ኢሳይያስ 47 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 47:1-15

የባቢሎን ውድቀት

1“አንቺ የባቢሎን47፥1 ወይም በዚህና በ5 ላይ ከለዳውያን ድንግል ልጅ ሆይ፤

ውረጂ፤ በትቢያ ላይ ተቀመጪ፤

አንቺ የባቢሎናውያን ልጅ ሆይ፤

ከዙፋንሽ ውረጂ፤ መሬት ላይ ተቀመጪ፤

ከእንግዲህ ውብ ወይም ለግላጋ፣

ተብለሽ አትጠሪም።

2ወፍጮ ወስደሽ እህል ፍጪ፤

መሸፋፈኛሽን አውልቂ፤

ቀሚስሽንም ከፍ ከፍ አድርጊ፤ ባትሽን ግለጪ፤

እየተንገዳገድሽ ወንዙን ተሻገሪ።

3ዕርቃንሽ ይገለጥ፤

ኀፍረትሽ ይታይ፤

እበቀላለሁ፤

እኔ ማንንም አልተውም።”

4የሚቤዠን የእስራኤል ቅዱስ፣

ስሙ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው።

5“አንቺ የባቢሎናውያን ልጅ ሆይ፤

ወደ ጨለማ ግቢ፤ ዝም ብለሽም ተቀመጪ፤

ከእንግዲህ የመንግሥታት እመቤት

ተብለሽ አትጠሪም።

6ሕዝቤን ተቈጥቼ ነበር፤

ርስቴን አርክሼው ነበር፤

አሳልፌ በእጅሽ ሰጠኋቸው፤

አንቺ ግን አልራራሽላቸውም፤

በዕድሜ በገፉት ላይ እንኳ፣

እጅግ ከባድ ቀንበር ጫንሽባቸው።

7አንቺም፣ ‘እስከ መጨረሻው፣

ለዘላለም ንግሥት እሆናለሁ!’ አልሽ፤

ሆኖም እነዚህን ነገሮች አላስተዋልሽም፤

ፍጻሜያቸው ምን እንደሚሆንም አላሰብሽም።

8“አሁንም አንቺ ቅምጥል ፍጡር፣

በራስሽ ተማምነሽ የምትቀመጪ፣

በልብሽም፣

‘እኔ ነኝ፣ ከእኔ በቀር ሌላ የለም፤

ከእንግዲህ መበለት አልሆንም፤

የወላድ መካንም አልሆንም’ የምትይ ስሚ!

9እነዚህ ሁለት ነገሮች፣

መበለትነትና የወላድ መካንነት፣

አንድ ቀን ድንገት ይመጡብሻል፤

የቱን ያህል አስማት፣

የቱንም ያህል መተት ቢኖርሽ፣

በሙሉ ኀይላቸው ይመጡብሻል።

10በክፋትሽ ተማምነሽ፣

‘ማንም አያየኝም’ አልሽ፤

ደግሞም፣ ‘እኔ ነኝ፣ ከእኔ በቀር ሌላ የለም’

ባልሽ ጊዜ፣

ጥበብሽና ዕውቀትሽ አሳሳቱሽ።

11ጥፋት ይመጣብሻል፤

ነገር ግን በአስማትሽ እንዴት እንደምታርቂው አታውቂም፤

ወጆ ከፍለሽ ለማስወገድ የማትችዪው፣

ጕዳት ይወድቅብሻል፤

ያላሰብሽው አደጋ፣

ድንገት ይደርስብሻል።

12“በይ እንግዲህ፣ ከልጅነትሽ ጀምሮ የደከምሽባቸውን፣

አስማቶችሽን፣

ብዙ መተቶችን ቀጥዪባቸው፤

ምናልባት ይሳካልሽ፣

ምናልባትም ጠላቶችሽን ታሸብሪባቸው ይሆናል።

13የተቀበልሽው ምክር ሁሉ ድካም ብቻ ሆኖ አስቀርቶሻል፤

እነዚያ ከወር እስከ ወር ከዋክብትን አንጋጦ በማየት የሚተነብዩ፣

ኮከብ ቈጣሪዎች እስቲ ይምጡ፤

ከሚደርስብሽም ነገር እስቲ ያድኑሽ።

14እነሆ፣ እነርሱ ገለባ ናቸው፤

እሳት ይበላቸዋል፤

ከነበልባሉ ወላፈን የተነሣ፣

ራሳቸውን ማዳን አይችሉም።

ሰው የሚሞቀው ፍም አይኖርም፤

ተቀምጠው የሚሞቁትም እሳት የለም።

15ከልጅነት ጀምሮ አብረሻቸው የደከምሽው፣

አብረሽ የተገበያየሻቸው፣

ሊያደርጉ የሚችሉት ይህንኑ ብቻ ነው።

እያንዳንዱ በስሕተቱ ይገፋበታል፤

አንቺን ግን የሚያድን የለም።

New International Version – UK

Isaiah 47:1-15

The fall of Babylon

1‘Go down, sit in the dust,

Virgin Daughter Babylon;

sit on the ground without a throne,

queen city of the Babylonians.47:1 Or Chaldeans; also in verse 5

No more will you be called

tender or delicate.

2Take millstones and grind flour;

take off your veil.

Lift up your skirts, bare your legs,

and wade through the streams.

3Your nakedness will be exposed

and your shame uncovered.

I will take vengeance;

I will spare no-one.’

4Our Redeemer – the Lord Almighty is his name –

is the Holy One of Israel.

5‘Sit in silence, go into darkness,

queen city of the Babylonians;

no more will you be called

queen of kingdoms.

6I was angry with my people

and desecrated my inheritance;

I gave them into your hand,

and you showed them no mercy.

Even on the aged

you laid a very heavy yoke.

7You said, “I am for ever –

the eternal queen!”

But you did not consider these things

or reflect on what might happen.

8‘Now then, listen, you lover of pleasure,

lounging in your security

and saying to yourself,

“I am, and there is none besides me.

I will never be a widow

or suffer the loss of children.”

9Both of these will overtake you

in a moment, on a single day:

loss of children and widowhood.

They will come upon you in full measure,

in spite of your many sorceries

and all your potent spells.

10You have trusted in your wickedness

and have said, “No-one sees me.”

Your wisdom and knowledge mislead you

when you say to yourself,

“I am, and there is none besides me.”

11Disaster will come upon you,

and you will not know how to conjure it away.

A calamity will fall upon you

that you cannot ward off with a ransom;

a catastrophe you cannot foresee

will suddenly come upon you.

12‘Keep on, then, with your magic spells

and with your many sorceries,

which you have laboured at since childhood.

Perhaps you will succeed,

perhaps you will cause terror.

13All the counsel you have received has only worn you out!

Let your astrologers come forward,

those stargazers who make predictions month by month,

let them save you from what is coming upon you.

14Surely they are like stubble;

the fire will burn them up.

They cannot even save themselves

from the power of the flame.

These are not coals for warmth;

this is not a fire to sit by.

15That is all they are to you –

these you have dealt with

and laboured with since childhood.

All of them go on in their error;

there is not one that can save you.