ኢሳይያስ 26 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 26:1-21

የምስጋና መዝሙር

1በዚያ ቀን ይህ መዝሙር በይሁዳ ምድር ይዘመራል፤

ብርቱ ከተማ አለችን፤

አምላካችን ቅጥሮቿንና ምሽጎቿን፣

ለድነት አድርጓል።

2በእምነቱ የጸና

ጻድቅ የሆነ ሕዝብ ይገባ ዘንድ፣

በሮቿን ክፈቱ።

3በአንተ ላይ ታምናለችና፣

በአንተ የምትደገፈውን ነፍስ

ፈጽመህ በሰላም ትጠብቃታለህ።

4በእግዚአብሔር ለዘላለም ታመኑ፤

ጌታ እግዚአብሔር የዘላለም ዐምባ ነውና።

5በከፍታ የሚኖሩትን ዝቅ ዝቅ ያደርጋል፤

ከፍ ከፍ ያለችውን ከተማ ያዋርዳል፤

ወደ ምድር ይጥላታል፤

ከትቢያም ጋር ይደባልቃታል።

6እግር፣

የተጨቋኞች እግር፣

የድኾች ኮቴ ይረግጣታል።

7የጻድቃን መንገድ ቅን ናት፤

አንተ ቅን የሆንህ ሆይ፤

የጻድቃንን መንገድ ታቃናለህ።

8እግዚአብሔር ሆይ፤ በሕግህ26፥8 ወይም፣ በፍርድህ ተብሎ መተርጐም ይችላል። ጐዳና በመሄድ፣

አንተን ተስፋ አድርገናል፤

ስምህና ዝናህ፣

የልባችን ምኞት ነው።

9ነፍሴ በሌሊት ትናፍቅሃለች፤

መንፈሴም በውስጤ ትፈልግሃለች።

ፍርድህ ወደ ምድር በመጣ ጊዜ፣

የዓለም ሕዝቦች ጽድቅን ይማራሉ።

10ክፉዎች ርኅራኄ ቢደረግላቸው እንኳ፣

ጽድቅን አይማሩም፤

በቅንነት ምድር እንኳ ክፋትን ያደርጋሉ፤

የእግዚአብሔርንም ግርማ አያስተውሉም።

11እግዚአብሔር ሆይ፤ ክንድህ ከፍ ከፍ ብሏል፤

እነርሱ ግን አላስተዋሉም፤

ለሕዝብህ ያለህን ቅናት ይዩ፤ ይፈሩም፤

ለጠላቶችህም የተዘጋጀው እሳት ይብላቸው።

12እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ሰላምን መሠረትህልን፤

የሠራነውንም ሁሉ አንተ አከናወንህልን።

13እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ፤

ከአንተ ሌላ ሌሎች ጌቶች ገዝተውናል፤

እኛ ግን የአንተን ስም ብቻ እናከብራለን።

14እነርሱ ሞተዋል፤ ከእንግዲህ በሕይወት አይኖሩም፤

መንፈሳቸው ተነሥቶ አይመጣም።

አንተ ቀጣሃቸው፤ አጠፋሃቸው፤

መታሰቢያቸውንም ሁሉ ደመሰስህ።

15እግዚአብሔር ሆይ፤ ሕዝብን አበዛህ፤

ሕዝብን አበዛህ።

ክብሩን ለራስህ አደረግህ፤

የምድሪቱንም ወሰን ሁሉ አሰፋህ።

16እግዚአብሔር ሆይ፤ በተጨነቁ ጊዜ ወደ አንተ መጡ፤

በገሠጽሃቸውም ጊዜ፣

በለሆሳስ ድምፅ ይጸልያሉ26፥16 በዕብራይስጡ የዚህ ሐረግ ትርጕም በትክክል አይታወቅም።

17እግዚአብሔር ሆይ፤ የፀነሰች ሴት ልትወልድ ስትል፣

በምጥ እንደምትጨነቅና እንደምትጮኽ፣

እኛም በፊትህ እንዲሁ ሆነናል።

18አረገዝን በምጥም ተጨነቅን፤

ነገር ግን ነፋስን ወለድን፤

ለምድርም ድነትን አላመጣንም፤

የዓለምን ሕዝብ አልወለድንም።

19ነገር ግን ሙታንህ ሕያዋን ይሆናሉ፤

በድናቸውም ይነሣል።

እናንት በዐፈር ውስጥ የምትኖሩ፣

ተነሡ፤ በደስታም ዘምሩ።

ጠልህ እንደ ንጋት ጠል ነው፤

ምድር ሙታንን ትወልዳለች።

20ሕዝቤ ሆይ፤ ሂድ ወደ ቤትህ ግባ፤

በርህን ከኋላህ ዝጋ፤

ቍጣው እስኪያልፍ ድረስ፣

ለጥቂት ቀን ተሸሸግ።

21በምድር ላይ የሚኖረውን ሕዝብ ስለ ኀጢአቱ ለመቅጣት፣

እነሆ፤ እግዚአብሔር ከመኖሪያው ወጥቶ ይመጣል፤

ምድር በላይዋ የፈሰሰውን ደም ትገልጣለች፤

የተገደሉትንም ከእንግዲህ አትሸሽግም።

Ketab El Hayat

إشعياء 26:1-21

أنشودة تسبيح

1فِي ذَلِكَ الْيَوْمِ يَتَرَدَّدُ هَذَا النَّشِيدُ فِي أَرْضِ يَهُوذَا: لَنَا مَدِينَةٌ مَنِيعَةٌ، يَجْعَلُ الرَّبُّ الْخَلاصَ أَسْوَاراً وَمَتْرَسَةً. 2افْتَحُوا الأَبْوَابَ لِتَدْخُلَ الأُمَّةُ الْبَارَّةُ الَّتِي حَافَظَتْ عَلَى الأَمَانَةِ. 3أَنْتَ تَحْفَظُ ذَا الرَّأْيِ الثَّابِتِ سَالِماً لأَنَّهُ عَلَيْكَ تَوَكَّلَ. 4اتَّكِلُوا عَلَى الرَّبِّ إِلَى الأَبَدِ، لأَنَّ الرَّبَّ اللهَ هُوَ صَخْرُ الدُّهُورِ. 5لَقَدْ أَذَلَّ السَّاكِنِينَ فِي الْعَلاءِ، وَخَفَضَ الْمَدِينَةَ الْمُتَشَامِخَةَ. سَاوَاهَا بِالأَرْضِ وَطَرَحَهَا إِلَى التُّرَابِ، 6فَدَاسَتْهَا أَقْدَامُ الْبَائِسِ وَالْفَقِيرِ.

7سَبِيلُ الصِّدِّيقِ اسْتِقَامَةٌ، لأَنَّكَ تَجْعَلُ طَرِيقَ الْبَارِّ مُمَهَّدَةً. 8انْتَظَرْنَاكَ يَا رَبُّ بِشَوْقٍ فِي طَرِيقِ أَحْكَامِكَ. تَتُوقُ النَّفْسُ إِلَى اسْمِكَ وَتَشْتَهِي ذِكْرَكَ. 9تَتُوقُ إِلَيْكَ نَفْسِي فِي اللَّيْلِ، وَفِي الصَّبَاحِ تَشْتَاقُ إِلَيْكَ رُوحِي. عِنْدَمَا تَسُدْ أَحْكَامُكَ فِي الأَرْضِ يَتَعَلَّمْ أَهْلُهَا الْعَدْلَ. 10إِنْ أَبْدَيْتَ رَحْمَتَكَ لِلْمُنَافِقِ فَإِنَّهُ لَا يَتَعَلَّمُ الْعَدْلَ، بَلْ يَظَلُّ يَرْتَكِبُ الشَّرَّ حَتَّى فِي أَرْضِ الاسْتِقَامَةِ، وَلا يَعْبَأُ بِجَلالِ الرَّبِّ.

11يَا رَبُّ إِنَّ يَدَكَ مُرْتَفِعَةٌ وَهُمْ لَا يَرَوْنَهَا، فَدَعْهُمْ يُشَاهِدُونَ غَيْرَتَكَ عَلَى شَعْبِكَ، وَيَخْزَوْنَ. لِتَلْتَهِمْهُمُ النَّارُ الَّتِي ادَّخَرْتَهَا لأَعْدَائِكَ. 12يَا رَبُّ أَنْتَ تَجْعَلُ سَلاماً لَنَا لأَنَّكَ صَنَعْتَ لَنَا كُلَّ أَعْمَالِنَا. 13أَيُّهَا الرَّبُّ إِلَهُنَا، قَدْ سَادَ عَلَيْنَا أَسْيَادٌ سِوَاكَ، وَلَكِنَّنَا لَا نَعْتَرِفُ إِلّا بِاسْمِكَ وَحْدَهُ. 14هُمْ أَمْوَاتٌ لَا يَحْيَوْنَ وَأَشْبَاحٌ لَا تَقُومُ. عَاقَبْتَهُمْ وَأَهْلَكْتَهُمْ وَأَبَدْتَ ذِكْرَهُمْ.

15قَدْ زِدْتَ الأُمَّةَ يَا رَبُّ وَنَمَّيْتَهَا، فَتَمَجَّدَتْ، وَوَسَّعْتَ تُخُومَهَا فِي الأَرْضِ.

الرجاء في القيامة

16يَا رَبُّ قَدْ طَلَبُوكَ فِي الْمِحْنَةِ، وَسَكَبُوا دُعَاءَهُمْ عِنْدَ تَأَدِيبِكَ لَهُمْ، 17وَكُنَّا فِي حَضْرَتِكَ يَا رَبُّ كَالْحُبْلَى الْمُشْرِفَةِ عَلَى الْوِلادَةِ، الَّتِي تَتَلَوَّى وَتَصْرُخُ فِي مَخَاضِهَا. 18حَبِلْنَا وَتَلَوَّيْنَا وَلَكِنَّنَا كُنَّا كَمَنْ يَتَمَخَّضُ عَنْ رِيحٍ. لَمْ نُخَلِّصِ الأَرْضَ وَلَمْ يُوْلَدْ مَنْ يُقِيمُ فِيهَا فَتَصِيرُ آهِلَةً عَامِرَةً. 19وَلَكِنَّ أَمْوَاتَكَ يَحْيَوْنَ، وَتَقُومُ أَجْسَادُهُمْ، فَيَا سُكَّانَ التُّرَابِ اسْتَيْقِظُوا وَاشْدُوا بِفَرَحٍ لأَنَّ طَلَّكَ هُوَ نَدىً مُتَلألِئٌ، جَعَلْتَهُ يَهْطِلُ عَلَى أَرْضِ الأَشْبَاحِ.

20تَعَالَوْا يَا شَعْبِي وَادْخُلُوا إِلَى مَخَادِعِكُمْ، وَأَوْصِدُوا أَبْوَابَكُمْ خَلْفَكُمْ. تَوَارَوْا قَلِيلاً حَتَّى يَعْبُرَ السَّخَطُ. 21وَانْظُرُوا فَإِنَّ الرَّبَّ خَارِجٌ مِنْ مَكَانِهِ لِيُعَاقِبَ سُكَّانَ الأَرْضِ عَلَى آثَامِهِمْ، فَتَكْشِفُ الأَرْضُ عَمَّا سُفِكَ عَلَيْهَا مِنْ دِمَاءٍ وَلا تُغَطِّي قَتْلاهَا فِيمَا بَعْدُ.