ኢሳይያስ 27 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 27:1-13

የእስራኤል ዐርነት መውጣት

1በዚያ ቀን እግዚአብሔር

ተወርዋሪውን እባብ ሌዋታንን፣

የሚጠቀለለውን ዘንዶ ሌዋታንን

በብርቱ፣ በታላቁና በኀይለኛ ሰይፍ ይቀጣዋል፤

የባሕሩንም ግዙፍ አውሬ ይቈራርጠዋል።

2በዚያን ቀን እንዲህ ይባላል፤

“ለመልካሙ የወይን ቦታ ዘምሩለት፤

3እኔ እግዚአብሔር ጠባቂው ነኝ፤

ዘወትር ውሃ አጠጣዋለሁ፤

ስለዚህ ማንም አይጐዳውም፣

ቀንና ሌሊት እጠብቀዋለሁ፤

4እኔ አልቈጣም።

እሾኽና ኵርንችት ምነው በተነሡብኝ!

ለውጊያ በወጣሁባቸው፣

አንድ ላይ ባቃጠልኋቸው!

5አለዚያ ይምጡና መሸሸጊያቸው ያድርጉኝ፤

ከእኔ ጋር ሰላም ይፍጠሩ፤

አዎን፤ ከእኔ ጋር ሰላም ያድርጉ።”

6በሚመጡት ቀናት ያዕቆብ ሥር ይሰድዳል፤

እስራኤልም ያቈጠቍጣል፣ ያብባልም፤

በፍሬያቸውም ምድርን ሁሉ ይሞላሉ።

7የመቷትን እንደ መታቸው፣

እግዚአብሔር እርሷንስ መታትን?

የገደሏትን እንደ ገደላቸው፣

እርሷስ ተገደለችን?

8በጦርነትና በስደት ተፋለምሃት27፥8 በዕብራይስጡ የዚህ ሐረግ ትርጕም በትክክል አይታወቅም።

የምሥራቅ ነፋስ እንደሚነፍስበት ቀን፣

በብርቱ ዐውሎ ነፋስ አሳደድሃት።

9ያዕቆብ የመሠዊያ ድንጋዮችን፣

እንደ ኖራ ድንጋይ ፈጭቶ ሲያደቅቃቸው፣

የአሼራን ዐምድና የዕጣን መሠዊያዎችን፣

ከቦታቸው ነቅሎ ሲጥል፣

በዚያን ጊዜ በደሉ ይሰረይለታል፤

ይህም ኀጢአቱን የማስወገዱ ሙሉ ፍሬ ይሆናል።

10የተመሸገባት ከተማ ባዶዋን ቀርታለች፤

እንደ ምድረ በዳም የተተወች ስፍራ ሆናለች፤

ጥጆች በዚያ ይሰማራሉ፤

እዚያም ይተኛሉ፤

ቅርንጫፎቿንም ልጠው ይበላሉ።

11ጫፎቿ ሲደርቁ ይሰበራሉ፤

ሴቶችም መጥተው ይማግዷቸዋል።

ማስተዋል የሌለው ሕዝብ ስለሆነ፣

ፈጣሪው አይራራለትም፤

ያበጀውም አይምረውም።

12በዚያ ቀን ከኤፍራጥስ ወንዝ አንሥቶ እስከ ግብፅ ደረቅ ወንዝ፣ እግዚአብሔር እህሉን ይወቃል፤ እናንተም የእስራኤል ልጆች ሆይ፤ አንድ በአንድ ትሰበሰባላችሁ። 13በዚያ ቀን ታላቅ መለከት ይነፋል፤ በአሦር የጠፉትና በግብፅ የተሰደዱትም መጥተው፣ በተቀደሰው ተራራ በኢየሩሳሌም እግዚአብሔርን ያመልካሉ።

Japanese Contemporary Bible

イザヤ書 27:1-13

27

イスラエルの解放

1その日、主は恐ろしく鋭い剣で、素早く動く蛇、

とぐろを巻いている蛇、

海の竜であるレビヤタンを殺します。

2イスラエルの解放の日、

民にこの賛歌を歌わせなさい。

3「イスラエルはわたしのぶどう園。

神であるこのわたしが、

実を結ぶぶどうの手入れをする。

毎日水をかけ、昼も夜も、

敵が近づかないように見張る。

4-5イスラエルへの怒りは、もう収まった。

いばらが彼らを煩わせているなら、

ひざまずいて赦しを求めない限り、

この私の敵を焼き払う。

6やがてイスラエルが根を張り、つぼみをつけ、

花を咲かせ、世界をその実で満たす時が来る。」

7-8神はイスラエルの敵を罰したように、

イスラエルを罰したのでしょうか。

そんなことはありません。

敵は息の根を止められました。

しかしイスラエルは、ほんの少し罰を受けただけです。

東からの嵐に吹き飛ばされるように、

遠く離れた地へ追いやられたにすぎません。

9では、なぜ神はそのようにしたのでしょう。

イスラエルの罪をきよめ、

偶像とその祭壇とを取り除くためです。

これらのものは二度と礼拝の対象にはなりません。

10城壁で囲まれた町々はひっそり静まり返り、

家は荒れ、通りには草が茂り、

牛は町をのし歩いて草を食べ、

木の枝を食べるようになります。

11私の国民は枯れ枝のように折られ、

猟師用のたきぎになります。

彼らは鈍い民で頭の回転が遅く、

思考力に欠けています。

それは神に背いているからです。

だから、彼らをお造りになった方は、

少しもあわれみをかけません。

12しかし、穀物の穂を一粒一粒拾い上げるように、

主が彼らを集め、ユーフラテス川から

エジプト国境に及ぶ、広大な打穀場から

選び分ける時がきます。

13その日、大きなラッパが鳴りわたり、

アッシリヤやエジプトで、息も絶え絶えになっている

多くのイスラエル人が救い出され、

聖なる山で主を拝むために

エルサレムへ連れ戻されます。