ኢሳይያስ 17 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 17:1-14

በደማስቆ ላይ የተነገረ ንግር

1ስለ ደማስቆ የተነገረ ንግር፤

“እነሆ፤ ደማስቆ ከእንግዲህ ከተማነቷ ይቀራል፤

የፍርስራሽ ክምር ትሆናለች።

2የአሮኤር ከተሞች ባድማ ይሆናሉ፤

የመንጎች መሰማሪያ ይሆናሉ፤

የሚያስፈራቸውም የለም።

3የተመሸገ ከተማ ከኤፍሬም፣

የመንግሥት ሥልጣን ከደማስቆ ይወርዳል፤

የሶርያም ቅሬታ

እንደ እስራኤላውያን ክብር ይሆናል”

ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

4“በዚያን ቀን የያዕቆብ ክብር ይደበዝዛል፤

የሰውነቱም ውፍረት ይሟሽሻል።

5ዐጫጅ የቆመውን ሰብል ሰብስቦ፣

ዛላውንም በክንዱ እንደሚያጭድ፣

ይህም በራፋይም ሸለቆ

እንደሚለቀም ቃርሚያ ይሆናል።

6ሆኖም የወይራ ዛፍ ሲመታ፣

ሁለት ወይም ሦስት ፍሬ በቅርንጫፍ ራስ ላይ እንደሚቀር፣

አራት ወይም አምስት ፍሬ ችፍግ ባለው ቅርንጫፍ ላይ እንደሚቀር፣

እንዲሁ ጥቂት ቃርሚያ ይተርፋል”

ይላል የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር

7በዚያ ቀን ሰዎች ወደ ፈጣሪያቸው ይመለከታሉ፤

ዐይኖቻቸውም ወደ እስራኤል ቅዱስ ያያሉ።

8በእጃቸውም ወደ ሠሯቸው መሠዊያዎች አይመለከቱም፤

በጣቶቻቸው ላበጇቸው የዕጣን መሠዊያዎች፣

ለአሼራም የአምልኮ ዐምዶች

ክብር አይሰጡም።

9በዚያን ቀን በእስራኤል ልጆች ምክንያት የተተዉት ጠንካራ ከተሞች ጥሻና ውድማ እንደ ሆኑ ሁሉ፣ እነዚህ ሁሉ ባድማ ይሆናሉ።

10አዳኝ አምላክህን ረስተሃል፤

መሸሸጊያ ዐለትህንም አላስታወስህም፤

ስለዚህ ምርጥ ተክል ብትተክልም፣

እንግዳ ዘርንም ብትዘራ፣

11በተከልህበት ቀን እንዲበቅል፣

በዘራህበትም ማግስት እንዲያብብ ብታደርግ እንኳ፣

መከሩ በደዌና በማይሽር ሕመም ቀን፣

እንዳልነበረ ይሆናል።

12አቤት፤ የብዙ ሕዝቦች የቍጣ ድምፅ

እንደ ባሕር ሞገድ ይጮኻል!

አቤት፤ የሰዎች ከፍተኛ ጩኸት

እንደ ኀይለኛ ውሃ ያስገመግማል!

13ሰዎቹ እንደ ኀይለኛ ውሃ ጩኸት ቢያስገመግሙም፣

እርሱ ሲገሥጻቸው፣

በኰረብታ ላይ በነፋስ እንደሚበንን ትቢያ፣

በዐውሎ ነፋስ ፊት እንደሚበተን ገለባ ይበተናሉ።

14እነሆ፤ ሲመሽ ድንገተኛ ሽብር ሆነ!

ከመንጋቱ በፊት ግን አንዳቸውም አልተገኙም።

የዘረፉን ዕድል ፈንታ፣

የበዘበዙን ዕጣ ይህ ሆነ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以賽亞書 17:1-14

關於大馬士革的預言

1以下是關於大馬士革的預言:

「看啊,大馬士革城必不復存在,淪為廢墟。

2亞羅珥的眾城邑必被廢棄,

羊群將在那裡棲息,

沒有人驚擾牠們。

3以法蓮17·3 舊約中常用以法蓮代表以色列國。的堡壘必被摧毀,

大馬士革的王權必喪失。

倖存的亞蘭人必像以色列人一樣失去榮耀。」

這是萬軍之耶和華說的。

4「到那日,雅各的榮耀必消失,

他肥胖的身軀必漸漸消瘦。

5國家好像一塊已收割的田地,

又像撿淨麥穗的利乏音谷。

6倖存者寥寥無幾,就像打過的橄欖樹上剩下的果子,

或兩三個掛在樹梢,

或四五個殘存在枝頭。」

這是以色列的上帝耶和華說的。

7到那日,人們必仰望他們的創造主,向以色列的聖者求助。 8那時他們不再仰望自己製造的祭壇,也不再供奉自己指頭所造的亞舍拉神像和香壇。 9到那日,他們因以色列人到來而遺棄的堅城必變為山林和高崗,一片荒涼。

10以色列人啊,

你們忘記了拯救你們的上帝,

不記得那保護你們的磐石。

所以,你們雖然栽種佳美的秧子,

插上遠方運來的樹苗,

11使它們在栽種的當天早上就生長開花,

也必一無所獲。

你們得到的只是艱難和無盡的痛苦。

12看啊,列國喧囂,如怒海洶湧;

萬民騷動,如洪水滔滔。

13雖然萬民喧囂如洶湧的洪水,

但上帝一聲斥責,他們便逃往遠方,

像山頂上被風捲走的糠秕,

又如狂風颳走的塵埃。

14他們晚上令人恐懼,早晨已無影無蹤。這就是擄掠我們之人的下場,搶奪我們之人的報應。