ኢሳይያስ 35 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 35:1-10

የተቤዠ ሕዝብ ደስታ

1ምድረ በዳውና ደረቁ ምድር ደስ ይላቸዋል፤

በረሓው ሐሤት ያደርጋል፤ ይፈካል፤

እንደ አደይም ያብባል።

2በደስታና በዝማሬ ሐሤት ያደርጋል፤

የሊባኖስ ክብር ይሰጠዋል፤

የቀርሜሎስንና የሳሮንን ግርማ ይለብሳል።

የአምላካችንን ታላቅ ግርማ፣

የእግዚአብሔርን ክብር ያያሉ።

3የደከሙትን እጆች አበርቱ፤

የላሉትንም ጕልበቶች አጽኑ፤

4የሚፈራ ልብ ላላቸው እንዲህ በሉ፤

“በርቱ፤ አትፍሩ፤

አምላካችሁ ይመጣል፤

ሊበቀል ይመጣል፤

እርሱም ብድራቱን ይዞ፣

ሊያድናችሁ ይመጣል።”

5በዚያን ጊዜም የዕውር ዐይኖች ይገለጣሉ፤

የደንቈሮም ጆሮዎች ይከፈታሉ።

6ዐንካሳ እንደ ሚዳቋ ይዘልላል፤

የድዳውም አንደበት በደስታ ይዘምራል፤

ውሃ ከበረሓ ይወጣል፤

ምንጮችም ከምድረ በዳ ይፈልቃሉ።

7ንዳዳማው ምድር ኵሬ ይሆናል፤

የተጠማው መሬት ውሃ ያመነጫል።

ቀበሮዎች በተኙባቸው ጕድጓዶች፣

ሣር፣ ሸንበቆና ደንገል ይበቅልበታል።

8በዚያ አውራ ጐዳና ይሆናል፤

“የተቀደሰ መንገድ” ተብሎ ይጠራል።

የረከሱ አይሄዱበትም፤

በመንገዱ ላይ ላሉት ብቻ ይሆናል፤

ገራገሮችም ከመንገዱ አይስቱም።

9አንበሳ አይኖርበትም፤

ነጣቂ አውሬም አይወጣበትም፤

እነዚህማ በዚያ ስፍራ አይገኙም፤

የዳኑት ብቻ በዚያ ይሄዳሉ፤

10እግዚአብሔር የዋጃቸው ይመለሳሉ።

እየዘመሩ ወደ ጽዮን ይገባሉ፤

ዘላለማዊ ደስታን እንደ አክሊል ይቀዳጁታል፤

ፍሥሓና ሐሤት ያገኛሉ፤

ሐዘንና ትካዜ ከዚያ ይሸሻሉ።

New International Version

Isaiah 35:1-10

Joy of the Redeemed

1The desert and the parched land will be glad;

the wilderness will rejoice and blossom.

Like the crocus, 2it will burst into bloom;

it will rejoice greatly and shout for joy.

The glory of Lebanon will be given to it,

the splendor of Carmel and Sharon;

they will see the glory of the Lord,

the splendor of our God.

3Strengthen the feeble hands,

steady the knees that give way;

4say to those with fearful hearts,

“Be strong, do not fear;

your God will come,

he will come with vengeance;

with divine retribution

he will come to save you.”

5Then will the eyes of the blind be opened

and the ears of the deaf unstopped.

6Then will the lame leap like a deer,

and the mute tongue shout for joy.

Water will gush forth in the wilderness

and streams in the desert.

7The burning sand will become a pool,

the thirsty ground bubbling springs.

In the haunts where jackals once lay,

grass and reeds and papyrus will grow.

8And a highway will be there;

it will be called the Way of Holiness;

it will be for those who walk on that Way.

The unclean will not journey on it;

wicked fools will not go about on it.

9No lion will be there,

nor any ravenous beast;

they will not be found there.

But only the redeemed will walk there,

10and those the Lord has rescued will return.

They will enter Zion with singing;

everlasting joy will crown their heads.

Gladness and joy will overtake them,

and sorrow and sighing will flee away.