ኢሳይያስ 27 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 27:1-13

የእስራኤል ዐርነት መውጣት

1በዚያ ቀን እግዚአብሔር

ተወርዋሪውን እባብ ሌዋታንን፣

የሚጠቀለለውን ዘንዶ ሌዋታንን

በብርቱ፣ በታላቁና በኀይለኛ ሰይፍ ይቀጣዋል፤

የባሕሩንም ግዙፍ አውሬ ይቈራርጠዋል።

2በዚያን ቀን እንዲህ ይባላል፤

“ለመልካሙ የወይን ቦታ ዘምሩለት፤

3እኔ እግዚአብሔር ጠባቂው ነኝ፤

ዘወትር ውሃ አጠጣዋለሁ፤

ስለዚህ ማንም አይጐዳውም፣

ቀንና ሌሊት እጠብቀዋለሁ፤

4እኔ አልቈጣም።

እሾኽና ኵርንችት ምነው በተነሡብኝ!

ለውጊያ በወጣሁባቸው፣

አንድ ላይ ባቃጠልኋቸው!

5አለዚያ ይምጡና መሸሸጊያቸው ያድርጉኝ፤

ከእኔ ጋር ሰላም ይፍጠሩ፤

አዎን፤ ከእኔ ጋር ሰላም ያድርጉ።”

6በሚመጡት ቀናት ያዕቆብ ሥር ይሰድዳል፤

እስራኤልም ያቈጠቍጣል፣ ያብባልም፤

በፍሬያቸውም ምድርን ሁሉ ይሞላሉ።

7የመቷትን እንደ መታቸው፣

እግዚአብሔር እርሷንስ መታትን?

የገደሏትን እንደ ገደላቸው፣

እርሷስ ተገደለችን?

8በጦርነትና በስደት ተፋለምሃት27፥8 በዕብራይስጡ የዚህ ሐረግ ትርጕም በትክክል አይታወቅም።

የምሥራቅ ነፋስ እንደሚነፍስበት ቀን፣

በብርቱ ዐውሎ ነፋስ አሳደድሃት።

9ያዕቆብ የመሠዊያ ድንጋዮችን፣

እንደ ኖራ ድንጋይ ፈጭቶ ሲያደቅቃቸው፣

የአሼራን ዐምድና የዕጣን መሠዊያዎችን፣

ከቦታቸው ነቅሎ ሲጥል፣

በዚያን ጊዜ በደሉ ይሰረይለታል፤

ይህም ኀጢአቱን የማስወገዱ ሙሉ ፍሬ ይሆናል።

10የተመሸገባት ከተማ ባዶዋን ቀርታለች፤

እንደ ምድረ በዳም የተተወች ስፍራ ሆናለች፤

ጥጆች በዚያ ይሰማራሉ፤

እዚያም ይተኛሉ፤

ቅርንጫፎቿንም ልጠው ይበላሉ።

11ጫፎቿ ሲደርቁ ይሰበራሉ፤

ሴቶችም መጥተው ይማግዷቸዋል።

ማስተዋል የሌለው ሕዝብ ስለሆነ፣

ፈጣሪው አይራራለትም፤

ያበጀውም አይምረውም።

12በዚያ ቀን ከኤፍራጥስ ወንዝ አንሥቶ እስከ ግብፅ ደረቅ ወንዝ፣ እግዚአብሔር እህሉን ይወቃል፤ እናንተም የእስራኤል ልጆች ሆይ፤ አንድ በአንድ ትሰበሰባላችሁ። 13በዚያ ቀን ታላቅ መለከት ይነፋል፤ በአሦር የጠፉትና በግብፅ የተሰደዱትም መጥተው፣ በተቀደሰው ተራራ በኢየሩሳሌም እግዚአብሔርን ያመልካሉ።

New International Version

Isaiah 27:1-13

Deliverance of Israel

1In that day,

the Lord will punish with his sword—

his fierce, great and powerful sword—

Leviathan the gliding serpent,

Leviathan the coiling serpent;

he will slay the monster of the sea.

2In that day—

“Sing about a fruitful vineyard:

3I, the Lord, watch over it;

I water it continually.

I guard it day and night

so that no one may harm it.

4I am not angry.

If only there were briers and thorns confronting me!

I would march against them in battle;

I would set them all on fire.

5Or else let them come to me for refuge;

let them make peace with me,

yes, let them make peace with me.”

6In days to come Jacob will take root,

Israel will bud and blossom

and fill all the world with fruit.

7Has the Lord struck her

as he struck down those who struck her?

Has she been killed

as those were killed who killed her?

8By warfare27:8 See Septuagint; the meaning of the Hebrew for this word is uncertain. and exile you contend with her—

with his fierce blast he drives her out,

as on a day the east wind blows.

9By this, then, will Jacob’s guilt be atoned for,

and this will be the full fruit of the removal of his sin:

When he makes all the altar stones

to be like limestone crushed to pieces,

no Asherah poles27:9 That is, wooden symbols of the goddess Asherah or incense altars

will be left standing.

10The fortified city stands desolate,

an abandoned settlement, forsaken like the wilderness;

there the calves graze,

there they lie down;

they strip its branches bare.

11When its twigs are dry, they are broken off

and women come and make fires with them.

For this is a people without understanding;

so their Maker has no compassion on them,

and their Creator shows them no favor.

12In that day the Lord will thresh from the flowing Euphrates to the Wadi of Egypt, and you, Israel, will be gathered up one by one. 13And in that day a great trumpet will sound. Those who were perishing in Assyria and those who were exiled in Egypt will come and worship the Lord on the holy mountain in Jerusalem.