ኢሳይያስ 22 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 22:1-25

ስለ ኢየሩሳሌም የተነገረ ትንቢት

1ስለ ራእይ ሸለቆ የተነገረ ንግር፤

እስቲ ምን ቢጨንቃችሁ ነው

ሁላችሁም ሰገነት ላይ የወጣችሁት?

2አንቺ ጫጫታ የሞላብሽ ከተማ፤

የውካታና የፈንጠዝያ ከተማ ሆይ፤

የተገደሉብሽ በሰይፍ የተሠዉ አይደሉም፤

በጦርነትም አልሞቱም።

3መሪዎችሽ በሙሉ በአንድ ላይ ሸሽተዋል፤

ቀስት እንኳ ሳያነሡ ተማርከዋል፤

ጠላት ገና በሩቅ ሳለ የሸሻችሁ ሁሉ፣

ተይዛችሁ በአንድነት ታስራችኋል።

4ስለዚህ፣ “ከእኔ ራቁ፤

አምርሬ ላልቅስበት፣

ስለ ሕዝቤ ጥፋት፣

ልታጽናኑኝ አትሞክሩ” አልሁ።

5ጌታ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

በራእይ ሸለቆ፣

የመጯጯኺያ፣ የመረገጥና የሽብር፣

ቅጥሮችን የማፈራረስ፣

ወደ ተራሮችም የሚጮኽበት ቀን አለው።

6ኤላም የፍላጻ ሰገባ፣

ፈረሷንና ሠረገላዋን አዘጋጀች፤

ቂርም ጋሻዋን አነገበች።

7መልካሞቹ ሸለቆዎችሽ በሠረገሎች ተሞልተዋል፤

ፈረሰኞችም በከተማዪቱ በሮች ላይ ቆመዋል፤

8የይሁዳን መከላከያዎች ገልጧል።

በዚያን ቀን በዱር ግምጃ ቤት የነበረውን፣

የጦር መሣሪያ ተመለከትህ፤

9የዳዊት ከተማ

ብዙ ፍርስራሾች እንዳሉበት አያችሁ፤

በታችኛውም ኵሬ፣

ውሃ አጠራቀማችሁ።

10በኢየሩሳሌም ያሉትን ቤቶች ቈጠራችሁ፤

ቅጥሩን ለመጠገንም ቤቶቹን አፈረሳችሁ።

11ለጥንቱ ኵሬ ውሃ የሚሆን፣

በሁለቱ ቅጥሮች መካከል ውሃ ማጠራቀሚያ ሠራችሁ፤

ነገር ግን ይህን ያደረገውን አልተመለከታችሁም፤

ቀድሞ ዐቅዶ የሠራውንም አላስታወሳችሁም።

12በዚያን ቀን ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

እንድታለቅሱና በዋይታ እንድትጮኹ፣

ጠጕራችሁን እንድትነጩ

ማቅም እንድትለብሱ ጠራችሁ።

13ነገር ግን እነሆ፤ ተድላና ደስታ፣

ፍሪዳ መጣልና ሙክት ማረድ፣

ሥጋ መብላትና የወይን ጠጅ መጠጣት አለ፤

“እንብላ እንጠጣ፣

ነገ እንሞታለንና” አላችሁ።

14የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ይህን ገለጠልኝ፤ እንዲህም ሲል በጆሮዬ ሰማሁ፤ “ይህ ኀጢአት እስከምትሞቱበት ቀን ድረስ አይሰረይላችሁም” ይላል ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

15ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ሂድና ይህን መጋቢ፣

የቤቱንም ኀላፊ ሳምናስን እንዲህ በለው፤

16‘እዚህ ምን ታደርጋለህ?

በዚህ ስፍራ ለራስህ መቃብርን እንድታዘጋጅ፣

በከፍታውም ላይ መቀበሪያህን እንድትወቅር፣

ሬሳህ የሚያርፍበትንም ዐለት እንድትጠርብ ማን ፈቀደልህ?’

17“አንተ ኀያል ሰው ሆይ፤ ተጠንቀቅ፤

እግዚአብሔር አጥብቆ ሊይዝህ፣ በእጆቹም ጨብጦ ሊወረውርህ ነው።

18አዙሮ አዙሮ እንደ ሩር አጡዞ፣

ወደ ሰፊ አገር ይወነጭፍሃል፤

አንተ የጌታህ ቤት ዕፍረት!

በዚያ ትሞታለህ፤

የክብር ሠረገሎችህም እዚያ ይቀራሉ።

19ከማዕረግህ አወርድሃለሁ፤

ከኀላፊነትህም ትባረራለህ።

20“በዚያን ቀን አገልጋዬን፣ የኬልቅያስን ልጅ ኤልያቄምን እጠራለሁ፤ 21መጐናጸፊያህን አለብሰዋለሁ፤ መታጠቂያህን አስታጥቀዋለሁ፤ ሥልጣንህንም አስረክበዋለሁ። እርሱም በኢየሩሳሌም ለሚኖሩ፣ ለይሁዳም ቤት አባት ይሆናል። 22የዳዊትን ቤት መክፈቻ በጫንቃው ላይ አደርጋለሁ፤ እርሱ የሚከፍተውን ማንም አይዘጋም፤ የሚዘጋውንም ማንም አይከፍትም። 23በአስተማማኝ ስፍራ እንደ ካስማ እተክለዋለሁ፤ ለአባቱም ቤት የክብር ዙፋን22፥23 ወይም፣ መቀመጫ ተብሎ መተርጐም ይችላል። ይሆናል። 24የቤተ ሰቡ ክብር፣ ልጅና የልጅ ልጅ፣ እንዲሁም ከማሰሮ ጀምሮ እስከ ጋን ድረስ ያለ የቤት ዕቃ ሁሉ በእርሱ ላይ ይንጠለጠላል።

25“በዚያ ቀን” ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣ “በአስተማማኝ ስፍራ የተተከለ ካስማ ይነቀላል፤ ተሰብሮም ይወድቃል፤ በእርሱም ላይ የተንጠለጠለው ሸክም ወድቆ ይከሰከሳል፤” እግዚአብሔር ይህን ተናግሯልና።

Ketab El Hayat

إشعياء 22:1-25

نبوءة عن أورشليم

1نُبُوءَةٌ بِشَأْنِ أُورُشَلِيمَ: مَاذَا حَدَثَ حَتَّى إِنَّكُمْ جَمِيعاً صَعِدْتُمْ إِلَى سُطُوحِ الْمَنَازِلِ؟ 2أَيَّتُهَا الْمَدِينَةُ الْمُمْتَلِئَةُ جَلَبَةً، الْعَجَّاجَةُ الْمَرِحَةُ، إِنَّ قَتْلاكِ لَيْسُوا قَتْلَى سَيْفٍ أَوْ صَرْعَى حَرْبٍ. 3قَدْ فَرَّ رُؤَسَاؤُكِ جَمِيعاً. أُسِرُوا مِنْ غَيْرِ مُقَاوَمَةٍ. وَسُبِيَ كُلُّ مَنْ عُثِرَ عَلَيْهِ، مَعَ أَنَّهُمْ هَرَبُوا بَعِيداً. 4لِذَلِكَ أَقُولُ: «ابْتَعِدُوا عَنِّي لأَبْكِيَ بِمَرَارَةٍ، لَا تَتَكَبَّدُوا جَهْداً فِي تَعْزِيَتِي مِنْ أَجْلِ دَمَارِ ابْنَةِ شَعْبِي». 5لأَنَّ لِلسَّيِّدِ الرَّبِّ الْقَدِيرِ فِي أُورُشَلِيمَ يَوْماً يَبُثُّ فِيهِ الرُّعْبَ، وَالذِّلَّةَ، وَالْفَوْضَى. فِيهِ يَنْقُبُ أَهْلُهَا الأَسْوَارَ وَيَسْتَجِيروُنَ بِالْجِبَالِ. 6إِذْ أَنَّ عِيلامَ قَدْ حَمَلَتِ السِّهَامَ وَاجْتَمَعَتْ بِمَرْكَبَاتٍ وَفُرْسَانٍ، وَقِيرَ جَرَّدَتِ الدُّرُوعَ، 7فَاكْتَظَّتْ خَيْرُ أَوْدِيَتِكِ بِالْمَرْكَبَاتِ، وَاصْطَفَّ الْفُرْسَانُ عِنْدَ الْبَوَّابَاتِ، 8لأَنَّ الرَّبَّ هَتَكَ سِتْرَ يَهُوذَا. فِي ذَلِكَ الْيَوْمِ تَبْحَثُونَ عَنْ سِلاحِ بَيْتِ الْغَابَةِ، 9وَتَجِدُونَ أَنَّ صُدُوعَ مَدِينَةِ دَاوُدَ قَدْ كَثُرَتْ، وَتَجْمَعُونَ الْمِيَاهَ مِنَ الْبُحَيْرَةِ السُّفْلَى، 10ثُمَّ تَعُدُّونَ بُيُوتَ أُورُشَلِيمَ وَتَهْدِمُونَ بَعْضاً مِنْهَا لِتُحَصِّنُوا السُّورَ. 11وَتَبْنُونَ خَزَّاناً بَيْنَ السُّورَيْنِ لِتَخْزِينِ مَاءِ الْبِرْكَةِ الْقَدِيمَةِ مِنْ غَيْرِ أَنْ تَأَبَهُوا لِبَانِيهَا، أَوْ تَكْتَرِثُوا لِمَنْ صَمَّمَهَا مُنْذُ زَمَنٍ بَعِيدٍ. 12فِي ذَلِكَ الْيَوْمِ يَدْعُوكُمُ السَّيِّدُ الرَّبُّ الْقَدِيرُ لِلْبُكَاءِ وَالنَّوْحِ وَحَلْقِ الشَّعْرِ وَالتَّنَطُّقِ بِالْمُسُوحِ. 13وَلَكِنَّكُمُ انْهَمَكْتُمْ بِالْفَرَحِ وَالسُّرُورِ وَذَبْحِ الثِّيَرانِ وَتَضْحِيَةِ الْغَنَمِ وَأَكْلِ اللَّحْمِ وَشُرْبِ الْخَمْرِ قَائِلِينَ: «لِنَأْكُلْ وَنَشْرَبْ لأَنَّنَا غَداً نَمُوتُ». 14فَقَالَ لِي الْقَدِيرُ: «لَنْ تُغْفَرَ لَكُمْ آثَامُكُمْ حَتَّى تَمُوتُوا».

15هَكَذَا قَالَ الرَّبُّ الْقَدِيرُ: «تَوَجَّهْ إِلَى شَبْنَا رَئِيسِ دِيوَانِ الْقَصْرِ وَقُلْ لَهُ: 16مَالَكَ هُنَا، وَمَنْ لَكَ حَتَّى نَقَرْتَ لِنَفْسِكَ ضَرِيحاً، أَيُّهَا النَّاقِرُ لَهُ قَبْراً فِي الأَعَالِي، وَالنَّاحِتُ لِنَفْسِهِ مَسْكَناً فِي الصَّخْرِ؟ 17هَا الرَّبُّ مُزْمِعٌ أَنْ يَطْرَحَكَ بِعُنْفٍ أَيُّهَا الْجَبَّارُ وَيُمْسِكَكَ بِقُوَّةٍ، 18وَيُلَوِّحَ بِكَ تَلْوِيحاً، وَيَقْذِفَكَ كَكُرَةٍ فِي أَرْضٍ وَاسِعَةٍ، فَتَمُوتُ هُنَاكَ، وَهُنَاكَ أَيْضاً تُطْرَحُ مَرْكَبَاتُ مَجْدِكَ يَا عَارَ بَيْتِ سَيِّدِكَ. 19وَأَطْرُدُكَ مِنْ مَنْصِبِكَ فَتُعْزَلُ مِنْ مَقَامِكَ.

20فِي ذَلِكَ الْيَوْمِ أَدْعُو عَبْدِي أَلْيَاقِيمَ بنَ حِلْقِيَّا، 21وَأَخْلَعُ عَلَيْهِ حُلَّتَكَ، وَأَشُدُّهُ بِمِنْطَقَتِكَ، وَأَعْهَدُ بِسُلْطَانِكَ إِلَى يَدِهِ، فَيُصْبِحُ أَباً لِكُلِّ سُكَّانِ أُورُشَلِيمَ وَلِبَيْتِ يَهُوذَا، 22وَأُعْطِيهِ السُّلْطَةَ عَلَى جَمِيعِ شَعْبِي، فَمَا يَأْمُرْ بِهِ يُطَعْ. 23وَأُرَسِّخُهُ كَوَتَدٍ فِي مَوْضِعٍ أَمِينٍ، فَيُصْبِحُ عَرْشَ مَجْدٍ لِبَيْتِ أَبِيهِ. 24وَيَضَعُونَ عَلَيْهِ كُلَّ مَجْدِ بَيْتِ أَبِيهِ بِفُرُوعِهِ وَأُصُولِهِ، كُلَّ آنِيَةٍ صَغِيرَةٍ مِنْ آنِيَةِ الطُّسُوسِ إِلَى آنِيَةِ القَنَانِيِّ. 25وَلَكَنَّ الرَّبَّ الْقَدِيرَ يَقُولُ، فِي ذَلِكَ الْيَومِ يُقْتَلَعُ الْوَتَدُ الْمُتَرَسِّخُ بِإِحْكَامٍ مِنْ مَوْضِعِهِ الأَمِينِ وَيُسْتأْصَلُ وَيُطْرَحُ عَلَى الأرْضِ وَيَبِيدُ مَعَهُ كُلُّ الَّذِينَ اتَّكَلُوا عَلَيْهِ».