ኢሳይያስ 13 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 13:1-22

በባቢሎን ላይ የተነገረ ትንቢት

1የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ ስለ ባቢሎን ያየው ንግር፤

2በተራቈተ ኰረብታ ዐናት ላይ ምልክት ስቀሉ፤

ድምፃችሁን ከፍ አድርጋችሁ ጩኹ፤

በመሳፍንቱም በር እንዲገቡ፣

በእጅ ምልክት ስጡ።

3በድል አድራጊነቴ ደስ የሚላቸውን ቅዱሳኔን አዝዛለሁ፤

ቍጣዬንም እንዲፈጽሙ፣

ተዋጊዎቼን ጠርቻለሁ።

4በተራሮች ላይ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ

የሚሰማውን ጩኸት አድምጡ፤

በመንግሥታትም መካከል፣

እንደ ተጨናነቀ ሕዝብ ድምፅ የሆነውን ውካታ ስሙ!

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

ሰራዊቱን ለጦርነት አሰልፏል።

5እግዚአብሔርና የቍጣው ጦር መሣሪያ፣

ምድሪቱን በሙሉ ለማጥፋት፣

ከሩቅ አገር፣

ከሰማያትም ዳርቻ መጥተዋል።

6የእግዚአብሔር ቀን ቀርቧልና አልቅሱ፤

ሁሉን ቻይ13፥6 ዕብራይስጡ ሻዳይ ይላል። ከሆነ አምላክ ዘንድ ጥፋት ይመጣልና።

7ስለዚህ እጆች ሁሉ ሽባ ይሆናሉ፤

የሰውም ሁሉ ልብ ይቀልጣል።

8ሽብር ይይዛቸዋል፤

ሥቃይና ጭንቀት ይደርስባቸዋል፤

ምጥ እንደ ያዛት ሴት ያምጣሉ፤

እርስ በርሳቸው በድንጋጤ ይተያያሉ፤

ፊታቸውም በፍርሀት ቀይ ይሆናል።

9እነሆ፤ የእግዚአብሔር ቀን ጨካኝ ነው፤

ምድርን ባድማ ሊያደርጋት፣

በውስጧም ያሉትን ኀጢአተኞች ሊያጠፋ፣

ከመዓትና ከብርቱ ቍጣ ጋር ይመጣል።

10የሰማይ ከዋክብትና ሰራዊታቸው፣

ብርሃን አይሰጡም፤

ፀሓይ ገና ከመውጣቷ ትጨልማለች፤

ጨረቃም ብርሃኗን አትሰጥም።

11ዓለምን ስለ ክፋቷ፣

ክፉዎችንም ስለ ኀጢአታቸው እቀጣለሁ፤

የትዕቢተኞችን እብሪት እሽራለሁ፤

የጨካኞችንም ጕራ አዋርዳለሁ።

12ሰውን ከነጠረ ወርቅ ይልቅ ውድ፣

ከኦፊርም ወርቅ ይበልጥ ብርቅ አደርጋለሁ።

13ስለዚህ በሰራዊት ጌታ በእግዚአብሔር መዓት፣

ቍጣው በሚነድድበት ቀን፣

ሰማያትን እነቀንቃለሁ፤

ምድርንም ከስፍራዋ አናውጣለሁ።

14እንደሚታደን ሚዳቋ፣

እረኛም እንደሌለው የበግ መንጋ፣

እያንዳንዱ ወደ ወገኑ ይመለሳል፣

እያንዳንዱም ወደ አገሩ ይሸሻል።

15የተማረከ ሁሉ ይወጋል፤

የተያዘም ሁሉ በሰይፍ ይወድቃል።

16ዐይናቸው እያየ ሕፃናታቸው ይጨፈጨፋሉ፤

ቤታቸው ይዘረፋል፤ ሚስቶቻቸው ይደፈራሉ።

17እነሆ፤ ለብር ደንታ የሌላቸውን፣

በወርቅም ደስ የማይሰኙትን፣

ሜዶናውያንን አስነሣባቸዋለሁ።

18ቀስታቸው ጐበዞችን ይፈጃል፤

ሕፃናትን አይምሩም፤

ዐይናቸውም ለልጆች አይራራም።

19የመንግሥታት ዕንቍ፣

የከለዳውያን13፥19 ወይም፣ ባቢሎናውያን ማለት ነው። ትምክሕት

የሆነችውን ባቢሎንን፣

እግዚአብሔር እንደ ሰዶምና እንደ ገሞራ ይገለብጣታል።

20በዘመናት ሁሉ የሚቀመጥባት አይኖርም፤

የሚቀመጥባትም የለም፤

ዐረብ በዚያ ድንኳኑን አይተክልም፤

እረኛም መንጋውን በዚያ አያሳርፍም።

21ነገር ግን የምድረ በዳ አራዊት በዚያ ይተኛሉ፤

ቀበሮዎች ቤቶቿን ይሞላሉ፤

ጕጕቶች በዚያ ይኖራሉ፤

በበረሓ ፍየል የሚመሰሉ አጋንንትም ይዛለሉበታል።

22ጅቦች በምሽጎቿ፣

ቀበሮዎችም በተዋቡ ቤተ መንግሥቶቿ ይጮኻሉ፤

ጊዜዋ ቀርቧል፤

ቀኗም አይራዘምም።

Japanese Contemporary Bible

イザヤ書 13:1-22

13

バビロンについての預言

1以下は、神がアモツの子イザヤに示したバビロン滅亡の幻です。

2「バビロンに攻め上る敵軍の旗を見よ。

資産家どもと権力者どもの屋敷を壊そうと

進撃して来る彼らに、歓声を上げて手を振れ。

3主であるわたしは、

この時のために彼らを取っておいた。

わたしは、わたしの怒りを晴らすために

喜んで協力する者を呼び集めた。

4山の上の騒動と、軍隊が行進して来る音を聞け。

あれは、多くの国の兵士がどよめき叫ぶ声だ。

天の軍勢の主が彼らを連れて来た。

5それも、ずっと遠い国々からだ。

バビロンよ、彼らはおまえを攻め立てる神の武器だ。

神の怒りを運んで来て、おまえの国を見るも無残に踏みにじる。

6いよいよ主の時が来たのだから、

恐怖におびえて泣き叫べ。

全能の神がおまえたちを打ち砕く時がついにきた。

7あまりの恐ろしさに腕は麻痺し、勇気はくじけ、

8震え上がる。産みの苦しみにあえぐ女のように、

激しい苦痛を伴う恐れに取りつかれる。

おまえたちは絶望して互いに見つめ合うが、

青ざめたその顔に映るのは、町を焼く炎ばかりだ。

9さあ、神の日が来る。

それは、神の憤りと激しい怒りに包まれた、

身の毛もよだつような日だ。

地は、そこに住む罪人もろとも滅びうせる。

10星も太陽も月も一筋の光さえ放たず、

天は真っ暗になる。

11わたしは世界をその悪のために、

悪者どもをその罪のために罰する。

傲慢な者とおごる金持ちとを踏みつぶす。

12わたしがそれを終えた時、

生き残っている者はほんの一握りだ。

その時、人を見いだすことは

金鉱を掘り当てることより難しく、

オフィルの金より価値あるものとなる。

13わたしが憤りと激しい怒りで天を震わすので、

大地は元の場所から移動する。

14バビロンの兵士は逃げ回り、ついに精根尽きて倒れる。

まるで犬に追われる鹿のように

故国めざして一目散に走り、

羊飼いに捨てられた羊のようにさまよう。

15走る気力を失った者は無残に殺される。

16幼子たちは彼らの目の前で、

舗道の石に投げつけられて殺される。

家は略奪され、妻は攻め入った敵兵に犯される。

17わたしはメディヤ人をバビロンに敵対させる。

どれほど金銀を積んでも、

彼らを買収することはできない。

18侵入した軍隊は、若者にも子どもにも幼子にも、

いっさい手ごころを加えない。

19こうして、王国の誉れであり

カルデヤ文明の華であったバビロンは、

天からの火に焼かれたソドムとゴモラのように滅びる。

20バビロンは二度と立ち上がれず、

永久に人が住みつかない。

遊牧の民でさえ、そこにテントを張らず、

羊飼いも、そこでは羊の群れを休ませない。

21バビロンは荒野の野獣やだちょうの

住みかとなり果てる。

家々はみみずくの巣となり、悪鬼が来ては踊り回る。

22ハイエナや山犬は宮殿を巣窟とする。

バビロンの寿命はあとわずか、運命の時はそこまで来ている。」