ኢሳይያስ 10 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 10:1-34

1ፍትሕ የጐደለውን ሕግ ለሚያወጡ፣

ጭቈና የሞላበትን ሥርዐት ለሚደነግጉ ወዮላቸው!

2የድኾችን መብት ለሚገፍፉ፣

የተጨቈነውን ሕዝቤን ፍትሕ ለሚያዛቡ፣

መበለቶችን ለሚበዘብዙ፣

ወላጅ የሌላቸውን ልጆች ለሚመዘብሩ ወዮላቸው!

3በምትጐበኙበት ቀን ምን ይውጣችኋል?

ጥፋት ከሩቅ ሲመጣስ ምን ትሆናላችሁ?

ርዳታን ለማግኘትስ ወደ ማን ትሸሻላችሁ?

ሀብታችሁንስ የት ታገኙታላችሁ?

4ከእስረኞች ጋር ከመርበትበት፣

ከታረዱትም ጋር ከመጣል በቀር ምንም አይተርፋችሁም።

ይህም ሁሉ ሆኖ፣ ቍጣው ገና አልበረደም።

እጁም እንደ ተዘረጋ ነው።

የእግዚአብሔር ፍርድ በአሦር ላይ

5“የቍጣዬ በትር ለሆነ፣

የመቅሠፍቴም ዱላ በእጁ ላለው ለአሦራዊው ወዮለት!

6ሀብታቸውን እንዲዘርፍ፣ ምርኮን እንዲያግበሰብስ፣

እንደ መንገድ ላይ ጭቃም እንዲረግጣቸው፣

አምላክ በሌለው ሕዝብ ላይ እልከዋለሁ፣

በሚያስቈጣኝም ሕዝብ ላይ እሰድደዋለሁ።

7እርሱ ግን እንዲህ አላሰበም፤

በልቡም ይህ አልነበረም፤

ነገር ግን ዕቅዱ ለማጥፋት፣

ብዙ ሕዝቦችንም ለመደምሰስ ነበር።

8እንዲህም ይል ነበር፤

‘የጦር አዛዦቼ በሙሉ ነገሥታት አይደሉምን?’

9ካልኖ እንደ ከርከሚሽ፣

ሐማት እንደ አርፋድ፣

ሰማርያስ እንደ ደማስቆ አይደሉምን?

10የጣዖታትን መንግሥታት፣

ምስሎቻቸው ከኢየሩሳሌምና ከሰማርያ መንግሥታት የሚበልጡትን እጄ እንደ ያዘች ሁሉ፣

11በሰማርያና በጣዖቶቿ ያደረግሁትን፣

በኢየሩሳሌምና በተቀረጹ ምስሎቿስ እንዲሁ አላደርግምን?”

12ጌታ በጽዮን ተራራና በኢየሩሳሌም ላይ የሚያደርገውን ሁሉ ከፈጸመ በኋላ፣ እንዲህ ይላል፤ “የአሦርን ንጉሥ ስለ ልቡ ትዕቢትና ስለ ንቀት አመለካከቱ እቀጣዋለሁ፤ 13የአሦር ንጉሥ እንዲህ ይላልና፤

“ ‘ይህን ሁሉ ያደረግሁት በክንዴ ብርታት ነው፤

ደግሞም በጥበቤ አስተዋይ ነኝና።

የመንግሥታትን ድንበር አፈረስሁ፤

ሀብታቸውን ዘረፍሁ፤

ነገሥታታቸውን እንደ አንድ ኀያል ሆኜ አዋረድሁ።10፥13 ወይም፣ ኀይላቸውን አዋረድሁ።

14ሰው እጁን ወደ ወፍ ጐጆ እንደሚሰድድ፣

እኔም እንዲሁ እጄን ወደ መንግሥታት ሀብት ሰደድሁ፤

ሰዎች የተተወ ዕንቍላል እንደሚሰበስቡ፣

እኔም እንዲሁ ምድርን ሁሉ ሰበሰብሁ፤

ክንፉን ያራገበ የለም፤

አፉንም ከፍቶ የጮኸ አልነበረም።’ ”

15መጥረቢያ በሚቈርጥበት ሰው ላይ ይኵራራልን?

መጋዝስ በሚስበው ላይ ይታበያልን?

በትር በሚያነሣው ሰው ላይ ራሱን እንደሚነቀንቅ፣

ዘንግም ራሱን ዕንጨት እንዳልሆነ አድርጎ እንደሚኵራራ ነው።

16ስለዚህ ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

በፈረጠሙ ጦረኞቹ ላይ የሚያከሳ በሽታ ይልካል፤

ከክብሩም በታች እንደ ነበልባል የሚንቦገቦግ እሳት

ይለኰሳል።

17የእስራኤል ብርሃን እሳት፣

ቅዱሱም ነበልባል ይሆናል፤

በአንድ ቀንም

እሾኹንና ኵርንችቱን እሳት ይበላዋል፤

18ሕመምተኛ እየመነመነ እንደሚሞት፣

የደኑን ክብርና የለማውን ዕርሻ፣

ነፍስና ሥጋንም ፈጽሞ ያጠፋል።

19በደኑ ውስጥ የሚተርፉት ዛፎች በጣም ጥቂት ናቸው፤

ሕፃን ልጅ እንኳ ቈጥሮ ሊመዘግባቸው ይችላል።

የተረፉት የእስራኤል ዘሮች

20በዚያን ቀን ከእስራኤል ዘር የተረፉት፣

ከያዕቆብም ቤት የዳኑት፣

ከእንግዲህ ወዲህ

በመታቸው ላይ አይታመኑም፤

ነገር ግን በእስራኤል ቅዱስ በእግዚአብሔር ላይ፣

በእውነት ይታመናሉ።

21የተረፉት ይመለሳሉ፣10፥21 በዚህና በ22 ላይ ዕብራይስጡ፣ ሼር ጃሹብ ይላል።

ከያዕቆብ ቤት የተረፉት ወደ ኀያሉ አምላክ ይመለሳሉ።

22እስራኤል ሆይ፤

ሕዝብህ እንደ ባሕር አሸዋ ቢሆንም፣

የተረፉት ብቻ ይመለሳሉ።

ታላቅና ጻድቅ የሆነ ጥፋት ታውጇል።

23ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

የወሰነውን ጥፋት በምድር ሁሉ ላይ ያመጣል።

24ስለዚህ ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

እንዲህ ይላል፤

“በጽዮን የምትኖሩ ሕዝቤ ሆይ፤

ግብፅ እንዳደረገብህ ሁሉ በትር ያነሡብህን፣

በሽመል የደበደቡህን አሦራውያንን አትፍራቸው።

25በአንተ ላይ ያመጣሁትን ቅጣት በጥቂት ጊዜ ውስጥ አቆማለሁ፤

በእነርሱም ላይ መቅሠፍቴን አመጣለሁ።”

26የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ምድያምን በሔሬብ ዐለት አካባቢ እንደ መታ፣

በጅራፍ ይገርፋቸዋል፤

በግብፅ እንዳደረገውም ሁሉ፣

በትሩን በውሆች ላይ ያነሣል።

27በዚያን ቀን ሸክማቸው ከትከሻህ፣

ቀንበራቸውም ከዐንገትህ ላይ ይነሣል፤

ከውፍረትህም የተነሣ

ቀንበሩ ይሰበራል።10፥27 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን፣ ቀንበሩ ከትከሻህ ላይ ይሰበራል ይላል።

28ወደ ዐያት ይገባሉ፣

በሚግሮን ያልፋሉ፤

ጓዛቸውንም በማክማስ ያከማቻሉ።

29መተላለፊያውን ዐልፈው እንዲህ ይላሉ፤

“በጌባዕ ሰፍረን እናድራለን።”

ራማ ደነገጠች፤

የሳኦል ከተማ ጊብዓ ሸሸች።

30የጋሊም ሴት ልጅ ሆይ፤ ጩኺ!

ላይሻ ሆይ፤ አድምጪ!

ምስኪን ዓናቶት ሆይ፤ ስሚ!

31ማድሜናህ በሽሽት ላይ ነች፤

የጌቢም ሕዝብ ሊደበቅ ይሮጣል።

32በዚህ ቀን ኖብ ይደርሳሉ፤

እጃቸውን በኢየሩሳሌም ኰረብታ፣

በጽዮን ሴት ልጅ ተራራ ላይ

በዛቻ ነቀነቁ።

33እነሆ፤ ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

በታላቅ ኀይል ቅርንጫፎችን ይቈራርጣል፤

ረዣዥም ዛፎች ይገነደሳሉ፤

ከፍ ከፍ ያሉትም ይወድቃሉ።

34ጥቅጥቅ ያለውን ደን በመጥረቢያ ይቈራርጣል፤

ሊባኖስም በኀያሉ ፊት ይወድቃል።

Japanese Contemporary Bible

イザヤ書 10:1-34

10

1「不正な裁判官と不公平な法律を作る者は

災いである」と主は言います。

2彼らは、貧しい人やみなしごを見殺しにし、

未亡人や父のない子の権利を奪っています。

3「わたしが遠い国から滅亡を招き寄せる。

さあ、どうするつもりか。

そのとき、だれに助けを求めるのか。

どこに財宝を隠すつもりか。

4わたしは助けない。

道は二つ。

囚人となって、よろめきながら引かれて行くか、

虐殺されて横たわるかだ。

それでもわたしの怒りは収まらない。

なお打ちのめそうと、こぶしを振り上げる。

アッシリヤへの神のさばき

5-6アッシリヤはわたしの怒りのむちだ。

わたしはその軍事力を使って、

滅びの運命にある、不敬虔なこの国を攻め立てる。

アッシリヤはこの民を捕虜にし、

略奪をほしいままにし、泥のように踏みにじる。

7ところが当のアッシリヤ王は、

わたしにあやつられているとは夢にも思わない。

世界征服の一部として、

神の民を攻めているだけだと考える。

8占領した国々の王に高官たちを据え、得意げに言う。

9『さあ、カルケミシュのように

カルノもやっつけてしまおう。

ハマテなど一飲みだ。

アルパデのように必ず降伏するだろう。

サマリヤもダマスコのように

足腰が立たないようにしてやろう。

10エルサレムやサマリヤの神より偉大な神々の国を、

われわれは片っ端から打ち倒してきた。

11サマリヤとその神を打ち砕いたように、

エルサレムとその神もそうしよう。』」

12主はアッシリヤ王を用いて目的を果たしたのち、今度は、高ぶるアッシリヤに襲いかかって罰を加えます。

13彼らは豪語したのです。

「われわれは自分の力と知恵で戦いに勝ってきた。

われわれは高度の文明を誇る偉大な民だ。

われわれの手で国々の城壁をぶち壊し、

住民を滅ぼし、財宝を運び出した。

14諸国の富を略奪し、

農夫が卵を集めるように、

王国を奪い取ってきた。

彼らはわれわれを阻止するどころか、

抗議することさえできなかった。」

15しかし主は、きびしく問い返します。

「斧は主人に、

自分のほうに力があると自慢できるだろうか。

のこぎりは、それを使う人よりほめられるだろうか。

棒は、それを動かす手がなかったら、

人を打つことができるだろうか。

杖は一人で歩くことができるだろうか。」

16あなたのおごりのゆえにアッシリヤの王よ、

天の軍勢の主は負け知らずのあなたの軍隊に

疫病をはやらせ、兵を打ちます。

17光であるイスラエルの聖なる神は、

燃えさかる炎となって全軍を焼き尽くします。

イスラエルの国土を荒らした、

いばらのようなアッシリヤ人を、

一夜のうちに焼き払うでしょう。

18今は壮麗な森のような大軍も無残な姿をさらし、

病人がやせ細っていくように、

身もたましいも滅び去ります。

19おびただしい兵力を誇った大軍のうち

生き残る者はわずかで、

子どもにも数えられるほどの数です。

イスラエルの残りの民

20そうなってようやく、

イスラエルとユダに残っていた者は、

二度とアッシリヤ人を恐れなくなり、

イスラエルの聖なる神である主だけを

頼みとするようになります。

21全能の神に立ち返るのです。

22しかし今、イスラエルの民は

海辺の砂のように多くいようとも、

その時まで生き残り、神に立ち返る者は、

ごくわずかしかいません。

神はご自分の民を滅ぼそうと、

堅く覚悟を決めているからです。

23彼らを根こそぎにすることは、

主なる神によってすでに決められたことです。

24それゆえ主なる神は命じます。「エルサレムに住むわたしの民よ、かつてのエジプト人のようにアッシリヤ人が圧力をかけても、怖がってはならない。 25もうしばらくの辛抱だ。わたしの怒りはおまえたちから離れ、アッシリヤ人に向けられる。彼らは滅びるのだ。」 26全能の主は、ギデオンがオレブの岩でミデヤン軍を打ち破った時のように、またエジプト軍が海でおぼれた時のように、アッシリヤ軍に立ち向かいます。

27その日、神はご自分の民を解放し、

奴隷のくびきをはずして粉々に壊します。

28-29見なさい。アッシリヤの大軍が押し寄せて来ます。

さっきまでアヤテにいたのに、

もうミグロンに着きました。

彼らはミクマスに軍用物資を置き、

渡し場を過ぎ、ゲバで野営します。

ラマの町は震え上がり、

サウルの町ギブアの住民は命からがら逃げ去ります。

30ガリムの人たちよ、

恐怖につかれて声の限り叫びなさい。

大軍がやって来るのだから、

ラユシャに大声で危険を知らせなさい。

哀れなアナトテよ、あなたの運命は何とも哀れです。

31あそこに行くのは、

落ち伸びて行くマデメナの人たちではありませんか。

ゲビムの住民は逃げる準備をしています。

32その日、敵軍はノブで止まり、

シオンの山の上にあるエルサレムに向けて

進軍の手を振ります。

33しかし、あれを見なさい。

天の軍勢の主が屈強な木々を切り倒しています。

大木と小木、将校と兵卒の区別なく、

あの大軍を滅ぼし尽くしています。

34全能の主が、きこりが斧でレバノンの森の木々を

切り倒すように、敵をなで切りにするのです。