ኢሳይያስ 19 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 19:1-25

ስለ ግብፅ የተነገረ ትንቢት

1ስለ ግብፅ የተነገረ ንግር፤

እነሆ፤ እግዚአብሔር በፈጣን ደመና ላይ ተቀምጦ

ወደ ግብፅ ይመጣል፤

የግብፅ ጣዖቶች በፊቱ ይርዳሉ፤

የግብፃውያንም ልብ በውስጣቸው ይቀልጣል።

2“ግብፃዊውን በግብፃዊው ላይ አስነሣለሁ፤

ወንድም ወንድሙን፣

ባልንጀራ ባልንጀራውን፣

ከተማም ከተማን፣

መንግሥትም መንግሥትን ይወጋል።

3የግብፃውያን ልብ ይሰለባል፤

ዕቅዳቸውንም መና አስቀራለሁ፤

እነርሱም ጣዖታትንና የሙታንን መናፍስት፣

መናፍስት ጠሪዎችንና ጠንቋዮችን ምክር ይጠይቃሉ።

4ግብፃውያንን አሳልፌ

ለጨካኝ ጌታ ክንድ እሰጣቸዋለሁ፤

አስፈሪ ንጉሥም ይገዛቸዋል”

ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

5የአባይ ወንዝ ይቀንሳል፤

ውሃውም እየጐደለ ይሄዳል።

6መስኖዎቹ ይከረፋሉ፤

የግብፅ ጅረቶች ይጐድላሉ፤ ይጠፋሉም።

ደንገሉና ቄጠማውም ይጠወልጋል፤

7እንዲሁም በአባይ ዳር፣

በወንዙ መፋሰሻ ላይ ያሉት ተክሎች ይጠወልጋሉ።

በአባይ ዳር የተዘራው ዕርሻ ሁሉ፣

በነፋስ ይወሰዳል፤ ምንም አይቀርም።

8ዓሣ አጥማጆች ያዝናሉ፤

በአባይ ወንዝ ላይ መንጠቋቸውን የሚወረውሩ ሁሉ ያለቅሳሉ፤

በውሃ ላይ መረባቸውን የሚጥሉ ሁሉ፣

ጕልበታቸው ይዝላል።

9የተነደፈ የተልባ እግር የሚፈትሉ፣

የተባዘተ ጥጥ የሚሠሩ ሸማኔዎችም ተስፋ ይቈርጣሉ።

10ልብስ ሠሪዎች ያዝናሉ፤

ደመወዝተኞችም ልባቸው ይሰበራል።

11የጣኔዎስ አለቆች በጣም ሞኞች ናቸው፤

የፈርዖን ጠቢባን ምክራቸው የማይረባ ነው፤

ፈርዖንን፣ “እኔ ከጥበበኞች አንዱ ነኝ፤

የጥንት ነገሥታትም ደቀ መዝሙር ነኝ”

እንዴት ትሉታላችሁ?

12የእናንተ ጠቢባን አሁን የት አሉ?

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

በግብፅ ላይ ያሰበውን ነገር፣

እስቲ ያሳዩአችሁ፤ ያሳውቋችሁም።

13የጣኔዎስ አለቆች ተሞኝተዋል፤

የሜምፊስ ሹማምት ተታልለዋል፤

የሕዝቧ ዋና ዋናዎች፣

ግብፅን አስተዋታል።

14እግዚአብሔር የድንዛዜን መንፈስ አፍስሶባቸዋል፤

ሰካራም በትፋቱ ዙሪያ እንደሚንገዳገድ፣

ግብፅንም በምታደርገው ነገር ሁሉ

እንድትንገዳገድ አደረጓት።

15ራስም ይሁን ጅራት፣ የዘንባባ ዝንጣፊም ይሁን ደንገል፣

ለግብፅ የሚያደርጉላት አንዳች ነገር የለም።

16በዚያን ቀን ግብፃውያን እንደ ሴት ይሆናሉ፤ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር በእነርሱ ላይ ካነሣው ክንዱ የተነሣ በፍርሀት ይንቀጠቀጣሉ። 17የይሁዳ ምድር በግብፅ ላይ ሽብር ትነዛለች፤ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር በእነርሱ ላይ ካቀደው የተነሣ፣ ስለ ይሁዳ ወሬ የሰማ ሁሉ ይሸበራል።

18በዚያ ቀን አምስት የግብፅ ከተሞች በከነዓን ቋንቋ ይናገራሉ፤ የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔርም ወገን ለመሆን ቃል ኪዳን ይገባሉ፤ ከእነዚህም ከተሞች አንዲቱ የጥፋት ከተማ ተብላ ትጠራለች።

19በዚያ ቀን በግብፅ ምድር መካከል ለእግዚአብሔር መሠዊያ ይሠራል፤ በድንበሯም ላይ ለእግዚአብሔር ዐምድ ይቆማል። 20ይህም በግብፅ ምድር ለሰራዊት ጌታ ለእግዚአብሔር ምልክትና ምስክር ይሆናል፤ ከሚያስጨንቋቸውም የተነሣ ወደ እግዚአብሔር ሲጮኹ፣ አዳኝና ታዳጊ ይልክላቸዋል፤ እርሱም ያድናቸዋል። 21እግዚአብሔር ራሱን ለግብፃውያን ይገልጣል፤ እነርሱም በዚያ ቀን እግዚአብሔርን ያውቁታል፤ በመሥዋዕትና በእህል ቍርባንም ያመልኩታል። ለእግዚአብሔር ስለት ይሳላሉ፤ የተሳሉትንም ይፈጽሙታል። 22እግዚአብሔር ግብፅን በመቅሠፍት ይመታታል፤ መትቶም፤ ይፈውሳቸዋል። እነርሱም ወደ እግዚአብሔር ይመለሳሉ፤ እርሱም ልመናቸውን ሰምቶ ይፈውሳቸዋል።

23በዚያ ቀን ከግብፅ ወደ አሦር አውራ መንገድ ይዘረጋል፤ አሦራውያን ወደ ግብፅ፣ ግብፃውያንም ወደ አሦር ይሄዳሉ፤ ግብፃውያንና አሦራውያን በአንድነት ያመልካሉ። 24በዚያ ቀን እስራኤል፣ ከግብፅና ከአሦር ጋር የምድር በረከት ለመሆን በሦስተኛነት ትቈጠራለች። 25የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርም፣ “ሕዝቤ ግብፅ፣ የእጄ ሥራ አሦር፣ ርስቴም እስራኤል የተባረኩ ይሁኑ” ብሎ ይባርካቸዋል።

Japanese Contemporary Bible

イザヤ書 19:1-25

19

エジプトについての預言

1これは、エジプトについての神のことばです。

「見よ。わたしは速い雲に乗ってエジプトへ向かう。

エジプトの偶像は身震いし、

エジプト人は恐ろしさのあまり意気消沈する。

2わたしが同士討ちをさせるので、兄弟は兄弟と、

隣人は隣人と、町は町と、州は州と争う。

3知恵ある助言者も、

どうしたらよいかわからず途方にくれ、

あげくの果てに、偶像に助けを求め、

霊媒や魔術師や魔女に伺いを立てる。

4「わたしはエジプトを、過酷な支配者に

引き渡す」と全能の主は告げます。

5ナイル川の水は、いつものようにあふれて

土地をうるおすこともなく、水路は干上がり、

6運河は水草が腐って悪臭を放ちます。

7川沿いの緑の草々は枯れ、風に吹き飛ばされます。

あらゆる作物が立ち枯れ、死に絶えるのです。

8漁師は仕事がなくて嘆き、

釣り師や網を打つ者は一人残らず解雇されます。

9機を織る者は、亜麻や綿が手に入りません。

10織工も労働者も大きな打撃に心を痛めます。

11ツォアン(エジプト北東部の有力都市)の助言者は、

なんという愚か者でしょう。

エジプトの王に進言する策さえ、全く愚かなものです。

それでも、知識をひけらかすことができるのでしょうか。

王の前で、学者の家柄を誇らしげに言えるでしょうか。

12エジプト王よ、あなたの知恵袋と呼ばれた賢者は、

どうしたのですか。あの知恵はどこへ行ったのですか。

彼らに知恵があるというなら、

主がエジプトに何をしようとしているかを、

彼らから聞けばよいのです。

13ツォアンの博学者たちは頼りにならず、

メンピス(エジプト古王国時代の首都)の知識人たちも、すっかり惑わされています。

なるほど、彼らはあなたにとって

最高の策略家でしょう。

しかし、その浅はかな進言によって、

エジプトは滅んだのです。

14主が正しく判断できないようにさせたので、

彼らは見当はずれのことばかり言います。

それを聞くエジプトは、

飲んだくれのようにふらつきながら歩きます。

15どんなものも、エジプトを救えません。

エジプトに正しい道を示すことのできる者は、

誰ひとりいません。

16その日、エジプト人は女のように弱くなり、振り上げられた神のこぶしを見て、恐れおののきます。 17イスラエルの名を耳にしただけでおびえます。それというのも、全能の主の計画が知らされたからです。

18その時、エジプトの五つの都市が全能の主に忠誠を誓い、ヘブル語を話すようになります。その一つはヘリオポリス(「太陽の都」の意)と呼ばれます。 19その時代には、主の祭壇がエジプトの中心地に設けられ、国境には主の記念碑が立てられて、 20主への忠誠のしるしとなります。彼らが迫害の中で助けを呼び求めると、主は救い主を送ります。この方が彼らを救い出すのです。

21その日、主はエジプト人にご自分を示します。彼らは主を知り、誓願のためのいけにえと供え物をささげ、神との約束を守るようになります。 22主はエジプトを打ちのめしたあとで、もう一度建て直すのです。エジプト人が素直に主を信じるので、願いを聞き入れ、すべてを元どおりにします。

23その日、エジプトとアッシリヤは街道で結ばれて自由に行き来し、共に同じ神を拝むようになります。

24イスラエルはこの両国と同盟を結び、三つの国が団結します。そしてイスラエルは、両国にとって祝福となるのです。 25イスラエルとの親交によって、エジプトとアッシリヤも祝福します。主は彼らに言います。「わたしの民エジプトに祝福あれ。わたしの造った国アッシリヤに祝福あれ。わたしのものであるイスラエルに祝福あれ。」