดเข็มขัดทะมัดทะแมง

สายรัดรองเท้าไม่ขาดสักเส้นเดียว

28ลูกศรของเขาคมกริบ

คันธนูของเขาโก่งไว้

กีบม้าของเขาเหมือนหินเหล็กไฟ

ล้อรถรบของเขาเหมือนพายุหมุน

29เสียงคำรามของเขาเหมือนราชสีห์

พวกเขาคำรามเหมือนสิงห์หนุ่ม

เขาส่งเสียงร้องขณะตะครุบเหยื่อ

และลากทึ้งไปโดยไม่มีใครช่วย

30ในวันนั้นพวกเขาจะคำรามเข้าใส่เหยื่อ

เหมือนเสียงทะเลคำรน

และเมื่อใครมองดูดินแดนนั้น

จะเห็นความมืดและความทุกข์โศก

แม้แต่แสงสว่างก็ถูกเมฆบดบังจนมืดมิด