ኢሳይያስ 21 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 21:1-17

በባቢሎን ላይ የተነገረ ትንቢት

1በባሕሩ ዳር ባለው ምድረ በዳ ላይ የተነገረ ንግር፤

ዐውሎ ነፋስ ከደቡብ እየጠራረገ እንደሚመጣ፣

ወራሪ ከአሸባሪ ምድር፣

ከምድረ በዳ ይመጣል።

2የሚያስጨንቅ ራእይ አየሁ፤

ከሓዲ አሳልፎ ይሰጣል፤ ዘራፊ ይዘርፋል።

ኤላም ሆይ፤ ተነሺ፤ ሜዶን ሆይ፤ ክበቢ፤

እርሷ ያደረሰችውን ሥቃይ ሁሉ አስቀራለሁ።

3ወገቤ በዚህ ሥቃይ ተሞላ፤

በምጥ ላይ እንዳለች ሴት ጭንቅ ያዘኝ፤

በሰማሁት ነገር ተንገዳገድሁ፤

ባየሁትም ነገር ተሸበርሁ።

4ልቤ ተናወጠ፤

ፍርሀት አንቀጠቀጠኝ፤

የጓጓሁለት ውጋጋን፣

ታላቅ ፍርሀት አሳደረብኝ።

5ማእዱን አሰናዱ፤

ምንጣፉን አነጠፉ፤

በሉ፤ ጠጡ!

እናንት ሹማምት ተነሡ፤

ጋሻውን በዘይት ወልውሉ!

6ጌታ እንዲህ አለኝ፤

“ሂድ፤ ጠባቂ አቁም፤

ያየውንም ይናገር፤

7በፈረሶች የሚሳብ፣

ሠረገሎችን ሲያይ፣

በአህያ ላይ የሚቀመጡትን፣

በግመል የሚጋልቡትን ሲመለከት፣

ያስተውል፤

በጥንቃቄም ያስተውል።”

8ጠባቂው ጮኸ፤21፥8 የሙት ባሕር ጥቅልልና የሱርስቱ ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የማሶሬቱ ቅጅ ግን፣ አንበሳ ጮኸ ይላል። እንዲህም አለ፤

“ጌታ ሆይ፤ በየቀኑ ማማ ላይ ቆሜአለሁ፤

በየሌሊቱም በቦታዬ አለሁ።

9እነሆ፤ አንድ ሰው በፈረሶች በሚሳብ

በሠረገላ መጥቷል፤

እንዲህም ሲል መለሰ፣

‘ባቢሎን ወደቀች፣ ወደቀች!

የአማልክቷም ምስሎች ሁሉ፣

ተሰባብረው ምድር ላይ ወደቁ!’ ”

10በዐውድማ ላይ የተወቃህ ሕዝቤ ሆይ፤

ከሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

ከእስራኤል አምላክ፣

የሰማሁትን እነግርሃለሁ።

በኤዶም ላይ የተነገረ ትንቢት

11ስለ ኤዶም የተነገረ ንግር፤

አንዱ ከሴይር ጠርቶኝ፣

“ጠባቂ ሆይ፤ ሊነጋ ምን ያህል ቀረው?

ጠባቂ ሆይ፤ ሊነጋ ምን ያህል ቀረው?” አለኝ።

12ጠባቂውም መለሰ፤

“ይነጋል፤ ግን ተመልሶ ይመሻል፤

መጠየቅ ከፈለጋችሁ፣ ጠይቁ፤

ነገር ግን ተመልሳችሁ ኑ” አለ።

በዐረብ ላይ የተነገረ ትንቢት

13ስለ ዐረብ አገር የተነገረ ንግር፤

እናንተ በዐረብ ዱር የምትሰፍሩ፣

የድዳን ሲራራ ነጋዴዎች፣

14ለተጠሙ ውሃ አምጡ።

በቴማን የምትኖሩ፣

ለስደተኞች ምግብ አምጡ።

15ከሰይፍ፣

ከተመዘዘ ሰይፍ፣

ከተደገነ ቀስት፣

ከተፋፋመ ጦርነት ሸሽተዋልና።

16ጌታም እንዲህ አለኝ፤ “በውል የተቀጠረ ሠራተኛ ቀን እንደሚቈጥር፣ የቄዳር ክብር በአንድ ዓመት ውስጥ ያበቃለታል። 17የተረፈው ቀስተኛ፣ የቄዳር ጦረኛ ጥቂት ይሆናል፤ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ተናግሯልና።”

Ketab El Hayat

إشعياء 21:1-17

نبوءة على بابل

1نُبُوءَةٌ بِشَأْنِ بَابِلَ: كَمَا تَعْبُرُ الزَّوَابِعُ فِي النَّقَبِ، هَكَذَا يُقْبِلُ الْغَازِي مِنَ الصَّحْرَاءِ، مِنْ أَرْضِ الرُّعْبِ. 2لَقَدْ أُعْلِنَتْ لِي رُؤْيَا رَهِيبَةٌ: رَأَيْتُ النَّاهِبَ يَنْهَبُ، وَالْمُدَمِّرَ يُدَمِّرُ. فَاصْعَدِي يَا عِيلامُ، وَحَاصِرِي يَا مَادِي، لأَنَّنِي سَأُسْكِتُ كُلَّ الأَنِينِ الَّذِي سَبَّبَهُ. 3لِذَلِكَ امْتَلَأَتْ حَقْوايَ أَلَماً، وَانْتَابَنِي مَخَاضٌ كَمَخَاضِ الْوَالِدَةِ. فَقَدْتُ الْوَعْيَ مِنْ جَرَّاءِ مَا سَمِعْتُ، وَذُهِلْتُ مِمَّا رَأَيْتُ 4تَحَيَّرَ قَلْبِي، وَأَرْعَبَنِي الْفَزَعُ، فَتَحَوَّلَ لَيْلِي الَّذِي كُنْتُ أَتُوقُ إِلَيْهِ إِلَى رَعْدَةٍ. 5أَعَدُّوا مَائِدَةً وَفَرَشُوا السَّجَاجِيدَ، أَكَلُوا وَشَرِبُوا، فَانْهَضُوا يَا أُمَرَاءُ، وَادْهِنُوا بِالزَّيْتِ تُرُوسَكُمْ.

6لأَنَّهُ هَكَذَا قَالَ الرَّبُّ لِي: اذْهَبْ وَأَقِمْ رَقِيباً لِيُعْلِنَ مَا يَرَاهُ. 7وَعِنْدَمَا يُشَاهِدُ رَاكِبِينَ فُرْسَاناً أَزْوَاجاً أَزْوَاجاً، أَوْ رَاكِبِينَ عَلَى حَمِيرٍ، وَرَاكِبِينَ عَلَى جِمَالٍ، فَلْيُصْغِ إِصْغَاءً شَدِيداً. 8ثُمَّ هَتَفَ الرَّقِيبُ: هَا أَنَا أَقِفُ عَلَى بُرْجِ الْمُرَاقَبَةِ يَوْماً بَعْدَ يَوْمٍ أَيُّهَا الرَّبُّ، وَأَقُوْمُ عَلَى الْمَحْرَسِ طَوَالَ اللَّيْلِ. 9فَهَا رَكْبٌ قَادِمٌ، فُرْسَانٌ أَزْوَاجٌ أَزْوَاجٌ. فَأَجَابَ: سَقَطَتْ سَقَطَتْ بَابِلُ وَتَحَطَّمَتْ سَائِرُ أَصْنَامِهَا عَلَى الأَرْضِ. 10آهِ يَا شَعْبِيَ الْمَطْحُونَ وَالْمُشَتَّتَ، لَقَدْ أَنْبَأْتُكُمْ بِكُلِّ مَا سَمِعْتُهُ مِنَ الرَّبِّ الْقَدِيرِ إِلَهِ إِسْرَائِيلَ.

نبوءة على أدوم

11نُبُوءَةٌ بِشَأْنِ أَدُومَ: هَتَفَ صَارِخٌ مِنْ سَعِيرَ: «يَا رَقِيبُ، مَاذَا بَقِيَ مِنَ اللَّيْلِ؟ أَمَا آنَ لَهُ أَنْ يَنْتَهِيَ؟» 12فَأَجَابَ الرَّقِيبُ: «أَشْرَقَ الصُّبْحُ وَلَكِنَّ اللَّيْلَ أَقْبَلَ مَعَهُ، فَإِنْ رَغِبْتُمْ فِي السُّؤَالِ فَاسْأَلُوا، ثُمَّ تَعَالَوْا وَارْجِعُوا إِلَى اللهِ».

13نُبُوءَةٌ بِشَأْنِ شِبْهِ الْجَزِيرَةِ الْعَرَبِيَّةِ: سَتَبِيتِينَ فِي صَحَارِي بِلادِ الْعَرَبِ يَا قَوَافِلَ الدَّدَانِيِّينَ، 14فَاحْمِلَوا يَا أَهْلَ تَيْمَاءَ الْمَاءَ لِلْعَطْشَانِ، وَاسْتَقْبِلُوا الْهَارِبِينَ بِالْخُبْزِ، 15لأَنَّهُمْ قَدْ فَرُّوا مِنَ السَّيْفِ الْمَسْلُولِ، وَالْقَوْسِ الْمُتَوَتِّرِ، وَمِنْ وَطِيسِ الْمَعْرَكَةِ. 16لأَنَّهُ هَذَا مَا قَالَهُ لِي الرَّبُّ: فِي غُضُونِ سَنَةٍ مَمَاثِلَةٍ لِسَنَةِ الأَجِيرِ يَفْنَى كُلُّ مَجْدِ قِيدَارَ، 17وَتَكُونُ بَقِيَّةُ الرُّمَاةِ، الأَبْطَالُ مِنْ أَبْنَاءِ قِيدَارَ، قِلَّةً. لأَنَّ الرَّبَّ إِلَهَ إِسْرَائِيلَ قَدْ تَكَلَّمَ.