አብድዩ 1 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

አብድዩ 1:1-21

የአብድዩ ራእይ

1ጌታ እግዚአብሔር ስለ ኤዶም እንዲህ ይላል፤

ከእግዚአብሔር ዘንድ መልእክት ሰምተናል፤

መልእክተኛውም ወደ አሕዛብ ተልኮ እንዲህ

ብሏል፤

“ተነሡ፤ እርሷን ለመውጋት እንውጣ።”

2“እነሆ፤ በአሕዛብ መካከል ታናሽ አደርግሃለሁ፤

እጅግ የተናቅህ ትሆናለህ።

3አንተ በሰንጣቃ1፥3 ወይም በሴላ ዐለት ውስጥ

የምትኖር፣

መኖሪያህንም በከፍታ ስፍራ ያደረግህ፣

ለራስህም፣

‘ማን ወደ ምድር ሊያወርደኝ ይችላል?’ የምትል፣

የልብህ ትዕቢት አታልሎሃል።

4እንደ ንስር መጥቀህ ወደ ላይ ብትወጣ፣

ጐጆህንም በከዋክብት መካከል ብታደርግ፣

ከዚያ አወርድሃለሁ”

ይላል እግዚአብሔር

5“ሌቦች ወደ አንተ ቢመጡ፣

ዘራፊዎችም በሌሊት ቢገቡ፣

የሚሰርቁት የሚፈልጉትን ያህል ብቻ አይደለምን?

ወይን ለቃሚዎች ወደ አንተ ቢመጡ፣

ጥቂት ቃርሚያ አይተዉምን?

አንተ ግን ምንኛ ጥፋት ይጠብቅሃል!

6ዔሳው ግን እንዴት ተዘረፈ?

የሸሸገውስ ሀብት ምንኛ ተመዘበረ!

7ወዳጆችህ ሁሉ ወደ ድንበር ይገፉሃል፤

ጓደኞችህ ያታልሉሃል፤ ያሸንፉህማል፤

እንጀራህን የበሉ ወጥመድ ይዘረጉብሃል፤1፥7 የዚህ ሐረግ የዕብራይስጡ ትርጓሜ በርግጠኝነት አይታወቅም።

አንተ ግን አታውቀውም።

8“በዚያ ቀን ጥበበኛ ሰዎችን ከኤዶም፣

አስተዋዮችንም ከዔሳው ተራሮች አልደመስስምን?”

ይላል እግዚአብሔር

9“ቴማን ሆይ፤ ተዋጊዎችህ ይደነግጣሉ፤

በዔሳውም ተራሮች ያለ ሁሉ፣

ተገድሎ ይጠፋል።

10በወንድምህ በያዕቆብ ላይ ስላደረግኸው ግፍ፣

በዕፍረት ትሸፈናለህ፤

ለዘላለምም ትጠፋለህ።

11እንግዶች ሀብቱን ዘርፈው ሲሄዱ፣

ባዕዳንም በበሮቹ ሲገቡ፣

በኢየሩሳሌምም ላይ ዕጣ ሲጣጣሉ፣

በዚያ ቀን ገለልተኛ ሆነህ ተመለከትህ፣

አንተም ከእነርሱ እንደ አንዱ ሆንህ።

12ክፉ ቀን በገጠመው ጊዜ፤

በወንድምህ ሥቃይ መደሰት አልነበረብህም፤

በጥፋታቸው ቀን፣ የይሁዳ ሕዝብ ሲያዝኑ

ሐሤት ማድረግ አልነበረብህም፤

በጭንቀታቸውም ቀን፣

በትዕቢት ልትናገር አይገባህም ነበር።

13በጥፋታቸው ቀን፣

በሕዝቤ በር መግባት የለብህም ነበር፤

በጥፋታቸው ቀን፣

በጭንቀታቸው መደሰት አልነበረብህም፤

በጥፋታቸው ቀን፣

ሀብታቸውን መዝረፍ አይገባህም ነበር።

14ስደተኞቻቸውን ለመግደል፣

በመንታ መንገድ መጠባበቅ አይገባህም ነበር፣

በጭንቀታቸው ቀን፣

የተረፉትን አሳልፈህ መስጠት አልነበረብህም።

15“በአሕዛብ ሁሉ ላይ፣

የእግዚአብሔር ቀን ደርሷል፤

አንተ እንዳደረግኸው፣ በአንተም ላይ ይደረጋል፤

ክፉ ሥራህም በራስህ ላይ ይመለሳል።

16እናንተ በቅዱሱ ተራራዬ እንደ ጠጣችሁ፣

አሕዛብ ሁሉ ዘወትር ይጠጣሉ፤

ይጠጣሉ፤ አብዝተውም ይጠጣሉ፤

ከዚህም በፊት እንዳልሆኑት ይሆናሉ።

17ነገር ግን በጽዮን ተራራ ነጻ መውጣት ይሆናል፤

የያዕቆብ ቤትም እርሷ የተቀደሰች ትሆናለች፤

ርስታቸውን ይወርሳሉ።

18የያዕቆብ ቤት እሳት፣

የዮሴፍም ቤት ነበልባል ይሆናል፤

የዔሳው ቤት ገለባ ይሆናል፤

ያቃጥሉታል፤ ይበሉትማል፤

ከዔሳው ቤት የሚተርፍ አይኖርም።”

እግዚአብሔር ተናግሯል።

19የኔጌብ ሰዎች፣

የዔሳውን ተራራ ይይዛሉ፤

ከተራራው ግርጌ ያሉ ሰዎችም፣

የፍልስጥኤማውያንን ምድር ይወርሳሉ፤

የኤፍሬምንና የሰማርያንም ዕርሻ ይይዛሉ፤

ብንያምም ገለዓድን ይወርሳል።

20በከነዓን ያለው ይህ የእስራኤል ስደተኞች ወገን፣

እስከ ሰራጵታ ያለውን ምድር ይወርሳል፤

በሰፋራድም ያሉ የኢየሩሳሌም ስደተኞች፣

የኔጌብን ከተሞች ይወርሳሉ።

21የዔሳውን ተራሮች ለመግዛት፣

ነጻ አውጪዎች ወደ ጽዮን ተራራ ይወጣሉ፤

መንግሥቱም የእግዚአብሔር ይሆናል።

King James Version

Obadiah 1:1-21

1The vision of Obadiah. Thus saith the Lord GOD concerning Edom; We have heard a rumour from the LORD, and an ambassador is sent among the heathen, Arise ye, and let us rise up against her in battle. 2Behold, I have made thee small among the heathen: thou art greatly despised.

3¶ The pride of thine heart hath deceived thee, thou that dwellest in the clefts of the rock, whose habitation is high; that saith in his heart, Who shall bring me down to the ground? 4Though thou exalt thyself as the eagle, and though thou set thy nest among the stars, thence will I bring thee down, saith the LORD. 5If thieves came to thee, if robbers by night, (how art thou cut off!) would they not have stolen till they had enough? if the grapegatherers came to thee, would they not leave some grapes?1.5 some…: or, gleanings? 6How are the things of Esau searched out! how are his hidden things sought up! 7All the men of thy confederacy have brought thee even to the border: the men that were at peace with thee have deceived thee, and prevailed against thee; they that eat thy bread have laid a wound under thee: there is none understanding in him.1.7 that were…: Heb. of thy peace1.7 they…: Heb. the men of thy bread1.7 in him: or, of it 8Shall I not in that day, saith the LORD, even destroy the wise men out of Edom, and understanding out of the mount of Esau? 9And thy mighty men, O Teman, shall be dismayed, to the end that every one of the mount of Esau may be cut off by slaughter.

10¶ For thy violence against thy brother Jacob shame shall cover thee, and thou shalt be cut off for ever. 11In the day that thou stoodest on the other side, in the day that the strangers carried away captive his forces, and foreigners entered into his gates, and cast lots upon Jerusalem, even thou wast as one of them.1.11 captive…: or, his substance 12But thou shouldest not have looked on the day of thy brother in the day that he became a stranger; neither shouldest thou have rejoiced over the children of Judah in the day of their destruction; neither shouldest thou have spoken proudly in the day of distress.1.12 spoken…: Heb. magnified thy mouth 13Thou shouldest not have entered into the gate of my people in the day of their calamity; yea, thou shouldest not have looked on their affliction in the day of their calamity, nor have laid hands on their substance in the day of their calamity;1.13 substance: or, forces 14Neither shouldest thou have stood in the crossway, to cut off those of his that did escape; neither shouldest thou have delivered up those of his that did remain in the day of distress.1.14 delivered up: or, shut up 15For the day of the LORD is near upon all the heathen: as thou hast done, it shall be done unto thee: thy reward shall return upon thine own head. 16For as ye have drunk upon my holy mountain, so shall all the heathen drink continually, yea, they shall drink, and they shall swallow down, and they shall be as though they had not been.1.16 swallow…: or, sup up

17¶ But upon mount Zion shall be deliverance, and there shall be holiness; and the house of Jacob shall possess their possessions.1.17 deliverance: or, they that escape1.17 there…: or, it shall be holy 18And the house of Jacob shall be a fire, and the house of Joseph a flame, and the house of Esau for stubble, and they shall kindle in them, and devour them; and there shall not be any remaining of the house of Esau; for the LORD hath spoken it. 19And they of the south shall possess the mount of Esau; and they of the plain the Philistines: and they shall possess the fields of Ephraim, and the fields of Samaria: and Benjamin shall possess Gilead. 20And the captivity of this host of the children of Israel shall possess that of the Canaanites, even unto Zarephath; and the captivity of Jerusalem, which is in Sepharad, shall possess the cities of the south.1.20 which…: or, shall possess that which is in 21And saviours shall come up on mount Zion to judge the mount of Esau; and the kingdom shall be the LORD’s.