ኢሳይያስ 32 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 32:1-20

የጽድቅ መንግሥት

1እነሆ፤ ንጉሥ በጽድቅ ይነግሣል፤

ገዦችም በፍትሕ ይገዛሉ።

2እያንዳንዱ ሰው ከነፋስ መከለያ፣

ከወጀብም መጠጊያ ይሆናል።

በበረሓም እንደ ውሃ ምንጭ፣

በተጠማም ምድር እንደ ትልቅ ቋጥኝ ጥላ ይሆናል።

3የሚያዩ ሰዎች ዐይን ከእንግዲህ አይጨፈንም፤

የሚሰሙም ጆሮዎች ነቅተው ያዳምጣሉ።

4የችኵል አእምሮ ያውቃል፤ ያስተውላልም፤

የተብታባም ምላስ የተፈታ ይሆናል፤

አጥርቶም ይናገራል።

5ከእንግዲህ ሰነፍ ጨዋ አይባልም፤

ጋጠወጥም አይከበርም።

6ሰነፍ ስንፍናን ይናገራል፤

አእምሮው ክፋትን ያውጠነጥናል፤

ፈሪሀ እግዚአብሔር የሌለበትን አድራጎት ይፈጽማል፤

በእግዚአብሔርም ላይ የስሕተት ቃል ይናገራል፤

ለተራበ ምግብ ይከለክላል፤

ለተጠማ ውሃ አይሰጥም።

7የጋጠወጥ ዘዴ ክፉ ነው፤

የችግረኛም አቤቱታ ትክክል ቢሆን፣

ድኻን በሐሰት ለማጥፋት፣

ክፋት ያውጠነጥናል።

8ጨዋ ግን ሐሳቡም ጨዋ ነው፤

በጨዋነት ምግባርም ጸንቶ ይገኛል።

የኢየሩሳሌም ሴቶች

9እናንት ትዕቢት የወጠራችሁ ሴቶች፣

ተነሡ፤ ድምፄን ስሙ፤

እናንት ተደላድላችሁ የምትኖሩ ሴቶች ልጆች ሆይ፤

የምነግራችሁን አድምጡ።

10ዓመቱ ገና እንዳለፈ፣

ተደላድላችሁ የነበራችሁ ትንቀጠቀጣላችሁ፤

የወይን ተክል ፍሬ አይሰጥም፤

የፍራፍሬም ወቅት አይመጣም።

11እናንት ትዕቢት የወጠራችሁ ሴቶች ተንቀጥቀጡ፤

እናንት ተደላድላችሁ የምትኖሩ ሴቶች ልጆች፣ በፍርሀት ተርበትበቱ፤

ልብሳችሁን አውልቁ፤

ወገባችሁን በማቅ ታጠቁ።

12ስለ ለሙ መሬት ደረታችሁን ምቱ፤

ስለ ፍሬያማው የወይን ተክል ዕዘኑ፤

13ስለ ሕዝቤ ምድር፣

እሾኽና አሜከላ ስለ በቀለበት ምድር፣

ስለ ፈንጠዝያ ቤቶች ሁሉ፣

ስለዚህችም መፈንጫ ከተማ አልቅሱ።

14ዐምባ ምሽጉ ወና ይሆናል፤

ውካታ የበዛበት ከተማ ጭር ይላል፤

ምሽጉና ማማው ለዘላለሙ ዋሻ፣

የዱር አህያ መፈንጫ፣ የመንጋም መሰማሪያ ይሆናል፤

15ይህም የሚሆነው መንፈስ ከላይ እስኪፈስስልን፣

ምድረ በዳው ለም መሬት፣

ለሙ መሬትም ጫካ እስኪመስል ድረስ ነው።

16በምድረ በዳ ፍትሕ ይሰፍናል፤

በለሙም መሬት ጽድቅ ይኖራል፤

17የጽድቅ ፍሬ ሰላም፣

የጽድቅ ውጤትም ጸጥታና ለዘላለም መታመን ይሆናል።

18ሕዝቤ ሰላማዊ በሆነ መኖሪያ፣

በሚያስተማምን ቤት፣

ጸጥ ባለም ስፍራ ዐርፎ ይኖራል።

19ደኑ በበረዶ ቢመታ፣

ከተማውም ፈጽሞ ቢወድም፣

20በየወንዙ ዳር ዘር የምትዘሩ፣

በሬዎቻችሁንና አህዮቻችሁን በነጻነት የምታሰማሩ፣

ምንኛ የተባረካችሁ ናችሁ።

Ketab El Hayat

إشعياء 32:1-20

مملكة البر

1انْظُرُوا هَا إِنَّ مَلِكاً يَمْلِكُ بِالْبِرِّ، وَرُؤَسَاءَ يَحْكُمُونَ بِالْعَدْلِ. 2وَيُصْبِحُ كُلُّ إِنْسَانٍ كَمَلاذٍ مِنَ الرِّيحِ، وَكَمَلْجَأٍ مِنَ الْعَاصِفَةِ، أَوْ كَجَدَاوِلِ مِيَاهٍ فِي صَحْرَاءَ، أَوْ كَظِلِّ صَخْرَةٍ عَظِيمَةٍ فِي أَرْضٍ جَدْبَاءَ. 3عِنْدَئِذٍ تَنْفَتِحُ عُيُونُ النَّاظِرِينَ، وَتُصْغِي آذَانُ السَّامِعِينَ (لاحْتِيَاجَاتِ شَعْبِهِمْ) 4فَتَفْهَمُ وَتَعْلَمُ الْعُقُولُ الْمُتَهَوِّرَةُ، تَنْطِقُ بِطَلاقَةٍ الأَلْسِنَةُ الثَّقِيلَةُ. 5وَلا يُدْعَى اللَّئِيمُ بَعْدُ كَرِيماً، وَلا يُقَالُ لِلْمَاكِرِ شَرِيفٌ، 6لأَنَّ اللَّئِيمَ يَنْطِقُ بِاللُّؤْمِ، وَقَلْبُهُ يَتَآمَرُ بِالإِثْمِ لِيَرْتَكِبَ شَرّاً وَلِيَفْتَرِيَ عَلَى الرَّبِّ، تَارِكاً الْمُتَضَوِّرَ جُوعاً مِنْ غَيْرِ شِبَعٍ، وَحَارِماً الظَّامِئَ مِنَ الشُّرْبِ. 7إِنَّ أَسَالِيبَ الْمَاكِرِ شِرِّيرَةٌ، وَمُؤَامَرَاتِهِ خَبِيثَةٌ لِيُهْلِكَ الْبَائِسِينَ بِالأَكَاذِيبِ، حَتَّى لَوْ كَانَ الْمِسْكِينُ يَنْطِقُ بِالْحَقِّ. 8أَمَّا الْكَرِيمُ فَبِالْمَآثِرِ يَفْتَكِرُ وَبِالْمَكَارِمِ يَشْتَهِرُ.

نساء أورشليم

9أَيَّتُهَا النِّسَاءُ الْمُتْرَفَاتُ الْمُتَكَاسِلاتُ، انْهَضْنَ وَاسْتَمِعْنَ إِلَى صَوْتِي. أَيَّتُهَا الْبَنَاتُ الْمُطْمَئِنَّاتُ أَصْغِينَ إِلَى أَقْوَالِي. 10مَا تَكَادُ تَنْقَضِي أَيَّامٌ عَلَى سَنَةٍ حَتَّى تَعْتَرِيكُنَّ رِعْدَةٌ أَيَّتُهَا الآمِنَاتُ، لأَنَّ الْقِطَافَ قَدْ تَلِفَ، وَمَوْعِدَ جَنْيِ الأَثْمَارِ قَدْ أَخْلَفَ. 11ارْتَعِدْنَ أَيَّتُهَا النِّسَاءُ الْمُطْمَئِنَّاتُ وَارْتَجِفْنَ أَيَّتُهَا الْفَتَيَاتُ الآمِنَاتُ. تَجَرَّدْنَ مِنْ ثِيَابِكُنَّ وَتَعَرَّيْنَ وَمَنْطِقْنَ أَحْقَاءَكُنَّ بِالْمُسُوحِ. 12اضْرِبْنَ عَلَى صُدُورِكُنَّ حَسْرَةً عَلَى الْمُرُوجِ الْمُبْهِجَةِ وَالْكُرُومِ الْمُثْمِرَةِ. 13لأَنَّ أَرْضَ شَعْبِي تُنْبِتُ الشَّوْكَ وَالْحَسَكَ، فَتَنْمُو حَتَّى فِي كُلِّ بُيُوتِ الْفَرَحِ فِي الْمَدِينَةِ الْمُبْتَهِجَةِ. 14لأَنَّ الْقَصْرَ يُصْبِحُ مَهْجُوراً، وَالْمُدُنَ الْعَامِرَةَ خَالِيَةً، وَالتِّلالَ وَالْبُرُوجَ مَغَاوِرَ إِلَى الأَبَدِ، وَمَرَاحاً لِلْحَمِيرِ الْوَحْشِيَّةِ وَمَرْعىً لِلْقُطْعَانِ، 15حَتَّى يَنْسَكِبَ عَلَيْنَا رُوحٌ مِنَ السَّمَاءِ، فَتَتَحَوَّلُ البَرِّيَّةُ إِلَى مَرْجٍ مُخْصِبٍ، وَيُحْسَبُ المَرْجُ غَابَةً.

16عِنْدَئِذٍ يَسْكُنُ الْعَدْلُ فِي الصَّحْرَاءِ، وَيُقِيمُ الْبِرُّ فِي الْمَرْجِ الْمُخْصِبِ، 17فَيَكُونُ ثَمَرُ الْبِرِّ سَلاماً، وَفِعْلُ الْبِرِّ سَكِينَةً وَطُمَأْنِينَةً إِلَى الأَبَدِ، 18فَيَسْكُنُ شَعْبِي فِي دِيَارِ سَلامٍ، وَفِي مَسَاكِنَ آمِنَةٍ، وَفِي أَمَاكِنَ رَاحَةٍ مُطْمَئِنَّةٍ، 19مَعَ أَنَّ الْبَرَدَ يُسَوِّي الْغَابَةَ بِالأَرْضِ، وَتُدَمَّرُ الْمَدِينَةُ حَتَّى الْحَضِيضِ. 20طُوبَاكُمْ أَيُّهَا الزَّارِعُونَ عِنْدَ كُلِّ مَاءٍ، الَّذِينَ سَرَّحْتُمْ قَوَائِمَ الثَّوْرِ وَالْحِمَارِ لِتَرْعَى طَلِيقَةً.