አስቴር 9 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

አስቴር 9:1-32

የአይሁድ ድል ማድረግ

1አዳር በተባለው በዐሥራ ሁለተኛው ወር ዐሥራ ሦስተኛ ቀን፣ በንጉሡ ትእዛዝ የወጣው ዐዋጅ የሚፈጸምበት ዕለት ነበር። በዚህም ዕለት የአይሁድ ጠላቶች የበላይነቱን እንደሚያገኙ ተማምነው ነበር፤ ሁኔታው ግን ተለወጠና አይሁድ በሚጠሏቸው ላይ የበላይነትን አገኙ። 2የእነርሱን መጥፋት በሚፈልጉ ወገኖች ላይ አደጋ ለመጣል አይሁድ በንጉሥ ጠረክሲስ አውራጃዎች ሁሉ ባሉት ከተሞቻቸው ተሰበሰቡ። የሌሎቹ አገር ዜጎች ሕዝብ ሁሉ ፈርተዋቸው ስለ ነበር፣ ማንም ሊደፍራቸው አልቻለም። 3የየአውራጃው መኳንንት ሁሉ፣ እንደራሴዎች፣ የአውራጃ ገዦች እንዲሁም የንጉሡ አስተዳዳሪዎች አይሁድን ረዷቸው፤ ይህን ያደረጉትም መርዶክዮስን ስለ ፈሩ ነበር። 4መርዶክዮስ በቤተ መንግሥቱ ታዋቂ ሆነ፤ ዝናው በየአውራጃው ሁሉ ተሰማ፤ ኀይሉም እየበረታ ሄደ።

5ስለዚህ አይሁድ ጠላቶቻቸውን ሁሉ በሰይፍ እየመቱ ገደሏቸው፤ አጠፏቸውም፤ በሚጠሏቸውም ላይ ደስ ያላቸውን አደረጉ። 6አይሁድ በሱሳ ግንብ አምስት መቶ ሰው ገደሉ፤ አጠፉም። 7ፖርሻንዳታን፣ ደልፎንን፣ አስፓታን፣ 8ፖራታን፣ አዳልያን፣ አሪዳታን፣ 9ፓርማ ሽታን፣ አሪሳይን፣ አሪዳይንና ዋይዛታንም ገደሉ፤ 10እነዚህም የአይሁድ ጠላት የሆነው የሐመዳቱ ልጅ የሐማ ዐሥር ወንዶች ልጆች ነበሩ። በምርኮው ላይ ግን እጃቸውን አልዘረጉም።

11በሱሳ ግንብ የተገደሉት ሰዎች ብዛት በዚያኑ ዕለት ለንጉሡ ተነገረው። 12ንጉሡም ንግሥት አስቴርን፣ “አይሁድ በሱሳ ግንብ አምስት መቶ ሰውና ዐሥሩን የሐማ ልጆች ገድለዋል፤ አጥፍተዋልም። በተቀሩት በንጉሡ አውራጃዎችስ ምን አድርገው ይሆን? አሁንስ የምትለምኚው ምንድን ነው? ይሰጥሻል፤ የምትጠይቂውስ ምንድን ነው? ይፈቀድልሻል” አላት።

13አስቴርም፣ “ንጉሥን ደስ የሚያሰኘው ከሆነ፣ በሱሳ የሚኖሩ አይሁድ የዛሬውን ዐዋጅ ነገም እንዲደግሙት ፈቃድህ ይሁን፤ ዐሥሩ የሐማ ወንዶች ልጆችም ዕንጨት ላይ ይሰቀሉ” አለች።

14ንጉሡም ይህ እንዲሆን አዘዘ። በሱሳ ዐዋጅ ተነገረ፤ ዐሥሩንም የሐማ ወንዶች ልጆች ሰቀሏቸው። 15በሱሳ የሚኖሩ አይሁድ አዳር በተባለው ወር በዐሥራ አራተኛው ቀን በአንድነት መጡ፤ በሱሳም ሦስት መቶ ሰዎች ገደሉ፤ በምርኮው ላይ ግን እጃቸውን አልዘረጉም።

16በዚህ ጊዜ በሌሎች በንጉሡ አውራጃዎች የሚኖሩ የተቀሩት አይሁድ ራሳቸውን ለመከላከልና ከጠላቶቻቸውም ለመገላገል ተሰበሰቡ፤ ከሚጠሏቸውም ሰባ አምስት ሺሕ ገደሉ፤ በምርኮው ላይ ግን እጃቸውን አልዘረጉም። 17ይህ የሆነው አዳር በተባለው ወር ዐሥራ ሦስተኛ ቀን ነበር፤ በዐሥራ አራተኛው ቀን ዐረፉ፤ ዕለቱንም የተድላና የደስታ ቀን አድርገው ዋሉ።

የፉሪም በዓል መከበር

18በሱሳ የሚኖሩ አይሁድ ግን በዐሥራ ሦስተኛውና በዐሥራ አራተኛው ቀን ተሰብስበው ነበር፤ ከዚያም በዐሥራ አምስተኛው ቀን ዐረፉ፤ ዕለቱንም የተድላና የደስታ ቀን አድርገው ዋሉ።

19በየመንደሩ የሚኖሩ የገጠር አይሁድ፣ የአዳርን ወር ዐሥራ አራተኛ ቀን የተድላና የደስታ፣ እርስ በርሳቸውም ስጦታ የሚለዋወጡበት ቀን አድርገው የሚያከብሩት ከዚሁ የተነሣ ነው።

20መርዶክዮስ የተፈጸሙትን እነዚህን ድርጊቶች ጻፈ፤ ደብዳቤ አዘጋጅቶም በመላው የንጉሥ ጠረክሲስ አውራጃ በቅርብና በሩቅ ለሚገኙት አይሁድ ሁሉ ላከ፤ 21የላከውም የአዳርን ወር ዐሥራ አራተኛና ዐሥራ አምስተኛ ቀን በየዓመቱ እንዲያከብሩ ነው፤ 22የሚያከብሩበትም ምክንያት አይሁድ ከጠላቶቻቸው ዕረፍት ያገኙበት፣ ሐዘናቸው ወደ ደስታ፣ ልቅሷቸውም ወደ ክብረ በዓል የተለወጠበት ቀን ስለሆነ ነው። ቀኖቹንም የተድላና የደስታ ቀኖች አድርገው፣ እርስ በርሳቸውም የምግብ ስጦታ እየተለዋወጡና ለድኾችም ስጦታ እየሰጡ እንዲያከብሩ ጻፈላቸው።

23ስለዚህ አይሁድ መርዶክዮስ የጻፈላቸውን ለመፈጸምና የጀመሩትን በዓል ለማክበር ተስማሙ፤ 24ምክንያቱም የአይሁድ ሁሉ ጠላት የሆነው የአጋጋዊው የሐመዳቱ ልጅ ሐማ አይሁድን ለማጥፋት አሢሮ ነበር፤ ሊፈጃቸውና ሊያጠፋቸውም ፉር የተባለ ዕጣ ጥሎ ነበር። 25ሤራው በንጉሡ ዘንድ እንደ ታወቀ9፥25 ወይም፣ አስቴር በንጉሡ ፊት በወጣች ጊዜ ሐማ በአይሁድ ላይ የሸረበው ሤራ በገዛ ራሱ ላይ እንዲጠመጠም፣ እርሱና ወንዶች ልጆቹም በዕንጨት ላይ እንዲሰቀሉ የጽሑፍ ትእዛዝ አስተላለፈ። 26ስለዚህ እነዚህ ቀኖች ፉር ከሚለው ቃል “ፉሪም” ለመባል በቁ። በዚህ ደብዳቤ ስለ ተጻፈው ሁሉ፣ ስላዩትና ስለ ደረሰባቸውም ነገር ሁሉ፣ 27አይሁድ በታዘዘውና በተወሰነው ጊዜ እነርሱና ዘሮቻቸው፣ እነርሱን የተጠጓቸውም ሁሉ እነዚህን ሁለት ቀኖች በየዓመቱ ባለማቋረጥ እንዲያከብሩ ሥርዐት አድርገው ራሳቸው ወሰኑ። 28እነዚህም ቀኖች በእያንዳንዱ ትውልድ፣ በእያንዳንዱ ቤተ ሰብ፣ በእያንዳንዱ አውራጃና በእያንዳንዱ ከተማ መታሰብና መከበር ይኖርባቸዋል፤ ይኸውም እነዚህ የፉሪም ቀኖች በአይሁድ ዘንድ ሳይከበሩ እንዳይቀሩ፤ መታሰቢያቸውም ከዘሮቻቸው መካከል እንዳይደመሰስ ነው።

29ስለዚህ የአቢካኢል ልጅ ንግሥት አስቴር ከአይሁዳዊው ከመርዶክዮስ ጋር በመሆን፣ ፉሪምን አስመልክተው ይህችን ሁለተኛዪቱን ደብዳቤ ለማጽናት በሙሉ ሥልጣን ጻፉ። 30መርዶክዮስም የመልካም ምኞት መግለጫና ማረጋገጫ የሆነውን ደብዳቤ በጠረክሲስ ግዛት ውስጥ በሚገኙት አንድ መቶ ሃያ ሰባት አውራጃዎች ለሚኖሩት አይሁድ ሁሉ ላከ፤ 31የላከውም አይሁዳዊው መርዶክዮስና ንግሥት አስቴር ባወጁላቸውና እንደዚሁም የጾሙንና የሰቈቃውን ጊዜ በሚመለከት ለራሳቸውና ለዘራቸው ባጸኑት ውሳኔ መሠረት እነዚህ የፉሪም ቀኖች በተወሰነላቸው ጊዜ እንዲከበሩ ነው። 32የአስቴር ዐዋጅ ስለ ፉሪም የወጣውን ሥርዐት አጸና፤ ይህም በመዝገብ ተጻፈ።

Persian Contemporary Bible

استر 9:1-32

يهوديان دشمنان خود را نابود می‌كنند

1روز سيزدهم ادار، يعنی روزی كه قرار بود فرمان پادشاه به مرحلهٔ اجرا درآيد، فرا رسيد. در اين روز، دشمنان يهود اميدوار بودند بر يهوديان غلبه يابند، اما قضيه برعكس شد و يهوديان بر دشمنان خود پيروز شدند. 2در سراسر مملكت، يهوديان در شهرهای خود جمع شدند تا به كسانی كه قصد آزارشان را داشتند، حمله كنند. همه مردم از يهوديان می‌ترسيدند و جرأت نمی‌كردند در برابرشان بايستند. 3تمام حاكمان و استانداران، مقامات مملكتی و درباريان از ترس مردخای، به يهوديان كمک می‌كردند؛ 4زيرا مردخای از شخصيتهای برجستهٔ دربار شده بود و در سراسر مملكت، شهرت فراوان داشت و روز بروز بر قدرتش افزوده می‌شد. 5به اين ترتيب يهوديان به دشمنان خود حمله كردند و آنها را از دم شمشير گذرانده، كشتند. 6آنها در شهر شوش كه پايتخت بود، ۵۰۰ نفر را كشتند. 7‏-10ده پسر هامان، دشمن يهوديان، نيز جزو اين كشته‌شدگان بودند. اسامی آنها عبارت بود از: فرشنداتا، دلفون، اسفاتا، فوراتا، ادليا، اريداتا، فرمشتا، اريسای، اريدای و ويزاتا. اما يهوديان اموال دشمنان را غارت نكردند.

11در آن روز، آمار كشته‌شدگان پايتخت به عرض پادشاه رسيد. 12سپس او ملكه استر را خواست و گفت: «يهوديان تنها در پايتخت ۵۰۰ نفر را كه ده پسر هامان نيز جزو آنها بودند، كشته‌اند، پس در ساير شهرهای مملكت چه كرده‌اند! آيا درخواست ديگری نيز داری؟ هر چه بخواهی به تو می‌دهم. بگو درخواست تو چيست.»

13استر گفت: «پادشاها، اگر صلاح بدانيد به يهوديان پايتخت اجازه دهيد كاری را كه امروز كرده‌اند، فردا هم ادامه دهند، و اجساد ده پسر هامان را نيز به دار بياويزند.»

14پادشاه با اين درخواست استر هم موافقت كرد و فرمان او در شوش اعلام شد. اجساد پسران هامان نيز به دار آويخته شد. 15پس روز بعد، باز يهوديان پايتخت جمع شدند و ۳۰۰ نفر ديگر را كشتند، ولی به مال كسی دست‌درازی نكردند.

16بقيهٔ يهوديان در ساير استانها نيز جمع شدند و از خود دفاع كردند. آنها ۷۵,۰۰۰ نفر از دشمنان خود را كشتند و از شر آنها رهايی يافتند، ولی اموالشان را غارت نكردند. 17اين كار در روز سيزدهم ماه ادار انجام گرفت و آنها روز بعد، يعنی چهاردهم ادار پيروزی خود را با شادی فراوان جشن گرفتند. 18اما يهوديان شوش، روز پانزدهم ادار را جشن گرفتند، زيرا در روزهای سيزدهم و چهاردهم، دشمنان خود را می‌كشتند.

19يهوديانِ روستاها به اين مناسبت روز چهاردهم ادار را با شادی جشن می‌گيرند و به هم هديه می‌دهند.

عيد پوريم

20مردخای تمام اين وقايع را نوشت و برای يهوديان سراسر مملكت پارس چه دور و چه نزديک فرستاد 21‏-22و از آنها خواست تا همه ساله روزهای چهاردهم و پانزدهم ادار را به مناسبت نجات يهود از چنگ دشمنانشان، جشن بگيرند و شادی نمايند، به يكديگر هديه بدهند و به فقيران كمک كنند، زيرا در چنين روزی بود كه غمشان به شادی، و ماتمشان به شادكامی تبديل شد.

23قوم يهود پيشنهاد مردخای را پذيرفتند و از آن پس، همه ساله اين روز را جشن گرفتند. 24اين روز به يهوديان يادآوری می‌كرد كه هامان پسر همداتای اجاجی و دشمن يهود برای نابودی آنان قرعه (كه به آن «پور» می‌گفتند) انداخته بود تا روز كشتارشان را تعيين كند؛ 25اما وقتی اين خبر به گوش پادشاه رسيد او فرمانی صادر كرد تا همان بلا بر سر هامان بيايد، پس هامان و پسرانش به دار كشيده شدند. 26(اين ايام «پوريم» ناميده می‌شود كه از كلمه «پور» به معنی قرعه، گرفته شده است.) با توجه به نامهٔ مردخای و آنچه كه اتفاق افتاده بود، 27يهوديان اين را به صورت رسم درآوردند كه خود و فرزندانشان و تمام كسانی كه به دين يهود می‌گروند اين دو روز را هر ساله طبق دستور مردخای جشن بگيرند. 28بنابراين، قرار بر اين شد كه يهوديان سراسر استانها و شهرها ايام «پوريم» را نسل اندر نسل هميشه به ياد آورند و آن را جشن بگيرند.

29در ضمن، ملكه استر با تمام اقتداری كه داشت نامهٔ مردخای را دربارهٔ برگزاری دائمی مراسم پوريم تأييد كرد. 30‏-31علاوه بر اين، نامه‌های تشويق‌آميز ديگری به تمام يهوديان ۱۲۷ استان مملكت پارس نوشته شد تا به موجب فرمان مردخای يهودی و ملكه استر، يهوديان و نسلهای آينده‌شان ايام «پوريم» را همه ساله نگه دارند. يهوديان روزه و سوگواری اين ايام را نيز به جا می‌آوردند. 32به اين ترتيب، مراسم ايام «پوريم» به فرمان استر تأييد شد و در تاريخ يهود ثبت گرديد.