ኢሳይያስ 5 – NASV & KLB

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 5:1-30

ስለ ወይን ቦታ የተነገረ ቅኔ

1ስለ ወዳጄ፣

ደግሞም ስለ ወይን ቦታው ልዘምር፤

ወዳጄ በለምለም ኰረብታ ላይ

የወይን ቦታ ነበረው።

2መሬቱን ቈፈረ፤ ድንጋይንም ለቅሞ አወጣ፤

ምርጥ የሆነውንም ወይን ተከለበት።

በመካከሉ መጠበቂያ ማማ ሠራ፤

የወይን መጭመቂያ ጕድጓድም አበጀ፤

ከዚያ መልካም ፍሬ ያፈራል ብሎ ዐሰበ፤

ነገር ግን ኮምጣጣ ፍሬ አፈራ።

3“እናንት በኢየሩሳሌም የምትኖሩና የይሁዳ ሰዎች ሆይ፤

በእኔና በወይኔ ቦታ መካከል እስቲ ፍረዱ።

4ከዚህ ካደረግሁለት በላይ ለወይኔ ቦታ ምን

ሊደረግለት ይገባ ነበር?

መልካም የወይን ፍሬ ያፈራል ብዬ

ስጠብቅ ለምን ኮምጣጣ ፍሬ አፈራ?

5እንግዲህ በወይኔ ቦታ

ምን እንደማደርግ ልንገራችሁ፤

ዐጥሩን እነቅላለሁ፤

ለጥፋት ይጋለጣል፤

ግንቡንም አፈርሳለሁ፣

መረጋገጫም ይሆናል።

6የማይኰተኰትና የማይታረም

ጠፍ መሬት አደርገዋለሁ፤

ኵርንችትና እሾኽም ይበቅልበታል፤

ዝናብም እንዳይዘንብበት

ደመናዎችን አዝዛለሁ።”

7የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔር

የወይን ቦታው የእስራኤል ቤት ነው፤

የይሁዳ ሰዎችም

የደስታው አትክልት ናቸው።

ፍትሕን ፈለገ፤ ነገር ግን ደም ማፍሰስን አየ፤

ጽድቅን ፈለገ፤ ነገር ግን የጭንቅን ጩኸት ሰማ።

ወዮታና ፍርድ

8ስፍራ ለሌሎች እስከማይተርፍ፣

ቤትን በቤት ላይ በመጨመር፣

መሬትን ከመሬት ጋር በማያያዝ፣

ለብቻችሁ በምድር ተስፋፍታችሁ ለምትኖሩ ወዮላችሁ

9የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ጆሮዬ እየሰማ እንዲህ ሲል ተናገረ፤

“ታላላቅ ቤቶች ወና ይቀራሉ፣

የሚያማምሩም ቤቶች ኗሪ ያጣሉ።

10ከሩብ ጋሻ5፥10 በዕብራይስጥ፣ ሩብ ጋሻ መሬት በዐሥር ጥማድ በሬ በአንድ ቀን የሚታረስ ነው። የወይን ቦታ አንድ የባዶስ መስፈሪያ ያህል የወይን ጭማቂ ብቻ ይገኛል፤ አንድ የቆሮስ መስፈሪያ ዘር ተዘርቶ አንድ የኢፍ መስፈሪያ እህል ብቻ ይሰጣል።”5፥10 ምናልባት አንድ ባዶስ ሀያ ሁለት ሊትር ያህል ነው። አንድ የቆሮስ መስፈሪያ መቶ ስድሳ ኪሎ ግራም ያህል ነው። አንድ የኢፍ መስፈሪያ ዐሥራ ስምንት ኪሎ ግራም ያህል ነው።

11የሚያሰክር መጠጥ ፍለጋ

ማልደው ለሚነሡ፣

እስኪያነድዳቸውም ወይን በመጠጣት

ሌሊቱን ለሚያነጉ ወዮላቸው!

12በግብዣቸው ላይ በገናና መሰንቆ፣

ከበሮና ዋሽንት እንዲሁም የወይን ጠጅ አለ፤

ነገር ግን ለእግዚአብሔር ሥራ ቦታ አልሰጡም፤

ለእጆቹም ሥራ ክብር አላሳዩም።

13ስለዚህ ሕዝቤ

ዕውቀት በማጣቱ ይማረካል፤

መኳንንቱም በራብ ይሞታሉ፤

ሕዝቡም በውሃ ጥም ይቃጠላል።

14ስለዚህ ሲኦል5፥14 በዕብራይስጡ፣ መቃብር ማለት ነው። ሆዷን አሰፋች፣

አፏንም ያለ ልክ ከፈተች፤

መኳንንቱና ሕዝቡ ከረብሸኞቻቸውና ከጨፋሪዎቻቸው ጋር

ወደዚያ ይወርዳሉ።

15ሰው ይዋረዳል፤

የሰው ልጅም ዝቅ ዝቅ ይላል፤

የእብሪተኛውም ዐይን ይሰበራል።

16የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ግን በፍትሕ ከፍ ከፍ ይላል፤

ቅዱሱም አምላክ ቅድስናውን በጽድቅ ይገልጻል።

17በጎችም በገዛ መሰማሪያቸው እንደሚሰማሩ ሆነው ይግጣሉ፤

የበግ ጠቦቶችም በባለጠጎች ፍርስራሽ ላይ ሣር ይበላሉ5፥17 በዕብራይስጡ፣ እንግዶች ይበሉታል ይለዋል።

18ኀጢአትን በማታለል ገመድ ለሚስቡ፣

በደልንም በሠረገላ ማሰሪያ ለሚጐትቱ ወዮላቸው!

19“በዐይናችን እንድናይ

እግዚአብሔር ይቸኵል፤

ሥራውንም ያፋጥን፤

የእስራኤልን ቅዱስ፣ የእርሱን ዕቅድ

እንድናውቃት ትቅረብ፤

ትምጣም” ለሚሉ ወዮላቸው!

20ክፉውን መልካም፣

መልካሙን ክፉ ለሚሉ

ብርሃኑን ጨለማ፣

ጨለማውን ብርሃን ለሚያደርጉ፣

ጣፋጩን መራራ፣

መራራውንም ጣፋጭ ለሚያደርጉ ወዮላቸው!

21ራሳቸውን እንደ ብልኅ ለሚቈጥሩ፣

በራሳቸውም አመለካከት ጥበበኛ ለሆኑ ወዮላቸው!

22የወይን ጠጅ ለመጠጣት ጀግኖች፣

የሚያሰክር መጠጥ ለመደባለቅ ብርቱ ለሆኑ ወዮላቸው!

23ጕቦን በመቀበል በደለኛን ንጹሕ ለሚያደርጉ፣

ለበደል አልባ ሰው ፍትሕን ለሚነፍጉ ወዮላቸው!

24ስለዚህ የእሳት ነበልባል ገለባን እንደሚበላ፣

ድርቆሽም በእሳት ጋይቶ እንደሚጠፋ፣

የእነርሱም ሥር እንዲሁ ይበሰብሳል፤

አበባቸውም እንደ ትቢያ ይበንናል፤

የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔርን ሕግ ንቀዋልና፤

የእስራኤል ቅዱስ የተናገረውንም ቃል አቃልለዋል።

25የእግዚአብሔር ቍጣ በሕዝቡ ላይ ነድዷል፤

እጁን አንሥቶ መትቷቸዋል፤

ተራሮች ራዱ፤

ሬሳዎችም በመንገድ ላይ እንደ ተጣለ ጥራጊ ሆኑ፤

ይህ ሁሉ ሆኖ ግን ቍጣው ገና አልተመለሰም፤

እጁም እንደ ተነሣ ነው።

26ከሩቅ ያሉትን ሕዝቦች የሚጠራበትን

ምልክት ያቆማል፤

ከምድር ዳርቻም በፉጨት ይጠራቸዋል፤

እነርሱም እየተጣደፉ በፍጥነት ይመጣሉ።

27በመካከላቸው ደካማና ስንኩል አይገኝም፤

የሚያንቀላፋና የሚተኛ አይኖርም፤

የወገባቸው መቀነት አይላላም፤

የጫማቸውም ማሰሪያ አይበጠስም።

28ፍላጻቸው የተሳለ፣

ቀስታቸውም የተደገነ ነው፤

የሠረገሎቻቸውም መንኰራኵሮች እንደ

ዐውሎ ነፋስ ናቸው።

29ጩኸታቸው እንደ አንበሳ ነው፤

እንደ አንበሳ ደቦል ያገሣሉ፤

ያደኑትንም ይዘው ይጮኻሉ፤

ተሸክመውት ይሄዳሉ፤ የሚያስጥልም የለም።

30በዚያን ቀን

እንደ ባሕር ሞገድ ይጮኹበታል፤

ማንም ወደ ምድር ቢመለከት፣

ጨለማንና መከራን ያያል፤

ብርሃን እንኳ በደመናዎች ይጋረዳል።

Korean Living Bible

이사야 5:1-30

포도원의 노래

1내가 사랑하는 자와

그의 포도원에 대하여 노래하리라.

내 사랑하는 자에게는

비옥한 야산에 포도원이 있어

2땅을 파서 돌을 없애고

제일 좋은 포도나무를 심었네.

그가 그 곳에 망대를 세우며

포도즙 짜는 틀을 만들어 놓고

좋은 포도가 맺히기를 기다렸으나

쓸모없는 포도가 맺혔구나.

3그래서 내 사랑하는 자가 말한다. “예루살렘과 유다에 사는 사람들아, 너희는 나와 내 포도원 사이를 심판하라.

4내가 내 포도원을 위해서 이 이상 더 어떻게 하란 말인가? 내가 좋은 포도를 기대했는데 어째서 쓸모없는 포도가 맺혔는가?

5이제 내가 내 포도원을 어떻게 해야 할지 너희에게 말하겠다. 내가 울타리를 헐어 내 포도원을 짐승에게 짓밟히는 풀밭이 되게 할 것이며

6내가 가지를 치거나 북을 돋우지 않고 찔레나 가시가 그대로 자라게 하여 황무지가 되게 할 것이며 내가 또 구름에게 비를 내리지 말라고 명령할 것이다.”

7이스라엘은 전능하신 여호와의 포도원이며 유다 사람은 그가 심은 포도나무이다. 여호와께서는 그들이 공정하고 옳은 일 하기를 바랐으나 그들은 살인을 일삼았으며, 여호와께서 선한 일을 기대하셨으나 고통당하는 자들의 부르짖는 소리뿐이었다.

임박한 재앙과 심판

8집과 땅을 계속 사들여 다른 사람이 살 공간도 남기지 않고 혼자 살려고 하는 사람에게 화가 있을 것이다.

9전능하신 여호와께서 나에게 이런 말씀을 들려 주셨다. “크고 호화로운 수많은 집들이 폐허가 되어 사람이 살지 않을 것이며

105:10 또는 ‘열흘갈이’약 40,000평방미터의 포도원에 포도주가 겨우 5:10 히 ‘한 바트’22리터밖에 나오지 않을 것이요 5:10 히 ‘한 호멜’한 말의 씨를 뿌려도 곡식은 5:10 히 ‘한 에바’한 되밖에 나오지 않을 것이다.”

11아침 일찍부터 일어나 독주를 따라 마시며 밤이 깊도록 술로 세월을 보내는 자에게 화가 있을 것이다.

12그들은 연회석에 수금과 비파와 소고와 피리, 그리고 술을 갖춰 놓았으나 여호와의 일에는 무관심하고 그가 하신 일은 생각지도 않는다.

13그러므로 내 백성은 무지 때문에 포로로 잡혀갈 것이며 그들의 지도자들은 굶어서 죽을 것이요 일반 백성은 목말라 죽을 것이다.

145:14 또는 ‘음부가’무덤이 입을 크게 벌려 예루살렘의 귀족들과 술로 흥청거리며 떠들어대는 많은 백성을 삼켜 버릴 것이다.

15천한 자도 귀한 자도 다 낮아지고 교만한 자도 낮아질 것이지만

16전능하신 여호와는 옳은 일을 행하심으로 그의 위대함을 보이시고 자기 백성을 심판하심으로 그의 거룩함을 나타내실 것이다.

17그 때에는 어린 양들이 폐허 가운데서 풀을 뜯어먹을 것이며 5:17 또는 ‘유리하는 자들이’이방인들이 황폐한 부자들의 땅에서 먹을 것이다.

18거짓의 줄로 죄를 끌고 다니며 수레처럼 악을 끌고 다니는 자에게 화가 있을 것이다.

19이들은 이스라엘의 거룩하신 분을 조롱하며 이렇게 말한다. “여호와여, 속히 우리를 벌하소서. 우리는 당신이 계획대로 일을 수행할 수 있는지 보고 싶습니다.”

20악을 선하다 하고 선을 악하다 하며, 어둠을 빛으로 바꾸고 빛을 어둠으로 바꾸며, 쓴 것을 달게 하고 단 것을 쓰게 하는 자들에게 화가 있을 것이다.

21스스로 지혜롭고 영리하다고 생각하는 자들에게 화가 있을 것이다.

22배짱 좋게 독주를 겁 없이 마구 퍼마시는 술고래들에게 화가 있을 것이다.

23그들은 뇌물을 받고 범죄한 사람을 놓아 주며 죄 없는 사람을 감옥에 가둔다.

24그러므로 지푸라기와 마른 풀이 불에 타서 소멸되듯이 그들의 뿌리가 썩고 꽃이 시들어 티끌처럼 날아가 버릴 것이다. 이것은 그들이 전능하신 여호와의 율법을 버리고 이스라엘의 거룩하신 하나님의 말씀을 무시하였기 때문이다.

25그러므로 여호와께서 자기 백성에게 분노하시고 손을 들어 그들을 치셨다. 산들이 진동하고 그들의 시체가 거리의 쓰레기처럼 버려져도 여호와의 분노는 그치지 않을 것이며 그 손도 거두지 않으실 것이다.

26그가 멀리 있는 나라들에게 신호를 보내 그들을 땅 끝에서부터 오게 하실 것이다. 그들이 예루살렘을 향해 돌진해 올 것이나

27그들 중에 피곤하여 넘어지는 자가 없고 조는 자나 자는 자도 없을 것이며 허리띠가 풀리거나 신발끈이 끊어진 자도 없을 것이다.

28그들의 화살은 날카롭고 활은 당겨진 채로 있으며 그들의 말굽은 부싯돌처럼 단단하고 그들의 전차 바퀴는 회오리바람 같을 것이다.

29그들이 무서운 소리를 지르며 사자가 먹이를 덮쳐 움켜가듯이 내 백성을 잡아 끌고 갈 것이나 그들을 구해 줄 자가 없을 것이다.

30그 날에 그들이 바다의 성난 파도처럼 이스라엘을 향해 소리를 지를 것이니 사람이 그 땅을 바라보면 슬픔과 고통뿐이요 빛은 구름에 가려 어두울 것이다.