ኢሳይያስ 16 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 16:1-14

1ከምድረ በዳው ማዶ ካለችው ከሴላ፣

ለምድሪቱ ገዥ፣

ወደ ጽዮን ሴት ልጅ ተራራ

የበግ ጠቦት ግብር ላኩ።

2ከጐጇቸው ተባርረው

ግራ እንደ ተጋቡ ወፎች፣

የሞዓብ ሴቶችም

በአርኖን ወንዝ መሻገሪያ እንዲሁ ይሆናሉ።

3“ምክር ለግሱን፤

ውሳኔ ስጡን፤

በቀትር ጥላችሁን

እንደ ሌሊት አጥሉብን፤

የሸሹትን ደብቁ፤

ስደተኞችን አሳልፋችሁ አትስጡ።

4የሞዓባውያን ስደተኞች ከእናንተ ጋር ይቈዩ፤

እናንተም ከአጥፊው መጠጊያ ሁኗቸው።”

የጨቋኙ ፍጻሜ ይመጣል፤

ጥፋቱ ያከትማል፤

እብሪተኛም ከምድር ገጽ ይጠፋል።

5ዙፋን በፍቅር ይመሠረታል፤

ከዳዊት ቤት16፥5 ዕብራይስጡ ድንኳን ይላል። የሆነ፣

በፍርድ ፍትሕን የሚሻ፣

ጽድቅንም የሚያፋጥን፣

አንድ ሰው በታማኝነት በላዩ ይቀመጣል።

6የሞዓብን መዘባነን፣

እጅግ መታበዩንና ኵራቱን፣

እብሪቱንና ስድነቱን ሰምተናል፤

ትምክሕቱ ግን ከንቱ ነው።

7ስለዚህ ሞዓባውያን ዋይ ይላሉ፤

በአንድነትም ስለ ሞዓብ ዋይታ ያሰማሉ፤

ስለ ቂርሐራሴት ከተማ ሰዎች ትዝታ፣

በሐዘን ያለቅሳሉ።

8የሐሴቦን ዕርሻ፣

የሴባማም የወይን ተክል ጠውልጓል፤

የአሕዛብ ገዦች፣

ኢያዜርን ዐልፈው፣

ምድረ በዳውን ዘልቀው፣

ሥሮቻቸውን እስከ ባሕር ሰድደው የነበሩትን

የተመረጡ የወይን ተክሎችን

ረጋግጠዋል።

9ስለዚህ ስለ ሴባማ የወይን ተክል፣

ኢያዜር እንዳለቀሰች፣ እኔም አለቅሳለሁ፤

ሐሴቦን ሆይ፤ ኤልያሊ ሆይ፤

በእንባዬ አርስሻለሁ፤

ፍሬ ባፈራሽበት ወቅት የነበረው ሆታ፣

መከርሽም ሲደርስ የነበረው ደስታ ተቋርጧልና።

10ደስታና ሐሤትም ከአትክልቱ ቦታ ተወግዷል፤

በወይን ተክልም ቦታ ዝማሬ የለም፤

እልልታም ቀርቷል።

በወይን መጭመቂያ ቦታ የሚረግጥ የለም፤

የረጋጮችን ሆታ አጥፍቻለሁና።

11ስለዚህ ልቤ ስለ ሞዓብ እንደ በገና የሐዘን እንጕርጕሮ ታሰማለች፤

አንጀቴም ስለ ቄርሔሬስ ታለቅሳለች፤

12ሞዓብ ወደ ኰረብታዋ ብትወጣ፣

ትርፏ ድካም ብቻ ነው፤

ለጸሎት ወደ መቅደሷ ብትገባም፣

ዋጋ የለውም።

13እግዚአብሔር አስቀድሞ ስለ ሞዓብ የተናገረው ቃል ይህ ነው። 14አሁን ግን እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “የተቀጠረ ሠራተኛ ቀን እንደሚቈጥር፣ የሞዓብ ክብርና የሕዝቧ ብዛት በሦስት ዓመት ውስጥ ይዋረዳል፤ የሚቀረውም ሕዝብ ጥቂትና ደካማ ይሆናል።”

New International Version – UK

Isaiah 16:1-14

1Send lambs as tribute

to the ruler of the land,

from Sela, across the desert,

to the mount of Daughter Zion.

2Like fluttering birds

pushed from the nest,

so are the women of Moab

at the fords of the Arnon.

3‘Make up your mind,’ Moab says.

‘Render a decision.

Make your shadow like night –

at high noon.

Hide the fugitives,

do not betray the refugees.

4Let the Moabite fugitives stay with you;

be their shelter from the destroyer.’

The oppressor will come to an end,

and destruction will cease;

the aggressor will vanish from the land.

5In love a throne will be established;

in faithfulness a man will sit on it –

one from the house16:5 Hebrew tent of David –

one who in judging seeks justice

and speeds the cause of righteousness.

6We have heard of Moab’s pride –

how great is her arrogance! –

of her conceit, her pride and her insolence;

but her boasts are empty.

7Therefore the Moabites wail,

they wail together for Moab.

Lament and grieve

for the raisin cakes of Kir Hareseth.

8The fields of Heshbon wither,

the vines of Sibmah also.

The rulers of the nations

have trampled down the choicest vines,

which once reached Jazer

and spread towards the desert.

Their shoots spread out

and went as far as the sea.16:8 Probably the Dead Sea

9So I weep, as Jazer weeps,

for the vines of Sibmah.

Heshbon and Elealeh,

I drench you with tears!

The shouts of joy over your ripened fruit

and over your harvests have been stilled.

10Joy and gladness are taken away from the orchards;

no-one sings or shouts in the vineyards;

no-one treads out wine at the presses,

for I have put an end to the shouting.

11My heart laments for Moab like a harp,

my inmost being for Kir Hareseth.

12When Moab appears at her high place,

she only wears herself out;

when she goes to her shrine to pray,

it is to no avail.

13This is the word the Lord has already spoken concerning Moab. 14But now the Lord says: ‘Within three years, as a servant bound by contract would count them, Moab’s splendour and all her many people will be despised, and her survivors will be very few and feeble.’