ኢሳይያስ 28 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 28:1-29

ወዮ ለኤፍሬም

1ለኤፍሬም ሰካራሞች የመታበያ አክሊል ለሆነች፣

በለመለመ ሸለቆ ዐናት ላይ ጕብ ብላ፣

የክብሩ ውበት ለሆነች ጠውላጋ አበባ፣

የወይን ጠጅ ለዘራቸው መኵራሪያ ለሆነች፣

ለዚያች ከተማ ወዮላት!

2እነሆ፤ ጌታ ኀያልና ብርቱ የሆነ ነገር አለው፤

ይህም እንደ በረዶ ወጀብ፣ እንደሚያጠፋ ዐውሎ ነፋስ፣

እንደ ኀይለኛ ማዕበል፣ እንደ ከባድ ዝናብ፣

በኀይል ወደ ምድር ይጥላታል።

3የኤፍሬም ሰካራሞች የመታበያ አክሊል፣

በእግር ይረገጣል።

4በለምለሙ ሸለቆ ዐናት ላይ ጕብ ብላ፣

የክብሩ ውበት የሆነች ጠውላጋ አበባ፣

ከመከር በፊት እንደ ደረሰች፣

ሰውም ድንገት አይቶ እንደሚቀጥፋት

ወዲያውኑም እንደሚውጣት በለስ ትሆናለች።

5በዚያን ቀን የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

ለተረፈው ሕዝቡ፣

የክብር ዘውድ፣

የውበትም አክሊል ይሆናል።

6እርሱም በፍርድ ወንበር ላይ ለሚቀመጠው፣

የፍትሕ መንፈስ፣

ጦርን ከከተማዪቱ በር ላይ ለሚመልሱም፣

የኀይል ምንጭ ይሆናል።

7እነዚህም በወይን ጠጅ ይንገዳገዳሉ፤

በሚያሰክርም መጠጥ ይወላገዳሉ፤

ካህናቱና ነቢያቱ በሚያሰክር መጠጥ ተንገዳገዱ፤

በወይን ጠጅ ነገር ተምታታባቸው፤

በሚያሰክር መጠጥ ተወላገዱ፤

ራእይ ሲያዩ ይስታሉ፤

ፍርድ ሲሰጡም ይሰናከላሉ።

8የማእድ ገበታቸው ሁሉ በትፋት ተሞልቷል፤

ከትውኪያም የጸዳ ቦታ የለም።

9እነርሱም እንዲህ ይላሉ፤ “የሚያስተምረው ማንን ነው?

መልእክቱን የሚያብራራውስ ለማን ነው?

ወተት ለተዉት ሕፃናት?

ወይስ ጡት ለጣሉት?

10በትእዛዝ ላይ ትእዛዝ፣ በትእዛዝ ላይ

ትእዛዝ፤

በደንብ ላይ ደንብ፣ በደንብ ላይ ደንብ፤28፥10 በዚህና በቍጥር 13 ላይ ዕብራይስጡ፣ ላቨ ላሳቨ ሳቨ ላሳቨ፣ ካቨ ላካቨ ካቨ ለካቨ ይላል፤ ምናልባት ትርጕም የለሽ ንግግርን ለማሳየት ይሆናል፤ ይኸውም የነቢያትን ቃል አስመስሎ መናገርን ሊሆን ይችላል።

እዚህ ጥቂት፣ እዚያ ጥቂት ነውና።”

11እንግዲያማ እግዚአብሔር

በባዕድ ልሳን በእንግዳ ቋንቋ ለዚህ ሕዝብ ይናገራል።

12እርሱ፣

“ይህች የዕረፍት ቦታ ናት፤ የደከመው ይረፍ፤

ይህች የእፎይታ ቦታ ናት” ያለው ለማን ነበር?

እነርሱ ግን መስማት አልፈለጉም።

13ስለዚህ የእግዚአብሔር ቃል፣

በትእዛዝ ላይ ትእዛዝ፣ በትእዛዝ ላይ ትእዛዝ፤

በደንብ ላይ ደንብ፣ በደንብ ላይ ደንብ፤

እዚህ ጥቂት እዚያ ጥቂት ይሆንባቸዋል።

ይህ የሚሆንባቸው ሄደው ወደ ኋላ እንዲወድቁ፣

እንዲቈስሉና በወጥመድ እንዲያዙ፣

እንዲማረኩም ነው።

14ስለዚህ በኢየሩሳሌም ያለውን ሕዝብ የምትገዙ፣

እናንት ፌዘኞች የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ።

15እናንት፣ “ከሞት ጋር ቃል ኪዳን ገብተናል፤

ከሲኦልም ጋር ስምምነት አድርገናል፤

ውሸትን መጠጊያችን፣

ሐሰትን28፥15 ወይም፣ ሐሰተኛ ጣዖታትን መደበቂያችን አድርገናል፤

ታላቅ መቅሠፍት እየጠራረገ ሲያልፍ፣

ሊነካን አይችልም” በማለት ታብያችኋል።

16ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ የተፈተነ ድንጋይ፣ የመሠረት ድንጋይ፣

ለጽኑ መሠረት የሚሆን የከበረ የማእዘን ድንጋይ፣

በጽዮን አስቀምጣለሁ፤

በእርሱም የሚያምን አያፍርም።

17ፍትሕን የመለኪያ ገመድ፣

ጽድቅንም ቱንቢ አደርጋለሁ፤

ውሸት መጠጊያችሁን የበረዶ ዝናብ ይጠራርገዋል፤

መደበቂያችሁንም ውሃ ያጥለቀልቀዋል።

18ከሞት ጋር የገባችሁት ቃል ኪዳን ይሻራል፤

ከሲኦልም ጋር ያደረጋችሁት ስምምነት ይፈርሳል፤

ታላቁ መቅሠፍት እየጠራረገ ሲያልፍ፣

እናንተም ትጠራረጋላችሁ።

19በመጣ ቍጥር ይዟችሁ ይሄዳል፤

ማለዳ ማለዳ፣ በቀንና በሌሊትም

ይጠራርጋል።”

ይህን ቃል ብታስተውሉ፣

ሽብር በሽብር በሆነ ነበር።

20እግር ዘርግቶ እንዳይተኛ ዐልጋው ዐጭር ነው፤

ሰውነትንም ለመሸፋፈን ብርድ ልብሱ ጠባብ ነው።

21እግዚአብሔር ሥራውን፣ አዎን ድንቅ ሥራውን ሊሠራ፣

ተግባሩን፣ እንግዳ የሆነ ተግባሩን ሊያከናውን፣

በፐራሲም ተራራ እንዳደረገው ይነሣል፣

በገባዖን ሸለቆ እንዳደረገው ይነሣሣል።

22እንግዲህ ፌዛችሁን አቁሙ፤

አለዚያ እስራታችሁ ይጸናባችኋል፤

ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

መላውን ምድር ለማጥፋት ያወጀውን ዐዋጅ ሰምቻለሁ።

23አድምጡ ድምፄን ስሙ፤

አስተውሉ ቃሌንም ስሙ።

24ገበሬ ሊዘራ መሬቱን ሲያዘጋጅ ያለ ማቋረጥ ያርሳልን?

ጓሉን ሲከሰክስ፣ ዐፈሩን ሲያለሰልስ ይከርማልን?

25ዕርሻውን አስተካክሎ፣

ጥቍር አዝሙድና ከሙን አይዘራምን?

ስንዴውንስ በትልሙ28፥25 በዕብራይስጡ የዚህ ቃል ትርጕም በትክክል አይታወቅም።

ገብሱን በተገቢ ቦታው፣

አጃውንም በተመደበው ስፍራ አይዘራምን?

26አምላኩ ያስተምረዋል፤

ትክክለኛውንም መንገድ ያሳየዋል።

27ጥቍር አዝሙድ በመውቂያ መሣሪያ አይወቃም፤

ከሙን የሠረገላ መንኰራኵር አይሄድበትም፤

ጥቍር አዝሙድ በበትር፣

ከሙንም በዘንግ ይወቃል።

28እንጀራን ለመጋገር እህል ይፈጫል፤

ስለዚህ አንድ ሰው ለዘላለም እህል ሲወቃ አይኖርም።

የመውቂያውን መንኰራኵር ቢያኼድበትም፣

ፈረሶቹ አይደፈጥጡትም።

29ይህ ሁሉ የሚሆነው በምክሩ ድንቅ፣ በጥበቡ

ታላቅ ከሆነው፣

ከሰራዊት ጌታ ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以賽亞書 28:1-29

北國必遭審判

1以法蓮酒徒引以為榮的華冠有禍了!

它座落在醉酒者肥美的山谷頂上,

它的榮美如將殘之花。

2看啊,主已經派來一位強壯有力的人,

他像冰雹和毀滅的暴風,

又像洶湧氾濫的洪水,

他必把那華冠猛力摔在地上。

3以法蓮酒徒引以為榮的華冠必被踐踏。

4那肥美山谷上將殘的榮美之花,

必像夏季到來之前早熟的無花果,

人一看見它就把它摘去吞掉。

5到那日,萬軍之耶和華必做祂餘民的榮冠和華冕。

6祂必使審判官公正斷案,

賜力量給守城退敵之人。

7但祭司和先知也因喝酒而搖搖晃晃,

因烈酒而東倒西歪。

他們因烈酒而搖搖晃晃、

酩酊大醉、東倒西歪,

他們錯解異象,糊塗判案。

8桌子上到處都是嘔吐之物,

一片狼藉。

9他們抱怨我說:

「他想教導誰知識呢?

他想把信息解釋給誰呢?

是剛剛斷奶、離開母懷的嬰孩嗎?

10因為他的教導只是命命令令、命命令令、律律例例、律律例例、這裡一點、那裡一點。」

11因此,耶和華必用外族人的口和語言來教訓他們。

12耶和華曾對他們說:

「這是安歇之地,

讓疲乏的人安歇吧。

這是安歇之地。」

他們卻不肯聽。

13所以,對他們來說,

耶和華的話成了命命令令、命命令令、律律例例、律律例例、這裡一點、那裡一點,

以致他們走路時仰面跌倒,摔傷,落網,被捉。

14你們這些好譏諷、在耶路撒冷統管百姓的人啊,

要聽耶和華的話。

15你們說:

「我們已經和死亡立約,

與陰間結盟。

災難席捲而來的時候,

我們會安然無恙,

因為我們以謊言為庇護所,

以詭詐為藏身處。」

16所以主耶和華說:

「看啊,我要在錫安放一塊基石,

一塊經過考驗的石頭,

一塊根基穩固的寶貴房角石,

信靠的人必不致蒙羞。

17我必以公平為準繩,

以公義作線錘。

冰雹必砸碎你們虛謊的庇護所,

洪水必淹沒你們的藏身處。

18你們和死亡所立的約必被廢棄,

與陰間的結盟必不能長久。

災難席捲而來的時候,

你們必遭毀滅。

19災難必不分晝夜、日復一日地掃過,

每次掃過都必將你們擄去。」

明白這信息的人都必驚恐萬分。

20你們的床太小,不能舒身;

你們的被子太窄,不足裹身。28·20 此處的床和被子象徵他們虛假的安全感。

21耶和華必像在毗拉心山一樣挺身而出,

像在基遍谷一樣發怒,

要完成祂奇異的作為,

成就祂不尋常的工作。

22現在你們不要再譏諷了,

以免捆綁你們的繩索勒得更緊,

因為我已從主——萬軍之耶和華那裡聽到毀滅全國的諭旨。

23你們要側耳聽我的聲音,

留心聽我的話語。

24難道農夫會一直耕地而不撒種嗎?

難道他會一直犁地、耙地嗎?

25他耙平土地之後,

難道不種小茴香、大茴香嗎?

不按行種小麥,

在合適的地方種大麥,

在田邊種粗麥嗎?

26因為上帝指點他,教導他耕種之道。

27打小茴香不用大槌,用棍子;

打大茴香不用石磙,用棒子。

28做餅的糧食要磨碎,

沒有人會不停地在場上碾壓糧食。

馬拉著石磙在場上軋過,

也不會把麥子磨碎。

29這些知識都是萬軍之耶和華所賜的,

祂有奇妙的謀略和偉大的智慧。