ኢሳይያስ 48 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 48:1-22

እልኸኛዪቱ እስራኤል

1“የያዕቆብ ቤት ሆይ፤

እናንት በእስራኤል ስም የተጠራችሁ፣

ከይሁዳ ዘር የተገኛችሁ፣

እናንት በእግዚአብሔር ስም የምትምሉ፣

በእውነት ወይም በጽድቅ ሳይሆን፣

የእስራኤልን አምላክ የምትጠሩ ይህን ስሙ!

2እናንት የቅድስቲቱ ከተማ ነዋሪዎች ነን ብላችሁ ራሳችሁን የምትጠሩ፣

በእስራኤል አምላክ የምትታመኑ፣

ስሙ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር የሆነው የሚለውን አድምጡ፤

3የቀደሙትን ነገሮች ከብዙ ዘመን በፊት ተናግሬአለሁ፤

ከአፌ ወጥተዋል፤ እንዲታወቁም አድርጌአለሁ፤

እኔም ድንገት ሠራሁ፤ እነርሱም ተፈጸሙ።

4የቱን ያህል እልኸኛ እንደ ነበርህ ዐውቃለሁና፤

የዐንገትህ ጅማት ብረት፣

ግንባርህም ናስ ነበር።

5ስለዚህ እነዚህን ነገሮች ገና ድሮ ነገርሁህ፤

ከመፈጸማቸው በፊት አስታወቅሁህ፤ ይህም፣

‘ጣዖቶቼ ይህን አደረጉ፤

ከዕንጨት የተቀረጸው ምስልና ከብረት የተሠራው አምላኬ ይህን ወስኗል’

እንዳትል ነው።

6እነዚህን ነገሮች ሰምተሃል፤ ሁሉንም ተመልከታቸው፤

ራስህ ትክክለኛነታቸውን አትመሰክርምን?

“ከአሁን ጀምሮ አዳዲስ ነገሮችን፣

የተሰወሩብህን ያላወቅሃቸውን ነገሮች እነግርሃለሁ።

7እነርሱም የተፈጠሩት አሁን እንጂ ጥንት አይደለም፤

ስለ እነርሱም ከዛሬ በፊት አልሰማህም።

ስለዚህ፣ ‘አዎን፤ ስለ እነርሱ ዐውቃለሁ’

ማለት አትችልም።

8አልሰማህም ወይም አላውቅህም፤

ጆሮህ ከጥንት የተከፈተ አልነበረም፤

አንተ አታላይ እንደ ነበርህ፣

ከልጅነትህ ጀምሮ ዐመፀኛ መባልህን ዐውቄአለሁና።

9ስለ ስሜ ስል ቍጣዬን አዘገያለሁ፤

ስለ ምስጋናዬም ስል ከአንተ እገታዋለሁ፤

ይኸውም እንዳልቈርጥህ ነው።

10እነሆ፤ እንደ ብር ባይሆንም አንጥሬሃለሁ፤

በመከራ እቶን ፈትኜሃለሁ።

11ስለ ራሴ፣ ስለ ራሴ ስል አደርጋለሁ፤

ራሴን ለውርደት እንዴት አሳልፌ እሰጣለሁ?

ክብሬን ለማንም አልሰጥም።

እስራኤል ነጻ ሆነች

12“ያዕቆብ ሆይ፤

የጠራሁህ እስራኤል ሆይ፤ ስማኝ፤

እኔ እኔው ነኝ፤

ፊተኛው እኔ ነኝ፤ ኋለኛውም እኔ ነኝ።

13ምድርን የመሠረተች የእኔው እጅ ናት፤

ሰማያትን የዘረጋችም ቀኝ እጄ ናት፤

በምጠራቸው ጊዜ፣

ሁሉም በአንድነት ይቆማሉ።

14“ሁላችሁም በአንድነት ተሰብሰቡ፤ አድምጡም፤

ከጣዖቶች አስቀድሞ እነዚህን የተናገረ ማን ነው?

የእግዚአብሔር ምርጥ ወዳጅ የሆነ፣

እርሱ በባቢሎን48፥14 ወይም በዚህና በ14 ላይ ከለዳውያን ላይ ያቀደውን እንዲፈጽም ያደርገዋል፤

ክንዱም በባቢሎናውያን ላይ ይሆናል።

15እኔ፣ እኔው ራሴ ተናግሬአለሁ፤

በርግጥ እኔ ጠርቼዋለሁ፤

አመጣዋለሁ፤

ሥራውም ይከናወንለታል።

16“ወደ እኔ ቅረቡ፤ ይህን ስሙ፤

“ከመጀመሪያ ጀምሮ በስውር አልተናገርሁም፤

ሲፈጸምም እኔ እዚያው ነበርሁ።”

አሁንም ጌታ እግዚአብሔርና መንፈሱ

ልከውኛል።

17የተቤዠህ፣ የእስራኤል ቅዱስ፣

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እኔ እግዚአብሔር አምላክህ፣

የሚበጅህ ምን እንደ ሆነ የማስተምርህ፣

መሄድ በሚገባህ መንገድ የምመራህ ነኝ።

18ትእዛዜን ሰምተህ ብቻ ቢሆን ኖሮ፣

ሰላምህ እንደ ወንዝ፣

ጽድቅህም እንደ ባሕር ሞገድ በሆነ ነበር።

19ዘርህ እንደ አሸዋ፣

ልጆችህ ስፍር እንደሌለው ትቢያ በሆኑ ነበር፤

ስማቸው አይወገድም፤

ከፊቴም አይጠፋም።”

20ከባቢሎን ውጡ፣

ከባቢሎናውያንም ሽሹ!

ይህን በእልልታ አስታውቁ፤ ዐውጁት፤

እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ተናገሩ፤

እግዚአብሔር ባሪያውን ያዕቆብን

ተቤዥቶታል” በሉ።

21በምድረ በዳ ሲመራቸው አልተጠሙም ነበር፤

ውሃ ከዐለት አፈለቀላቸው፤

ዐለቱን ሰነጠቀ፤

ውሃውም በኀይል ፈልቆ ወጣ።

22“ለክፉዎች ሰላም የላቸውም” ይላል እግዚአብሔር

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以賽亞書 48:1-22

頑梗的以色列

1雅各家啊,聽我說!

你們被稱為以色列人,是猶大的子孫,

憑耶和華的名起誓、

呼求以色列的上帝,

卻不真心誠意。

2你們還自稱為聖城的人,

聲稱倚靠名為萬軍之耶和華的以色列的上帝。

3「過去所發生的事,

我很久以前就預言過、

親口宣告過,

然後使它們瞬間發生。

4我知道你頑梗,

有鐵一般的頸項,

銅一般的額頭。

5所以,在很久以前,

事情還沒有發生時就向你預言這些事,

免得你說這些是你的偶像做的,

是你雕刻和鑄造的偶像命定的。

6「你已經聽見了,看看這一切,

難道你還不承認嗎?

現在我要把新事,把你不知道的隱秘事告訴你。

7這些事過去沒有,現在才有,

在今天以前你從未聽過,

免得你說,『這些事我早就知道了。』

8你不知道這些事,

甚至聞所未聞。

我知道你生性詭詐,

你自出母胎就被稱為悖逆之徒。

9「我為了我的名,暫時忍怒;

我為了我的榮耀,壓住怒氣,

不消滅你。

10看啊,我熬煉你,但不像在火爐中煉銀子,

我是在苦難的爐中熬煉你。

11我這樣做是為了自己,

我豈能讓自己的名受褻瀆,

把自己的榮耀給別人?

12雅各,我所揀選的以色列啊,

聽我說!

我是上帝,我是首先的,

也是末後的。

13我親手奠立大地的根基,

我的右手鋪展穹蒼。

我一呼喚,它們都侍立一旁。

14「你們一起來聽吧。

假神中有誰曾預言過這些事?

耶和華所揀選的人必成就祂的旨意,

他的臂膀必攻擊迦勒底人。

15唯有我說過這些事;

我召了他,領他出來;

他必一路亨通。

16你們到我跟前來聽吧。

我一開始就沒有暗地裡說話,

事情發生的時候,我就在場。」

現在主耶和華差遣我和祂的靈來。

17你的救贖主耶和華——以色列的聖者說:

「我是你的上帝耶和華,

我為了使你受益而教導你,

我引導你走當行的路。

18真希望你當時肯聽我的命令!

那樣,你的平安必像滾滾河水,

你的公義必如滔滔海浪;

19你的後裔必多如海沙,

你的子孫必像細沙一樣不可勝數,

他們的名號絕不會從我面前被剷除、被消滅。」

20你們要離開巴比倫

迦勒底人那裡逃出來。

你們要高聲歡呼,向普天下傳揚、宣告:

「耶和華救贖了祂的僕人雅各!」

21耶和華帶領他們經過沙漠,

他們也不會口渴。

為了他們,

祂使水從磐石中流出,祂使磐石裂開、湧出水來。

22耶和華說:「惡人得不到平安。」