ኢሳይያስ 47 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 47:1-15

የባቢሎን ውድቀት

1“አንቺ የባቢሎን47፥1 ወይም በዚህና በ5 ላይ ከለዳውያን ድንግል ልጅ ሆይ፤

ውረጂ፤ በትቢያ ላይ ተቀመጪ፤

አንቺ የባቢሎናውያን ልጅ ሆይ፤

ከዙፋንሽ ውረጂ፤ መሬት ላይ ተቀመጪ፤

ከእንግዲህ ውብ ወይም ለግላጋ፣

ተብለሽ አትጠሪም።

2ወፍጮ ወስደሽ እህል ፍጪ፤

መሸፋፈኛሽን አውልቂ፤

ቀሚስሽንም ከፍ ከፍ አድርጊ፤ ባትሽን ግለጪ፤

እየተንገዳገድሽ ወንዙን ተሻገሪ።

3ዕርቃንሽ ይገለጥ፤

ኀፍረትሽ ይታይ፤

እበቀላለሁ፤

እኔ ማንንም አልተውም።”

4የሚቤዠን የእስራኤል ቅዱስ፣

ስሙ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው።

5“አንቺ የባቢሎናውያን ልጅ ሆይ፤

ወደ ጨለማ ግቢ፤ ዝም ብለሽም ተቀመጪ፤

ከእንግዲህ የመንግሥታት እመቤት

ተብለሽ አትጠሪም።

6ሕዝቤን ተቈጥቼ ነበር፤

ርስቴን አርክሼው ነበር፤

አሳልፌ በእጅሽ ሰጠኋቸው፤

አንቺ ግን አልራራሽላቸውም፤

በዕድሜ በገፉት ላይ እንኳ፣

እጅግ ከባድ ቀንበር ጫንሽባቸው።

7አንቺም፣ ‘እስከ መጨረሻው፣

ለዘላለም ንግሥት እሆናለሁ!’ አልሽ፤

ሆኖም እነዚህን ነገሮች አላስተዋልሽም፤

ፍጻሜያቸው ምን እንደሚሆንም አላሰብሽም።

8“አሁንም አንቺ ቅምጥል ፍጡር፣

በራስሽ ተማምነሽ የምትቀመጪ፣

በልብሽም፣

‘እኔ ነኝ፣ ከእኔ በቀር ሌላ የለም፤

ከእንግዲህ መበለት አልሆንም፤

የወላድ መካንም አልሆንም’ የምትይ ስሚ!

9እነዚህ ሁለት ነገሮች፣

መበለትነትና የወላድ መካንነት፣

አንድ ቀን ድንገት ይመጡብሻል፤

የቱን ያህል አስማት፣

የቱንም ያህል መተት ቢኖርሽ፣

በሙሉ ኀይላቸው ይመጡብሻል።

10በክፋትሽ ተማምነሽ፣

‘ማንም አያየኝም’ አልሽ፤

ደግሞም፣ ‘እኔ ነኝ፣ ከእኔ በቀር ሌላ የለም’

ባልሽ ጊዜ፣

ጥበብሽና ዕውቀትሽ አሳሳቱሽ።

11ጥፋት ይመጣብሻል፤

ነገር ግን በአስማትሽ እንዴት እንደምታርቂው አታውቂም፤

ወጆ ከፍለሽ ለማስወገድ የማትችዪው፣

ጕዳት ይወድቅብሻል፤

ያላሰብሽው አደጋ፣

ድንገት ይደርስብሻል።

12“በይ እንግዲህ፣ ከልጅነትሽ ጀምሮ የደከምሽባቸውን፣

አስማቶችሽን፣

ብዙ መተቶችን ቀጥዪባቸው፤

ምናልባት ይሳካልሽ፣

ምናልባትም ጠላቶችሽን ታሸብሪባቸው ይሆናል።

13የተቀበልሽው ምክር ሁሉ ድካም ብቻ ሆኖ አስቀርቶሻል፤

እነዚያ ከወር እስከ ወር ከዋክብትን አንጋጦ በማየት የሚተነብዩ፣

ኮከብ ቈጣሪዎች እስቲ ይምጡ፤

ከሚደርስብሽም ነገር እስቲ ያድኑሽ።

14እነሆ፣ እነርሱ ገለባ ናቸው፤

እሳት ይበላቸዋል፤

ከነበልባሉ ወላፈን የተነሣ፣

ራሳቸውን ማዳን አይችሉም።

ሰው የሚሞቀው ፍም አይኖርም፤

ተቀምጠው የሚሞቁትም እሳት የለም።

15ከልጅነት ጀምሮ አብረሻቸው የደከምሽው፣

አብረሽ የተገበያየሻቸው፣

ሊያደርጉ የሚችሉት ይህንኑ ብቻ ነው።

እያንዳንዱ በስሕተቱ ይገፋበታል፤

አንቺን ግን የሚያድን የለም።

Ketab El Hayat

إشعياء 47:1-15

سقوط بابل

1انْزِلِي وَاجْلِسِي عَلَى التُّرَابِ أَيَّتُهَا الْعَذْرَاءُ ابْنَةُ بَابِلَ. اجْلِسِي عَلَى الأَرْضِ لَا عَلَى الْعَرْشِ يَا ابْنَةَ الْكَلْدَانِيِّينَ، لأَنَّكِ لَنْ تُدْعَيْ مِنْ بَعْدُ النَّاعِمَةَ الْمُتَرَفِّهَةَ. 2خُذِي حَجَرَيِ الرَّحَى وَاطْحَنِي الدَّقِيقَ. اكْشِفِي نِقَابَكِ، وَشَمِّرِي عَنِ الذَّيْلِ، وَاكْشِفِي عَنِ السَّاقِ، وَاعْبُرِي الأَنْهَارَ، 3فَيَظَلَّ عُرْيُكِ مَكْشُوفاً وَعَارُكِ ظَاهِراً، فَإِنِّي أَنْتَقِمُ وَلا أَعْفُو عَنْ أَحَدٍ. 4إِنَّ فَادِينَا، الرَّبَّ الْقَدِيرَ اسْمُهُ، هُوَ قُدُّوسُ إِسْرَائِيلَ. 5اجْلِسِي صَامِتَةً وَأَوْغِلِي فِي الظَّلامِ يَا ابْنَةَ الْكَلْدَانِيِّينَ، لأَنَّكِ لَنْ تُدْعَيْ بَعْدُ سَيِّدَةَ الْمَمَالِكِ.

6قَدْ سَخِطْتُ عَلَى شَعْبِي وَنَجَّسْتُ مِيرَاثِي. أَسْلَمْتُهُمْ إِلَى يَدَيْكِ، فَلَمْ تُبْدِي نَحْوَهُمْ رَحْمَةً بَلْ أَرْهَقْتِ الشَّيْخَ بِنِيرِكِ الثَّقِيلِ جِدّاً. 7وَقُلْتِ: سَأَظَلُّ السَّيِّدَةَ إِلَى الأَبَدِ. لِذَلِكَ لَمْ تُفَكِّرِي بِهَذِهِ الأُمُورِ فِي نَفْسِكِ وَلا تَأَمَّلْتِ بِمَا تَؤُولُ إِلَيْهِ. 8فَالآنَ اسْمَعِي هَذَا أَيَّتُهَا الْمُتَرَفِّهَةُ الْمُتَنَعِّمَةُ الْمُطْمَئِنَّةُ، الْقَائِلَةُ فِي قَلْبِهَا: أَنَا وَحْدِي وَلَيْسَ هُنَاكَ غَيْرِي، لَنْ أَعْرِفَ التَّرَمُّلَ وَلَنْ أُثْكَلَ 9لِذَلِكَ سَتُبْتَلِينَ بِكِلا الأَمْرَيْنِ مَعاً فِي لَحْظَةٍ، فِي يَوْمٍ وَاحِدٍ، إِذْ تُثْكَلِينَ وَتَتَرَمَّلِينَ حَتَّى النِّهَايَةِ عَلَى الرَّغْمِ مِنْ كَثْرَةِ سِحْرِكِ وَقُوَّةِ رُقَاكِ. 10قَدْ تَوَلَّتْكِ طُمَأْنِينَةٌ فِي شَرِّكِ، وَقُلْتِ: لَا يَرَانِي أَحَدٌ وَلَكِنَّ حِكْمَتَكِ وَمَعْرِفَتَكِ أَضَلَّتَاكِ، فَقُلْتِ فِي نَفْسِكِ: أَنَا وَحْدِي، وَلَيْسَ هُنَاكَ غَيْرِي. 11سَيَدْهَمُكِ شَرٌّ لَا تَدْرِينَ كَيْفَ تَدْفَعِينَهُ عَنْكِ، وَتُبَاغِتُكِ دَاهِيَةٌ تَعْجَزِينَ عَنِ التَّكْفِيرِ عَنْهَا، وَيُفَاجِئُكِ خَرَابٌ لَا تَتَوَقَّعِينَهُ.

12تَشَبَّثِي بِرُقَاكِ وَكَثْرَةِ سِحْرِكِ الَّتِي تَعِبْتِ فِيهَا مُنْذُ صِبَاكِ، فَقَدْ يُحَالِفُكِ النَّجَاحُ أَوْ تُثِيرِينَ الرُّعْبَ. 13لَقَدْ ضَعُفْتِ مِنْ كَثْرَةِ طَلَبِ الْمَشُورَةِ، فَادْعِي الْمُنَجِّمِينَ وَالْفَلَكِيِّينَ لِيَكْشِفُوا لَكِ طَوَالِعَ الْمُسْتَقْبَلِ وَيُنْقِذُوكِ مِمَّا يَأْتِي عَلَيْكِ. 14غَيْرَ أَنَّهُمْ أَنْفُسَهُمْ أَصْبَحُوا كَالهَشِيمِ الَّذِي تَلْتَهِمُهُ النَّارُ عَاجِزِينَ عَنْ إِنْقَاذِ أَنْفُسِهِمْ وَإِنْقَاذِكِ مِنْ شِدَّةِ الَّلَهَبِ المُحْرِقِ، فَلا هُوَ جَمْرٌ لِلاسْتِدْفَاءِ وَلا هِيَ نَارٌ لِلْجُلُوسِ حَوْلَهَا. 15هَكَذَا يَجْرِي عَلَى الَّذِينَ تَعِبْتِ فِيهِمْ وَتَاجَرُوا مَعَكِ مُنْذُ صِبَاكِ، قَدْ شَرَدَ كُلٌّ مِنْهُمْ فِي طَرِيقِهِ وَلَيْسَ مَنْ يُنْقِذُكِ.