ኢሳይያስ 49 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 49:1-26

የእግዚአብሔር ባሪያ

1እናንት ደሴቶች ስሙኝ፤

እናንት በሩቅ ያላችሁ ሕዝቦች ይህን አድምጡ፤

በእናቴ ማሕፀን ሳለሁ እግዚአብሔር ጠራኝ፤

ከመወለዴ በፊት በስም ጠራኝ።

2አፌን እንደ ተሳለ ሰይፍ አደረገው፤

በእጁ ጥላ ሰወረኝ፤

የተወለወለ ፍላጻ አደረገኝ፤

በሰገባውም ውስጥ ሸሸገኝ።

3እርሱም፣ “እስራኤል፤ አንተ ባሪያዬ ነህ፤

በአንተ ክብሬን እገልጣለሁ” አለኝ።

4እኔ ግን፣ “ዐላማ ሳይኖረኝ እንዲሁ ደከምሁ፤

ምንም ጥቅም ለሌለውና ለከንቱ ነገር ጕልበቴን ጨረስሁ፤

ሆኖም ግን ብድራቴ በእግዚአብሔር እጅ፣

ዋጋዬም በአምላኬ ዘንድ ነው” አልሁ።

5በእግዚአብሔር ዐይን ፊት ከብሬአለሁ፤

አምላኬ ጕልበት ሆኖልኛል፤

ባሪያው እንድሆን ከማሕፀን የሠራኝ፣

ያዕቆብን ወደ እርሱ እንድመልስ፣

እስራኤልን ወደ እርሱ እንድሰበስብ ያደረገኝ፣

እግዚአብሔር አሁንም እንዲህ ይላል፤

6እርሱም፣

“ባሪያዬ መሆንህ፣

የያዕቆብን ነገዶች እንደ ገና መመለስህ፣

የጠበቅኋቸውን እስራኤል መልሰህ ማምጣት ለአንተ ቀላል ነገር ነው፤

ድነቴን እስከ ምድር ዳርቻ እንድታመጣ፣

ለአሕዛብ ብርሃን አደርግሃለሁ” አለኝ።

7እግዚአብሔር

ታዳጊ የሆነው የእስራኤል ቅዱስ፣

ለተናቀውና በሕዝብ ለተጠላው፣

የገዦች አገልጋይ እንዲህ ይላል፤

“ነገሥታት አይተውህ ይነሣሉ፤

ልዑላንም አይተው፤ ይሰግዳሉ፤

ምክንያቱም የመረጠህ የእስራኤል ቅዱስ፣

እግዚአብሔር ታማኝ ነው።”

የእስራኤል እንደ ገና መቋቋም

8እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“በወደድሁ ጊዜ እመልስልሃለሁ፤

በድነትም ቀን እረዳሃለሁ።

ለሕዝቡ ቃል ኪዳን እንድትሆን፣

ምድሪቱን እንደ ገና እንድትሠራት፣

ጠፍ የሆኑትን ርስቶች ለየባለቤታቸው እንድትመልስ፣

እጠብቅሃለሁ፤ እሠራሃለሁም፤

9የተማረኩትን፣ ‘ኑ ውጡ’

በጨለማ ያሉትን፣ ‘ነጻ ሁኑ’ እንድትል አድርጌሃለሁ።

“በየመንገዱ ዳር ይመገባሉ፤

በተራቈተውም ኰረብታ ሁሉ ላይ መሰማሪያ ያገኛሉ።

10አይራቡም፤ አይጠሙም፤

የምድረ በዳ ትኵሳት ወይም የፀሓይ ቃጠሎ አይጐዳቸውም።

የሚራራላቸው ይመራቸዋል፤

በውሃ ምንጭ ዳርም ያሰማራቸዋል።

11ተራሮቼን ሁሉ መንገድ አደርጋለሁ፤

ጐዳናዎቼም ከፍ ይላሉ።

12እነሆ፤ ከሩቅ አገር ይመጣሉ፤

አንዳንዶች ከሰሜን ሌሎች ከምዕራብ፣

የቀሩት ደግሞ ከሲኒም49፥12 የማሶሬቱ ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማል፣ የሙት ባሕር ጥቅልሎች ግን፣ አስዋን ይላሉ። ይመጣሉ።”

13ሰማያት ሆይ፤ እልል በሉ፤

ምድር ሆይ፤ ደስ ይበልሽ፤

ተራሮች ሆይ፤ በደስታ ዘምሩ፤

እግዚአብሔር ሕዝቡን ያጽናናል፤

ለተቸገሩትም ይራራልና።

14ጽዮን ግን፣ “እግዚአብሔር ትቶኛል፤

ጌታም ረስቶኛል” አለች።

15“እናት የምታጠባውን ልጇን ልትረሳ ትችላለችን?

ለወለደችውስ ልጅ አትራራለትምን?

ምናልባት እርሷ ትረሳ ይሆናል፣

እኔ ግን አልረሳሽም።

16እነሆ፤ በእጄ መዳፍ ላይ ቀርጬሻለሁ፤

ቅጥሮችሽ ምንጊዜም በፊቴ ናቸው።

17ወንዶች ልጆችሽ ፈጥነው ይመለሳሉ፤

ያፈራረሱሽም ከአንቺ ይሸሻሉ።

18ዐይንሽን ቀና አድርጊ፤ ዙሪያውንም ተመልከቺ፤

ወንዶች ልጆችሽ ሁሉ ተሰብስበው ወደ አንቺ ይመጣሉ።

በሕያውነቴ እምላለሁ፤

እነዚህን ሁሉ እንደ ጌጥ ትለብሻቸዋለሽ፤

እንደ ሙሽራም ትጐናጸፊያቸዋለሽ” ይላል እግዚአብሔር

19“ፈራርሰሽ ባድማ ብትሆኚ፣

ምድርሽ ፈጽሞ ቢጠፋ፣

ዛሬ ለሕዝብሽ ጠባብ ብትሆኚም እንኳ፣

የዋጡሽ ከአንቺ ይርቃሉ።

20በሐዘንሽ ዘመን የወለድሻቸው ልጆች፣

ጆሮሽ እየሰማ፣

‘ይህ ቦታ በጣም ጠብቦናል፤

የምንኖርበት በቂ ስፍራ ስጪን’ ይሉሻል።

21በልብሽም እንዲህ ትያለሽ፣

‘እነዚህን የወለደልኝ ማን ነው?

እኔ ሐዘንተኛና መካን፣

የተሰደድሁና የተጠላሁ ነበርሁ፤

እነዚህን ማን አሳደጋቸው?

ብቻዬን ቀርቼ ነበር፤

ታዲያ፣ እነዚህ ከየት መጡ?’ ”

22ልዑል እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ አሕዛብን በጥቅሻ እጣራለሁ፤

ዐርማዬንም ለሕዝቦች ከፍ አደርጋለሁ፤

ወንዶች ልጆችሽን በዕቅፋቸው ያመጡልሻል፤

ሴቶች ልጆችሽንም በትከሻቸው ይሸከሙልሻል።

23ነገሥታት አሳዳጊ አባቶችሽ፣

እቴጌዎቻቸው ሞግዚቶችሽ ይሆናሉ፤

በግንባራቸው ተደፍተው ይሰግዱልሻል፤

የእግርሽን ትቢያ ይልሳሉ፤

አንቺም እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቂያለሽ፤

እኔን ተስፋ የሚያደርጉም አያፍሩም።”

24ከተዋጊ ብዝበዛ ማስጣል፣

ከጨካኝስ49፥24 የሙት ባሕር ጥቅሎች፣ ቩልጌትና የሱርስቱ ቅጅ (እንዲሁም የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም 25 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ የማሶሬቱ ቅጅ ግን፣ ከጻድቅስ ይላል። ምርኮኞችን ማዳን ይቻላልን?

25እግዚአብሔር ግን እንዲህ ይላል፤

“ከተዋጊዎች ላይ ምርኮኞች በርግጥ ይወሰዳሉ፤

ከጨካኞችም ላይ ምርኮ ይበዘበዛል፤

ከአንቺ ጋር የሚጣሉትን እጣላቸዋለሁ፤

ልጆችሽንም እታደጋለሁ።

26አስጨናቂዎችሽ የራሳቸውን ሥጋ እንዲበሉ አደርጋቸዋለሁ፤

በወይን ጠጅ እንደሚሰከር ሁሉ፣ በገዛ ደማቸው ይሰክራሉ።

ከዚያም የሰው ዘር ሁሉ፣

እኔ እግዚአብሔር አዳኝሽ፣

ታዳጊሽም የያዕቆብ ኀያል እንደ ሆንሁ ያውቃል።”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以賽亞書 49:1-26

主的僕人

1眾海島啊,聽我說!

遠方的眾民啊,要留心聽!

我還沒有出生,

耶和華就呼召我;

我還沒有離開母腹,

祂就點我的名。

2祂使我的口像利劍,

用祂的手護庇我;

祂使我成為磨亮的箭,

把我藏在祂的箭囊中。

3祂對我說:「以色列啊,

你是我的僕人,

我要藉著你彰顯我的榮耀。」

4但我說:「我虛耗精力,

徒勞無功。

然而,耶和華必公正地待我,

我的報酬在我的上帝那裡。」

5我在母腹之中,耶和華便塑造我做祂的僕人,

叫我領雅各歸向祂,

以色列人召集到祂那裡。

我在耶和華眼中是尊貴的,

我的上帝是我的力量。

6祂對我說:「我不僅要你做我的僕人,

去復興雅各的眾支派,

使以色列的餘民重歸故土,

我還要使你成為外族人的光,

好把我的救恩帶到地極。」

7以色列的救贖主和聖者——耶和華對受藐視、

被本國人憎恨、

遭官長奴役的那位說:

「因為揀選你的以色列的聖者耶和華是信實的,

君王必在你面前肅然起立,

首領必在你面前俯伏下拜。」

以色列的復興

8耶和華說:

「在悅納的時候,我應允了你;

在拯救的日子,我幫助了你。

我要保護你,

使你做我跟民眾立約的中保,

復興家園,

分配荒涼的產業。

9你要對被囚禁的人說,

『出來吧!』

要對暗牢中的人說,

『你們自由了。』

他們在路上必有吃的,

光禿的山嶺必有食物。

10他們不再饑渴,

也不再被熱風和烈日灼傷,

因為憐憫他們的那位必引導他們,

領他們到泉水邊。

11我要使我的群山變為通途,

修築我的大路。

12看啊,他們必從遠方來,

有的來自北方,有的來自西方,

還有的來自希尼49·12 希尼」可能指遙遠的東方或南方某地。。」

13諸天啊,要歡呼!

大地啊,要快樂!

群山啊,要歌唱!

因為耶和華必安慰祂的子民,

憐憫祂受苦的百姓。

14錫安說:「耶和華撇棄了我,

主把我忘了。」

15耶和華說:「母親豈能忘記自己吃奶的嬰兒,

不憐憫自己親生的孩子?

就算有母親忘記,

我也不會忘記你。

16看啊,我已經把你銘刻在我的手掌上,

你的牆垣在我的看顧之下。

17你的兒女必很快回來,

毀滅和破壞你的必離你而去。

18舉目四下看看吧,

你的兒女正聚集到你這裡。

我憑我的永恆起誓,

你必把他們作為飾物戴在身上,

如新娘一樣用他們妝扮自己。

這是耶和華說的。

19「你那曾經荒廢、淒涼、

遭到毀壞之地現在必容不下你的居民,

那些吞滅你的人必遠遠地離開你。

20你流亡期間所生的子女必在你耳邊說,

『這地方太小了,

再給我們一些地方住吧。』

21你會在心裡問,『我喪失了兒女、

不再生育、流亡在外、漂流不定,

誰給我生了這些兒女?

誰把他們養大?

我孤身一人,

他們是從哪裡來的?』」

22主耶和華說:

「我必向列國招手,

向萬民豎立我的旗幟,

他們必抱著你的兒子、

背著你的女兒回來。

23列王必做你的養父,

王后必做你的褓姆。

他們必向你俯伏下拜,

舔你腳上的塵土。

那時你便知道我是耶和華,

信靠我的必不致失望。」

24勇士搶去的能奪回來嗎?

暴君擄走的能救回來嗎?

25但耶和華說:

「勇士擄去的必被奪回,

暴君搶去的必被救出。

我必與你的敵人爭戰,

拯救你的兒女。

26我要使那些欺壓你的人吞吃自己的肉,

喝自己的血喝得酩酊大醉,

好像喝酒一樣。

那時候,世人都必知道我耶和華是你的救主,

是你的救贖主,

雅各的大能者。」