ኢሳይያስ 43 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 43:1-28

የእስራኤል ብቸኛ አዳኝ

1አሁን ግን፣ ያዕቆብ ሆይ! የፈጠረህ፣

እስራኤል ሆይ! የሠራህ፣

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ተቤዥቼሃለሁና አትፍራ፤

በስምህ ጠርቼሃለሁ፤ አንተ የእኔ ነህ፤

2በውሃ ውስጥ በምታልፍበት ጊዜ፣

ከአንተ ጋር እሆናለሁ፤

ወንዙን ስትሻገረው፣

አያሰጥምህም፤

በእሳት ውስጥ ስትሄድ፣

አያቃጥልህም፤

ነበልባሉም አይፈጅህም።

3እኔ እግዚአብሔር አምላክህ፣

የእስራኤልም ቅዱስ መድኀኒትህ ነኝና፤

ግብፅን ለአንተ ቤዛ እንድትሆን፣

ኢትዮጵያንና ሳባን በአንተ ፈንታ እሰጣለሁ።

4ለዐይኔ ብርቅና ክቡርም ስለ ሆንህ፣

እኔም ስለምወድድህ፣

ሰዎችን በአንተ ምትክ፣

ሕዝቦችንም በሕይወትህ ፈንታ እሰጣለሁ።

5ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤

ልጆችህን ከምሥራቅ አመጣለሁ፤

ከምዕራብም እሰበስብሃለሁ።

6ሰሜንን፣ ‘አምጣ’፣

ደቡብንም፣ ‘ልቀቅ’ እላለሁ፤

ወንዶች ልጆቼን ከሩቅ፣

ሴቶች ልጆቼንም ከምድር ዳርቻ፣

7በስሜ የተጠራውን ሁሉ፣

ለክብሬ የፈጠርሁትን፣

ያበጀሁትንና የሠራሁትን አምጡ።”

8ዐይን እያላቸው የታወሩትን፣

ጆሮ እያላቸው የደነቈሩትን አውጣ።

9ሕዝብ ሁሉ በአንድነት ይሰብሰብ፤

ሰውም ይከማች፤

ከእነርሱ አስቀድሞ ይህን የነገረን፣

የቀድሞውን ነገር ያወጀልን ማን ነው?

ሌሎችን ሰምተው፣ “እውነት ነው” እንዲሉ፣

ትክክለኝነታቸውም እንዲረጋገጥ ምስክሮቻቸውን ያቅርቡ።

10“ታውቁና ታምኑብኝ ዘንድ፣

እርሱ እኔ እንደ ሆንሁ ትረዱ ዘንድ፣

እናንተ ምስክሮቼ፣

የመረጥሁትም ባሪያዬ ናችሁ” ይላል እግዚአብሔር

“ከእኔ በፊት አምላክ አልተሠራም፤

ከእኔም በኋላ አይኖርም።

11እኔ፣ እኔ እግዚአብሔር ነኝ፤

ከእኔም ሌላ የሚያድን የለም።

12ገልጫለሁ፤ አድኛለሁ፤ ተናግሬአለሁ፤

በመካከላችሁ እኔ እንጂ ባዕድ አምላክ አልነበረም።

እኔ አምላክ እንደ ሆንሁ፣ እናንተ ምስክሮቼ ናችሁ” ይላል እግዚአብሔር

13“ከጥንት ጀምሮ እኔው ነኝ፤

ከእጄም ማውጣት የሚችል የለም፤

እኔ የምሠራውን ማን ማገድ ይችላል?”

የእግዚአብሔር ምሕረትና የእስራኤል አለመታመን

14የእስራኤል ቅዱስ፣

የሚቤዣችሁ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ እናንተ በባቢሎን43፥14 ወይም፣ ከለዳውያን ማለት ነው። ላይ ሰራዊት እሰድዳለሁ፤

በሚመኩባቸውም መርከቦች፣

ባቢሎናውያንን ሁሉ እንደ ኰብላይ አመጣለሁ።

15እኔ እግዚአብሔር፣ የእናንተ ቅዱስ፣

የእስራኤል ፈጣሪ፣ ንጉሣችሁ ነኝ።”

16በባሕር ውስጥ መንገድ፣

በማዕበል ውስጥ መተላለፊያ ያበጀ፣

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

17እንደ ገና ላይነሡ እዚያው እንዲተኙ፣

እንደ ጧፍ ኵስታሪ ረግፈው እንዲጠፉ፣

ሠረገሎችንና ፈረሶችን፣

ሰራዊቱንና ደጀኑን በአንድነት ያወጣ እንዲህ ይላል፤

18“የቀደመውን ነገር አታስቡ፤

ያለፈውን እርሱ።

19እነሆ፤ አዲስ ነገር አደርጋለሁ፤

እርሱም አሁን ይበቅላል፤ አታስተውሉትምን?

በምድረ በዳም መንገድ አዘጋጃለሁ፤

በበረሓም ምንጭ አፈልቃለሁ፤

20የምድረ በዳ አራዊት፣

ቀበሮና ጕጕት ያከብሩኛል፤

በምድረ በዳ ውሃ፣

በበረሓም ምንጭ እሰጣለሁና።

ለመረጥሁት ሕዝቤ ውሃ እሰጣለሁ፤

21ለራሴ ያበጀሁት ሕዝብ

ምስጋናዬን ያውጅ ዘንድ ይህን አደርጋለሁ።

22“ያዕቆብ ሆይ፤ አንተ ግን አልጠራኸኝም፤

እስራኤል ሆይ፤ የእኔ ነገር ታክቶሃል።

23ለሚቃጠል መሥዋዕት በጎች አላመጣህልኝም፤

በመሥዋዕትህም አላከበርኸኝም።

በእህል ቍርባን አላስቸገርሁህም፤

በዕጣን መሥዋዕትም አላሰለቸሁህም።

24መልካም መዐዛ ያለው ዕጣን አልገዛህልኝም፤

በመሥዋዕትህ ሥብ አላጠገብኸኝም፤

ነገር ግን የኀጢአት ሸክምህን ጫንህብኝ፤

በበደልህም አደከምኸኝ።

25“ስለ ራሴ ስል መተላለፍህን የምደመስስልህ፣

እኔ፣ እኔው ነኝ፤

ኀጢአትህን አላስባትም።

26እስቲ ያለፈውን አስታውሰኝ፤

ተቀራርበን እንከራከርበት፤

ትክክለኛ ስለ መሆንህም አስረዳ።

27የመጀመሪያው አባትህ ኀጢአት ሠርቷል፤

መምህሮችህም ዐምፀውብኛል።

28ስለዚህ የመቅደስህን አለቆች አዋርዳለሁ፤

ያዕቆብን ለጥፋት፣43፥28 የዕብራይስጡ ቃል አንድን ሰው ወይም ነገር ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠትን ያመለክታል።

እስራኤልን ለስድብ እዳርጋለሁ።

Japanese Contemporary Bible

イザヤ書 43:1-28

43

イスラエルの唯一の救い主

1しかし、イスラエルよ。あなたを造った主は、

今こう言って慰めてくれます。

「恐れるな。わたしはあなたを買い戻したのだ。

わたしはあなたの名を呼んだ。

あなたはわたしのものだ。

2たとえ水の中をくぐり、大きな困難にぶつかっても、

わたしは共にいる。

悩みの川を渡るときも、おぼれはしない。

迫害の火の手が上がり、

そこを通り抜けていくときも心配はない。

炎はあなたを焼き殺さないからだ。

3わたしは主、あなたの神、あなたの救い主、

イスラエルの聖なる神だ。

わたしはあなたを自由の身とする代わりに、

エジプトとエチオピヤとセバを与えた。

4あなたを生かすために他の者が犠牲になった。

あなたのいのちを買い戻すため、

他の者のいのちと交換した。

わたしにとって、あなたは高価で尊いからだ。

わたしはあなたを愛している。

5-6恐れるな。わたしがついている。

わたしはあなたを東と西、南と北から集める。

地の果てから、私の子孫をイスラエルに連れ戻す。

7わたしを神として礼拝する者はみな集まってくる。

わたしはそのような人たちを、

わたしの栄光のために造った。

8わたしに呼ばれても、

目が見えず、耳が聞こえない者たちを、

わたしのもとに連れ戻せ。

9すべての国々の民を集めよ。

どの偶像が、このようなことを前もって知らせたか。

どの偶像が、一日先のことでも予告できるか。

どこに、彼らのことばを少しでも聞いた証人がいるか。

そんな者は一人もいない。

だとしたら、預言できるのは神だけだと

認めないわけにはいかないだろう。

10わたしには証人がいる。

イスラエルよ、あなたがたがわたしの証人、

わたしのしもべだ。

わたしを信じ、わたしだけが神であることを知るために

選ばれたのだ。

わたしのほかに神はいない。

今までも、またこれからも。

11わたしが主であって、ほかに救い主はいない。

12あなたがたが偶像を捨てるとき、

わたしは力を示した。

ただひと言で、あなたがたを救った。

あなたがたはわたしの救いをその目で見たのだから、

わたしの証人だ。

13永遠から永遠まで、わたしは神である。

わたしが何かをしようと身を起こすとき、

その前に立ちはだかる者はだれもいない。」

神のあわれみとイスラエルの不誠実

14あなたがたの救い主、イスラエルの聖なる神は、

こう告げます。

「わたしはあなたがたのために、

バビロンに軍隊を侵入させる。

それもほとんど無傷のままに。

おごり高ぶっていたバビロニヤ人は、

恐怖の叫びを上げる。

15わたしは主、あなたがたの聖なる神、

イスラエルを造った、あなたがたの王である。

16海の中に道を開き、海の底を進む道を造った主である。

17わたしはエジプトの強力な軍隊を、

戦車や馬とともに海のもくずとした。

彼らのいのちは燈心のように吹き消された。

18しかしこんなことは、

これからすることに比べれば物の数ではない。

19わたしは新しいことをしようとしている。

いや、すでに手をつけた。あなたがたの目には見えないか。

わたしの民が故国へ戻るために、荒野に道を造り、

彼らの飲み水として荒野に川を開く。

20野の獣、山犬、だちょうも、わたしに感謝する。

わたしに選ばれた民は、

この荒野の泉でのどをうるおし、元気づく。

21わたしはイスラエルを自分のために造った。

この民は、いつかきっと、

人々の前でわたしをたたえるようになる。

22だがイスラエルよ、

あなたはわたしに助けを求めなかった。

わたしにいや気がさしたのか。

23いけにえの子羊を持って来なかったし、

供え物をささげて、わたしをあがめもしなかった。

わたしが自分からささげ物を要求したことは、

ほとんどない。あなたがたを奴隷扱いしたこともない。

24それなのに、わたしのために

香りのよい香料を持って来ず、

いけにえの脂肪でわたしを喜ばせようともしなかった。

それどころか、贈り物といえば罪だけで、

ありとあらゆる欠点を見せつけ、わたしを煩わせた。

25わたしは自分のために、あなたがたの罪をぬぐい去り、

それを二度と思い出さない。

26ああ、この罪の赦しの約束を、わたしに思い出させよ。

あなたがたの罪について論じよ。

赦してほしければ、

あなたがたのほうから申し出なさい。

27あなたがたの先祖は、最初からわたしに罪を犯し、

わたしの教えに背いた。

28それで、わたしは祭司たちを免職し、

イスラエルを滅ぼし、

彼らを辱しめられるままにしておいたのだ。」