ኢሳይያስ 42 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 42:1-25

የእግዚአብሔር አገልጋይ

1“ደግፌ የያዝሁት አገልጋዬ፣

በእርሱም ደስ የሚለኝ ምርጤ ይህ ነው፤

መንፈሴን በእርሱ ላይ አደርጋለሁ፤

ለአሕዛብም ፍትሕን ያመጣል።

2አይጮኽም፣ ቃሉን ከፍ አያደርግም፤

ድምፁን በመንገድ ላይ በኀይል አያሰማም።

3የተቀጠቀጠ ሸምበቆ አይሰብርም፤

የሚጤስም የጧፍ ክር አያጠፋም፤

ፍትሕን በታማኝነት ያመጣል።

4ፍትሕን በምድር እስኪያመጣ ድረስ፣

አይደክምም፤ ተስፋም አይቈርጥም፤

ደሴቶች በሕጉ ይታመናሉ።”

5ሰማያትን የፈጠረ፣ የዘረጋቸውም፣

ምድርንና በውስጧ ያሉትን ሁሉ ያበጀ፣

ለሕዝቧ እስትንፋስን፣

ለሚኖሩባትም ሕይወትን የሚሰጥ፣

ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

6“እኔ እግዚአብሔር በጽድቅ ጠርቼሃለሁ፤

እጅህንም እይዛለሁ፤

እጠብቅሃለሁ፤

ለሕዝቡ ቃል ኪዳን፣

ለአሕዛብም ብርሃን አደርግሃለሁ።

7የዕውሮችን ዐይን ትከፍታለህ፤

ምርኮኞችን ከእስር ቤት፣

በጨለማ የተቀመጡትንም ከወህኒ ታወጣለህ።

8“እኔ እግዚአብሔር ነኝ፤ ስሜም ይህ ነው፤

ክብሬን ለሌላ፣

ምስጋናዬንም ለጣዖት አልሰጥም።

9እነሆ፤ የቀድሞው ነገር ተፈጽሟል፤

እኔም አዲስ ነገር እናገራለሁ፤

ከመብቀሉም በፊት፣

ለእናንተ አስታውቃለሁ።”

ለእግዚአብሔር የውዳሴ መዝሙር

10እናንት ወደ ባሕር የምትወርዱ፣ በዚያም ያላችሁ ሁሉ፣

ደሴቶችና በዚያ የምትኖሩ በሙሉ፣

ለእግዚአብሔር አዲስ መዝሙር፣

ከምድር ዳርቻም ምስጋናውን ዘምሩ።

11ምድረ በዳውና ከተሞቹ ድምፃቸውን ከፍ ያድርጉ፤

ቄዳር ያለችበት መንደር ደስ ይበለው፤

የሴላ ሕዝቦች በደስታ ይዘምሩ፤

ከተራሮችም ራስ ላይ ይጩኹ።

12ክብር ለእግዚአብሔር ይስጡ፤

ምስጋናውንም በደሴቶች ያውጁ።

13እግዚአብሔር እንደ ኀያል ሰው ይዘምታል፤

እንደ ተዋጊ በወኔ ይነሣል፤

የቀረርቶ ጩኸት ያሰማል፤

ጠላቶቹንም ድል ያደርጋል።

14“ለረዥም ጊዜ ዝም አልሁ፤

ጸጥ አልሁ፤ ራሴንም ገታሁ፤

አሁን ግን ምጥ እንደ ያዛት ሴት፣

እጮኻለሁ፤ ቍና ቍና እቃትታለሁ፤ እተነፍሳለሁ።

15ተራራውንና ኰረብታውን አፈርሳለሁ፤

ዕፀዋቱን ሁሉ አደርቃለሁ፤

ወንዙንም ደሴት አደርጋለሁ፤

ኵሬውን አደርቃለሁ።

16ዕውሮችን በማያወቁት መንገድ

እመራቸዋለሁ፤

ባልተለመደ ጐዳና እወስዳቸዋለሁ።

ጨለማውን በፊታቸው ብርሃን አደርጋለሁ፤

ጐርባጣውን ስፍራ አስተካክላለሁ።

ይህን አደርጋለሁ፤

አልተዋቸውም።

17በጣዖት የሚታመኑ ግን፣

ምስሎችን፣ ‘አምላኮቻችን ናችሁ’ የሚሉ፣

ወደ ኋላቸው ይመለሳሉ፤ ፈጽመው ይዋረዳሉም።

ዕውሯና ደንቈሮዋ እስራኤል

18“እናንት ደንቈሮዎች ስሙ፤

እናንት ዕውሮች እዩ፤ ተመልከቱም።

19አገልጋዬ እንጂ፣ ሌላ ዕውር ማን አለ?

ከምልከው መልእክተኛዬስ በቀር ማን ደንቈሮ አለ?

ለእኔ ታማኝ እንደ ሆነ ሰው የታወረ፣

እንደ እግዚአብሔርስ አገልጋይ ዕውር ማነው?

20ብዙ ነገርን አያችሁ፤ ነገር ግን አላስተዋላችሁም፤

ጆሯችሁ ክፍት ነው፤ ነገር ግን ምንም አትሰሙም።”

21እግዚአብሔር ስለ ጽድቁ ሲል፣

ሕጉን ታላቅና የተከበረ በማድረግ ደስ

አለው።

22ይህ ሕዝብ ግን የተበዘበዘና የተዘረፈ፣

በጕድጓድ ውስጥ የተጠመደበት፣

በወህኒ ቤት የተዘጋበት ነው፤

ተበዝብዘዋል፣

የሚያድናቸውም የለም፤

ተማርከዋል፣

“መልሷቸው” የሚልም የለም።

23ከእናንተ ይህን የሚሰማ፣

ለሚመጣውም ጊዜ አስተውሎ የሚያደምጥ ማነው?

24ያዕቆብን ለዝርፊያ፣

እስራኤልን ለምርኮ የዳረገ ማነው?

በኀጢአት የበደልነው፣

እግዚአብሔር አይደለምን?

መንገዱን ለመከተል፣

ለሕጉም መታዘዝ አልፈለጉምና።

25ስለዚህ የሚነድድ ቍጣውን፣

የጦርነትንም መዓት አፈሰሰባቸው፤

በእሳት ነበልባል ከበባቸው፤ እነርሱ ግን አላስተዋሉም፤

አቃጠላቸው፤ እነርሱ ግን ልብ አላሉም።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以賽亞書 42:1-25

主的僕人

1「看啊,我所扶持、所揀選、所喜悅的僕人,

我已將我的靈賜給祂,

祂必將正義帶給萬邦。

2祂不喧嚷,不呼喊,

不在街上高聲說話。

3壓傷的蘆葦,祂不折斷;

將殘的燈火,祂不吹滅。

祂必信實地帶來正義。

4祂不灰心也不沮喪,

直到祂在地上設立正義。

四海都渴望祂的訓誨。」

5創造諸天、鋪展穹蒼、

設立大地和地上的一切、

賜給世人生命氣息和靈性的耶和華上帝說:

6「我耶和華憑公義呼召你,

我必扶持你,保護你,

使你做我與眾民立約的中保、

成為列國的光,

7使你開瞎子的眼睛、

從監牢中釋放囚犯、

領出陷在黑暗中的人。

8我是耶和華,這就是我的名字。

我不會把我的榮耀給假神,

也不會把我當受的讚美給雕刻的偶像。

9看啊,以前的預言都已應驗,

我現在要宣告新的預言,

把還未發生的事告訴你們。」

讚美主的歌

10航海的和海中的一切、

眾海島和島上的居民啊,

你們要向耶和華高唱新歌,

從地極讚美祂。

11曠野和其中的城邑以及基達人居住的村莊,

要一同揚聲頌讚。

西拉的居民要歌唱,

在山頂歡呼。

12願他們把榮耀歸給耶和華,

在眾海島上頌讚祂。

13耶和華像出征的勇士,

像鬥志激昂的戰士。

祂必高呼吶喊,戰勝仇敵。

上帝應許幫助以色列人

14「我已沉默多時,我克制不語,

現在我要發出急促的呐喊,

像分娩的婦人。

15我要使大山小丘一片荒涼,

上面的草木都枯萎。

我要使河川變成島嶼,

池塘乾涸。

16我要帶領瞎子走他們不認識的路,

引導他們走陌生的道。

我要把他們面前的黑暗變為光明,

坎坷之地變得平坦。

我必行這些事,我必不離棄他們。

17但那些信靠雕刻的偶像、

供奉金屬鑄像的必遭唾棄,

羞愧難當。

以色列眼瞎耳聾

18「耳聾的人啊,聽吧!

眼瞎的人啊,看吧!

19有誰比我的僕人更瞎,

比我差遣的使者更聾呢?

有誰像那些與我立約的人那樣瞎呢?

有誰像耶和華的僕人那樣瞎呢?

20你們看見許多事卻不領會,

耳朵開著卻聽不見。」

21耶和華樂意使祂的律法尊大而榮耀,

因為祂行事公義。

22但這些百姓飽受劫掠,

都被困在坑中,囚在監內。

他們淪為俘虜,無人搭救;

被當作戰利品擄走,無人追回。

23你們當中誰肯專心聽呢?

以後誰肯留心傾聽呢?

24誰把雅各交給了擄掠者,

使以色列任人劫掠?

難道不是被我們得罪的耶和華嗎?

他們不肯遵行祂的道,

也不聽從祂的訓誨。

25所以,祂把烈怒和戰火傾倒在他們身上。

他們被火包圍,卻不明白;

被烈火焚身,卻不在乎。