ኢሳይያስ 31 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 31:1-9

በግብፅ ለሚደገፉ ወዮላቸው

1ወደ እስራኤል ቅዱስ ለማይመለከቱ፣

ከእግዚአብሔርም ርዳታን ለማይሹ፣

ነገር ግን፤ ለርዳታ ብለው ወደ ግብፅ ለሚወርዱ፣

በፈረሶች ለሚታመኑ፣

በሠረገሎቻቸው ብዛት፣

በፈረሶቻቸውም ታላቅ ብርታት ለሚመኩ ወዮላቸው!

2እርሱም ግን ጠቢብ ነው፤ ጥፋትን ያመጣል፤

ቃሉን አያጥፍም።

በክፉ አድራጊዎች ቤት ላይ፣

በደለኞችንም በሚረዱ ላይ ይነሣል።

3ግብፃውያን ሰዎች እንጂ አምላክ አይደሉም፤

ፈረሶቻቸውም ሥጋ እንጂ መንፈስ አይደሉም፤

እግዚአብሔር እጁን ሲዘረጋ፣

ርዳታ ሰጪው ይሰናከላል፤

ተረጂውም ይወድቃል፤

ሁለቱም በአንድ ላይ ይጠፋሉ።

4እግዚአብሔር እንዲህ ብሎኛል፤

“አንበሳ ወይም የአንበሳ ደቦል

የሰበረውን ይዞ ሲያገሣ፣

ብዙ እረኞች

ተጠራርተው ሲመጡበት፣

ጩኸታቸው እንደማያስፈራው፣

በድምፃቸውም እንደማይታወክ፣

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

በጽዮን ተራራና በከፍታዎቿ ላይ ለውጊያ እንዲሁ ይወርዳል።

5በዐናት ላይ እንደሚያንዣብቡ ወፎች፣

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ኢየሩሳሌምን እንዲሁ ይጋርዳታል፤

ይከልላታል፤ ይታደጋታል፤

በላይዋ ያልፋል፤ ያድናታልም።”

6እናንተ እስራኤላውያን ሆይ፤ እጅግ ወዳመፃችሁበት ወደ እርሱ ተመለሱ። 7በዚያን ቀን በኀጢአት የተሞላ እጃችሁ የሠራቸውን የወርቅና የብር ጣዖቶች ሁላችሁም ትጥላላችሁና።

8“አሦር የሰው ባልሆነ ሰይፍ ይወድቃል፤

የሥጋ ለባሽ ያልሆነም ሰይፍ ይበላዋል።

ከሰይፍ ፊት ይሸሻል፤

ጕልማሶቹም የግዳጅ ሥራ ይሠራሉ።

9ጠንካራ ምሽጉ በሽብር ምክንያት ይወድቃል፤

መሪዎቹም የጦር ዐርማ ሲያዩ

በድንጋጤ ይዋጣሉ”

ይላል እሳቱ በጽዮን፣

ማንደጃውም በኢየሩሳሌም የሆነ እግዚአብሔር

Ketab El Hayat

إشعياء 31:1-9

الويل لمن يعتمد على غير الرب

1وَيْلٌ لِلْمُنْحَدِرِينَ إِلَى مِصْرَ طَلَباً لِلْعَوْنِ، الْمُتَوَكِّلِينَ عَلَى الْخَيْلِ، الْوَاثِقِينَ بِكَثْرَةِ الْمَرْكَبَاتِ وَبِبَأْسِ الْفُرْسَانِ، مِنْ غَيْرِ أَنْ يَلْتَفِتُوا إِلَى قُدُّوسِ إِسْرَائِيلَ، أَوْ يَطْلُبُوا مَشُورَةَ الرَّبِّ. 2وَمَعَ ذَلِكَ فَهُوَ حَكِيمٌ يَجْلِبُ الشَّرَّ، وَلا يَنْقُضُ كَلامَهُ بَلْ سَيَهُبُّ لِيُعَاقِبَ بَيْتَ الأَشْرَارِ وَنَاصِري فَعَلَةِ الإِثْمِ. 3لَيْسَ الْمِصْرِيُّونَ آلِهَةً بَلْ بَشَراً، وَخُيُولُهُمْ مُجَرَّدُ أَجْسَادٍ وَلَيْسَتْ أَرْوَاحاً، وَعِنْدَمَا يَمُدُّ الرَّبُّ يَدَهُ، يَتَعَثَّرُ الْمُعِينُ وَيَسْقُطُ الْمُسْتَعِينُ، وَيَهْلِكَانِ كِلاهُمَا مَعاً.

4لأَنَّهُ هَكَذَا قَالَ الرَّبُّ لِي: «كَمَا يُزَمْجِرُ الأَسَدُ أَوِ الشِّبْلُ عَلَى فَرِيسَتِهِ، مِنْ غَيْرِ أَنْ يَخْشَى مِنْ صَرَخَاتِ جَمَاعَةِ الرُّعَاةِ الْمُتَأَلِّبِينَ عَلَيْهِ، أَوْ يَفْزَعَ مِنْ جَلَبَتِهِمْ، هَكَذَا يُقْبِلُ الرَّبُّ الْقَدِيرُ لِيُحَارِبَ عَنْ جَبَلِ صِهْيَوْنَ. 5وَيَرِفُّ الرَّبُّ الْقَدِيرُ عَلَى أُورُشَلِيمَ لِحِمَايَتِهَا كَالطُّيُورِ الْحَائِمَةِ فَوْقَ أَعْشَاشِهَا، فَيَحْمِي وَيُنْقِذُ وَيَعْفُو وَيُخَلِّصُ.

6ارْجِعُوا أَيُّهَا الإِسْرَائِيلِيُّونَ إِلَى مَنْ تَمَرَّدْتُمْ عَلَيْهِ أَشَدَّ التَّمَرُّدِ، 7لأَنَّهُ فِي ذَلِكَ الْيَوْمِ يَنْبِذُ كُلُّ وَاحِدٍ أَصْنَامَهُ الْفِضِّيَّةَ وَأَوْثَانَهُ الذَّهَبِيَّةَ الَّتِي صَنَعَهَا بِيَدِهِ الْخَاطِئَةِ. 8وَيُصْرَعُ الأَشُورِيُّونَ وَيُلْتَهَمُونَ، وَلَكِنْ لَيْسَ بِسَيْفِ بَشَرٍ، وَيَفِرُّونَ مِنْ أَمَامِ السَّيْفِ، وَيُسَاقُ فِتْيَانُهُمْ إِلَى الأَعْمَالِ الشَّاقَّةِ، 9وَتَفْنَى صُخُورُهُمْ مِنَ الْفَزَعِ، وَيُوَلِّي قَادَتُهُمُ الأَدْبَارَ عِنْدَمَا يَرَوْنَ عَلَمَ إِسْرَائِيلَ». هَذَا مَا يَقُولُهُ الرَّبُّ الَّذِي نَارُهُ فِي صِهْيَوْنَ، وَتَنُّورُهُ فِي أُورُشَلِيمَ.