ኢሳይያስ 14 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 14:1-32

1እግዚአብሔር ለያዕቆብ ይራራለታል፤

እስራኤልን እንደ ገና ይመርጠዋል፤

በራሳቸውም አገር ያኖራቸዋል።

መጻተኞች አብረዋቸው ይኖራሉ፤

ከያዕቆብም ቤት ጋር ይተባበራሉ።

2አሕዛብም ይወስዷቸዋል፤

ወደ ገዛ ስፍራቸውም ይመልሷቸዋል።

የእስራኤል ቤት አሕዛብን ርስት ያደርጓቸዋል፤

በእግዚአብሔርም ምድር ወንዶችና ሴቶች ባሪያዎች አድርገው ይገዟቸዋል፤

የማረኳቸውን ይማርኳቸዋል፤

የጨቈኗቸውንም ይገዟቸዋል።

3እግዚአብሔር ከሥቃይህ፣ ከመከራህና ከጽኑ ባርነትህ ባሳረፈህ ቀን፣ 4በባቢሎን ንጉሥ ላይ ትሣለቃለህ፤ እንዲህም ትላለህ፤

ጨቋኙ እንዴት አበቃለት!

አስገባሪነቱስ14፥4 የሙት ባሕር ጥቅልል፣ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕምና የሱርስቱ ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ ነገር ግን በማሶሬቱ ቅጅ የቃሉ ትርጕም በትክክል አይታወቅም። እንዴት አከተመ!

5እግዚአብሔር የክፉዎችን ዘንግ፣

የገዦችንም በትረ መንግሥት ሰብሯል፤

6ሕዝቦችን በማያቋርጥ ቍጣ የመታውን፣

ያለ ርኅራኄ እያሳደደ

የቀጠቀጠውን ሰብሯል።

7ምድር ሁሉ ሰላምና ዕረፍት አግኝታለች፤

የደስታም ዝማሬ ታስተጋባለች።

8ጥድና የሊባኖስ ዝግባ እንኳ ደስ ብሏቸው፣

“አንተም ወደቅህ፤

ዕንጨት ቈራጭም

መጥረቢያ አላነሣብንም” አሉ።

9በመጣህ ጊዜ

ሲኦል14፥9 በዚህና በቍጥር 11 እንዲሁም 15 ላይ አንዳንድ ቅጆች፣ መቃብር ይላሉ። ልትቀበልህ ተነሣሥታለች፤

ይቀበሉህም ዘንድ የሙታንን መናፍስት፣

በዓለም ገዥ የነበሩትን ሁሉ ቀስቅሳለች፤

በአሕዛብ ላይ የነገሡትን ነገሥታት

ከዙፋናቸው አውርዳለች።

10እነርሱ ሁሉ ይመልሱልሃል፤

እንዲህም ይሉሃል፤

“አንተም እንደ እኛ ደከምህ፤

እንደ እኛም ሆንህ።”

11ክብርህ፣ ከነበገና ድምፁ

ወደ ሲኦል ወረደ፤

ብሎች ከበታችህ ተነጥፈዋል፤

ትሎችም መደረቢያህ ይሆናሉ።

12አንተ የንጋት ልጅ፣ አጥቢያ ኮከብ ሆይ፤

እንዴት ከሰማይ ወደቅህ!

አንተ ቀድሞ መንግሥታትን ያዋረድህ፣

እንዴት ወደ ምድር ተጣልህ!

13በልብህም እንዲህ አልህ፤

“ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ፤

ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ አደርጋለሁ፤

በተራራው መሰብሰቢያ፣

በተቀደሰውም ተራራ14፥13 ወይም ሰሜኑ፤ በዕብራይስጡ፣ ዛፎን ተብሎ መተርጐም ይችላል። ከፍታ ላይ በዙፋኔ

እቀመጣለሁ፤

14ከደመናዎችም ከፍታ በላይ ዐርጋለሁ፤

ራሴንም እንደ ልዑል አደርጋለሁ።”

15ነገር ግን ወደ ሲኦል፣

ወደ ጥልቁም ጕድጓድ ወርደሃል።

16የሚያዩህም አትኵረው እየተመለከቱህ፣

በመገረም ስለ አንተ እንዲህ ይላሉ፤

“ያ ምድርን ያናወጠ፣

መንግሥታትን ያንቀጠቀጠ፣ ይህ ሰው ነውን?

17ዓለምን ምድረ በዳ ያደረገ፤

ከተሞችን ያፈራረሰ፣

ምርኮኞቹንም ወደ አገራቸው እንዳይሄዱ የከለከለ ይህ ነውን?”

18የአሕዛብ ነገሥታት ሁሉ በክብር አንቀላፍተዋል፤

በየመቃብራቸው ዐርፈዋል።

19አንተ ግን እንደማይፈለግ ቅርንጫፍ፣

ከመቃብር ወጥተህ ተጥለሃል፤

በሰይፍ በተወጉት፣

ወደ ጥልቁ ድንጋዮች በወረዱት፣

በተገደሉትም ተሸፍነሃል፤

እንደ ተረገጠም ሬሳ ሆነሃል።

20ከእነርሱ ጋር በመቃብር አትሆንም፤

ምድርህን አጥፍተሃልና፤

ሕዝብህንም ፈጅተሃልና።

የክፉ አድራጊዎች ዘር

ፈጽሞ አይታወስም።

21ተነሥተው ምድርን እንዳይወርሱ፣

ዓለምንም በከተሞቻቸው እንዳይሞሉ፣

ስለ አባቶቻቸው ኀጢአት፣

ወንድ ልጆቹ የሚታረዱበትን ስፍራ አዘጋጁ።

22“በእነርሱ ላይ እነሣለሁ”

ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

“ስሟንና ትሩፋኖቿን፣

ዘሯንና ትውልዷን ከባቢሎን እቈርጣለሁ”

ይላል እግዚአብሔር

23“የጃርት መኖሪያ፣

ረግረጋማ ቦታ አደርጋታለሁ፤

በጥፋትም መጥረጊያ እጠርጋታለሁ”

ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

በአሦር ላይ የተነገረ ትንቢት

24የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ብሎ ምሏል፤

“እንደ ዐቀድሁት በርግጥ ይከናወናል፤

እንደ አሰብሁትም ይሆናል።

25አሦርን በምድሬ ላይ አደቅቃለሁ፤

በተራራዬም ላይ እረግጠዋለሁ፤

ቀንበሩ ከሕዝቤ ላይ ይነሣል፤

ሸክሙም ከትከሻቸው ላይ ይወርዳል።”

26ለምድር ሁሉ የታሰበው ዕቅድ ይህ ነው፤

በአሕዛብም ሁሉ ላይ የተዘረጋው እጅ ይኸው ነው።

27የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ አስቧል፤

ማንስ ያግደዋል?

እጁም ተዘርግቷል?

ማንስ ይመልሰዋል?

በፍልስጥኤማውያን ላይ የተነገረ ትንቢት

28ንጉሡ አካዝ በሞተበት ዓመት እንዲህ የሚል ንግር መጣ፤

29“እናንት ፍልስጥኤማውያን ሆይ፤

የመታችሁ በትር ስለ ተሰበረ ሁላችሁ ደስ አይበላችሁ፤

ከእባቡ ሥር እፉኝት ይወጣልና፤

ፍሬውም ተወርዋሪ መርዘኛ እባብ ይሆናል።

30ከድኻም ድኻ የሆኑት መሰማሪያ ያገኛሉ፤

ችግረኞችም ተዝናንተው ይተኛሉ፤

ሥርህን ግን በራብ እገድላለሁ፤

ትሩፋንህንም እፈጃለሁ።

31“በር ሆይ፤ ዋይ በል! ከተማ ሆይ፤ ጩኽ!

ፍልስጥኤማውያን ሆይ፤ ሁላችሁም በፍርሀት ቅለጡ!

ጢስ ከሰሜን መጥቶብሃል፤

ከሰልፉ ተነጥሎ የሚቀር የለምና።

32ከዚያ ሕዝብ ለሚመጡ መልእክተኞች ምን መልስ ይሰጣል?

መልሱ፣ ‘እግዚአብሔር ጽዮንን መሥርቷል፤

መከራን የተቀበለው ሕዝብም፣

በእርሷ ውስጥ መጠጊያን አግኝቷል’ የሚል ነው።”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以賽亞書 14:1-32

以色列人必重歸故土

1耶和華必憐憫雅各,再次選擇以色列人做祂的子民,把他們安置在他們自己的土地上。外族人必與他們聯合,歸入以色列2各國必幫助他們重返故鄉。在耶和華賜給他們的土地上,外族人必做他們的僕婢。他們必擄掠以前擄掠他們的人,統治以前壓制他們的人。

對巴比倫的諷刺

3耶和華使他們脫離痛苦、悲傷和殘酷奴役的時候, 4他們必這樣譏笑巴比倫王:

「暴君滅亡了!

暴政結束了!

5耶和華折斷了邪惡君主的權杖。

6他曾狂怒地攻伐列邦,

無休無止,

怒氣沖沖地征服列國,

大肆迫害。

7如今天下太平,

人人歡呼歌唱,

8連松樹和黎巴嫩的香柏樹都歡喜快樂地說,

『自從他滅亡後,

再沒有人上來砍伐我們。』

9巴比倫王啊,你下到陰間,

陰間興奮地迎接你,

那些在世上做過君王和首領的陰魂都從座位上站起來迎接你,

10對你說,

『你如今也跟我們一樣軟弱無能。』

11你的榮耀和琴聲一同落入陰間,

蟲成了你的床鋪,

蛆成了你的被子。

12「明亮的晨星、黎明之子啊,

你怎麼從天上墜落下來?

你這打敗列國的怎麼被砍倒在地上?

13你曾想,『我要升到天上,

把自己的寶座設在上帝的眾星之上;

我要坐在遙遠的北方眾神明聚會的山上;

14我要升到雲天之上,

使自己與至高者一樣。』

15可是,你必墜入陰間,

掉進死亡的深坑。

16看見你的都瞪大眼睛盯著你,

都在想,『這就是那曾使大地震動、列國顫抖的人嗎?

17這就是那曾使天下荒涼、城邑傾覆、不肯釋放俘虜回家的人嗎?』

18萬國的君王都躺在自己華麗的陵墓中,

19只有你像一根毫無用處的樹枝,

被拋棄在自己的墳墓外。

你就像一具遭人踐踏的屍體,

與喪身刀下的人一同被扔進亂石坑裡。

20你必得不到君王的葬禮,

因為你禍國殃民,

殺害自己的百姓。

「惡人的子孫必永遠被遺忘。

21預備殺戮他的子孫吧,

因為他們的祖先罪惡深重,

免得他們興起統治世界、到處建造城邑。」

22萬軍之耶和華說:

「我必攻擊巴比倫

剷除巴比倫的名號、餘民和後裔。

這是耶和華說的。

23我必用毀滅的掃帚清掃它,

使它成為沼澤之地和刺蝟的住所。

這是萬軍之耶和華說的。」

關於亞述的預言

24萬軍之耶和華起誓說:

「我的計劃必實現,

我的旨意必成就。

25我必在我的土地上擊垮亞述人,

在我的山上踐踏他們,

除去他們加在我子民身上的軛和重擔。

26這是我對全世界所定的計劃,

是向列國伸出的懲罰之手。」

27萬軍之耶和華定了計劃,

誰能阻撓呢?

祂的手已經伸出,

誰能叫祂收回呢?

關於非利士的預言

28亞哈斯王駕崩那年,我得到以下預言:

29非利士人啊,

不要因擊打你們的杖已經折斷14·29 擊打你們的杖已經折斷」指攻擊非利士的王已死。便高興。

因為那杖就像一條蛇,

必生出一條更危險的蛇,

一條會飛的毒蛇。

30貧窮人必衣食無憂,

困苦人必安然度日,

但我必用饑荒除掉你們的子孫,

消滅你們殘存的人。

31城門啊,哀號吧!

城邑啊,哭喊吧!

非利士人啊,戰抖吧!

因為有陣容整齊的軍隊從北方如塵煙滾滾而來。

32該怎樣回覆外國的使者呢?

要告訴他們:「耶和華建立了錫安

祂困苦的子民必得到保護。」