ኢሳይያስ 39 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 39:1-8

ከባቢሎን የመጡ መልእክተኞች

1በዚያን ጊዜ የባቢሎን ንጉሥ፣ የባልዳን ልጅ፣ መሮዳክ ባልዳን የሕዝቅያስን መታመምና መፈወስ ሰምቶ ስለ ነበር፣ ደብዳቤና ስጦታ ላከለት። 2ሕዝቅያስም መልእክተኞቹን በደስታ ተቀበለ፤ ለእነርሱም በግምጃ ቤቱ ውስጥ ያለውን ብሩን፣ ወርቁን፣ ቅመማ ቅመሙን፣ ምርጡን ዘይት እንዲሁም የጦር መሣሪያውን በሙሉ፣ ያለውንም ንብረት አንዳች ሳያስቀር አሳያቸው። በቤተ መንግሥቱም ሆነ በግዛቱ ሁሉ ሕዝቅያስ ያላሳያቸው ነገር አልነበረም።

3ከዚያም ነቢዩ ኢሳይያስ ወደ ንጉሡ ሕዝቅያስ መጥቶ፣ “እነዚያ ሰዎች ምን አሉህ? ወደ አንተ ዘንድ የመጡትስ ከየት ነው?” አለው።

ሕዝቅያስም፣ “ወደ እኔ የመጡት ከሩቅ አገር፣ ከባቢሎን ነው” አለው።

4ነቢዩም፣ “በቤተ መንግሥትህ ያዩት ምንድን ነው?” አለው።

ሕዝቅያስም፣ “በቤተ መንግሥቴ ያለውን ሁሉ አይተዋል፤ ከንብረቴ ያላሳየኋቸው ምንም ነገር የለም” አለ።

5ኢሳይያስም ሕዝቅያስን እንዲህ አለው፤ “የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔርን ቃል ስማ፤ 6እነሆ፤ በቤተ መንግሥትህ ያለው ሁሉ፣ አባቶችህ እስከዚህች ቀን ድረስ ያከማቹትም ሁሉ ወደ ባቢሎን ተማርኮ የሚወሰድበት ቀን ይመጣል፤ አንዳች የሚተርፍ ነገር የለም፤ ይላል እግዚአብሔር7ከአብራክህ ከሚከፈሉት፣ ከዘርህ፣ ከአንተ ከሚወለዱት ልጆች ተወስደው፣ በባቢሎን ንጉሥ ቤተ መንግሥት ጃንደረባዎች ይሆናሉ።”

8ሕዝቅያስም፣ “የተናገርኸው የእግዚአብሔር ቃል መልካም ነው” አለው፤ “በዘመኔ ሰላምና ጸጥታ ከኖረ ዘንድ” ብሎ ዐስቦ ነበርና።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以賽亞書 39:1-8

巴比倫的使者

1那時,巴比倫王——巴拉但的兒子米羅達·巴拉但聽說希西迦患病、後來痊癒,便派人送去書信和禮物。 2希西迦欣然接見使者,讓他們觀看國庫裡的金銀、香料、珍貴膏油、所有兵器和一切寶物。希西迦把宮中及國內的一切都給他們看。

3以賽亞先知來見希西迦王,問他:「這些人說了些什麼?他們從哪裡來?」

希西迦答道:「他們從遙遠的巴比倫來。」

4以賽亞問:「他們在你宮中看見了什麼?」

希西迦答道:「他們看到了我宮中的一切。我把國庫裡的一切都給他們看了。」

5以賽亞希西迦說:「你聽著,萬軍之耶和華說, 6『終有一天,你王宮中的一切和你祖先積攢到現在的一切,必一件不留地被擄到巴比倫。這是耶和華說的。 7你的子孫當中必有人被擄去,在巴比倫王的宮中做太監。』」 8希西迦以賽亞說:「耶和華藉你說的話很好。」因為他想:「我有生之年將平安穩妥。」