አስቴር 9 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

አስቴር 9:1-32

የአይሁድ ድል ማድረግ

1አዳር በተባለው በዐሥራ ሁለተኛው ወር ዐሥራ ሦስተኛ ቀን፣ በንጉሡ ትእዛዝ የወጣው ዐዋጅ የሚፈጸምበት ዕለት ነበር። በዚህም ዕለት የአይሁድ ጠላቶች የበላይነቱን እንደሚያገኙ ተማምነው ነበር፤ ሁኔታው ግን ተለወጠና አይሁድ በሚጠሏቸው ላይ የበላይነትን አገኙ። 2የእነርሱን መጥፋት በሚፈልጉ ወገኖች ላይ አደጋ ለመጣል አይሁድ በንጉሥ ጠረክሲስ አውራጃዎች ሁሉ ባሉት ከተሞቻቸው ተሰበሰቡ። የሌሎቹ አገር ዜጎች ሕዝብ ሁሉ ፈርተዋቸው ስለ ነበር፣ ማንም ሊደፍራቸው አልቻለም። 3የየአውራጃው መኳንንት ሁሉ፣ እንደራሴዎች፣ የአውራጃ ገዦች እንዲሁም የንጉሡ አስተዳዳሪዎች አይሁድን ረዷቸው፤ ይህን ያደረጉትም መርዶክዮስን ስለ ፈሩ ነበር። 4መርዶክዮስ በቤተ መንግሥቱ ታዋቂ ሆነ፤ ዝናው በየአውራጃው ሁሉ ተሰማ፤ ኀይሉም እየበረታ ሄደ።

5ስለዚህ አይሁድ ጠላቶቻቸውን ሁሉ በሰይፍ እየመቱ ገደሏቸው፤ አጠፏቸውም፤ በሚጠሏቸውም ላይ ደስ ያላቸውን አደረጉ። 6አይሁድ በሱሳ ግንብ አምስት መቶ ሰው ገደሉ፤ አጠፉም። 7ፖርሻንዳታን፣ ደልፎንን፣ አስፓታን፣ 8ፖራታን፣ አዳልያን፣ አሪዳታን፣ 9ፓርማ ሽታን፣ አሪሳይን፣ አሪዳይንና ዋይዛታንም ገደሉ፤ 10እነዚህም የአይሁድ ጠላት የሆነው የሐመዳቱ ልጅ የሐማ ዐሥር ወንዶች ልጆች ነበሩ። በምርኮው ላይ ግን እጃቸውን አልዘረጉም።

11በሱሳ ግንብ የተገደሉት ሰዎች ብዛት በዚያኑ ዕለት ለንጉሡ ተነገረው። 12ንጉሡም ንግሥት አስቴርን፣ “አይሁድ በሱሳ ግንብ አምስት መቶ ሰውና ዐሥሩን የሐማ ልጆች ገድለዋል፤ አጥፍተዋልም። በተቀሩት በንጉሡ አውራጃዎችስ ምን አድርገው ይሆን? አሁንስ የምትለምኚው ምንድን ነው? ይሰጥሻል፤ የምትጠይቂውስ ምንድን ነው? ይፈቀድልሻል” አላት።

13አስቴርም፣ “ንጉሥን ደስ የሚያሰኘው ከሆነ፣ በሱሳ የሚኖሩ አይሁድ የዛሬውን ዐዋጅ ነገም እንዲደግሙት ፈቃድህ ይሁን፤ ዐሥሩ የሐማ ወንዶች ልጆችም ዕንጨት ላይ ይሰቀሉ” አለች።

14ንጉሡም ይህ እንዲሆን አዘዘ። በሱሳ ዐዋጅ ተነገረ፤ ዐሥሩንም የሐማ ወንዶች ልጆች ሰቀሏቸው። 15በሱሳ የሚኖሩ አይሁድ አዳር በተባለው ወር በዐሥራ አራተኛው ቀን በአንድነት መጡ፤ በሱሳም ሦስት መቶ ሰዎች ገደሉ፤ በምርኮው ላይ ግን እጃቸውን አልዘረጉም።

16በዚህ ጊዜ በሌሎች በንጉሡ አውራጃዎች የሚኖሩ የተቀሩት አይሁድ ራሳቸውን ለመከላከልና ከጠላቶቻቸውም ለመገላገል ተሰበሰቡ፤ ከሚጠሏቸውም ሰባ አምስት ሺሕ ገደሉ፤ በምርኮው ላይ ግን እጃቸውን አልዘረጉም። 17ይህ የሆነው አዳር በተባለው ወር ዐሥራ ሦስተኛ ቀን ነበር፤ በዐሥራ አራተኛው ቀን ዐረፉ፤ ዕለቱንም የተድላና የደስታ ቀን አድርገው ዋሉ።

የፉሪም በዓል መከበር

18በሱሳ የሚኖሩ አይሁድ ግን በዐሥራ ሦስተኛውና በዐሥራ አራተኛው ቀን ተሰብስበው ነበር፤ ከዚያም በዐሥራ አምስተኛው ቀን ዐረፉ፤ ዕለቱንም የተድላና የደስታ ቀን አድርገው ዋሉ።

19በየመንደሩ የሚኖሩ የገጠር አይሁድ፣ የአዳርን ወር ዐሥራ አራተኛ ቀን የተድላና የደስታ፣ እርስ በርሳቸውም ስጦታ የሚለዋወጡበት ቀን አድርገው የሚያከብሩት ከዚሁ የተነሣ ነው።

20መርዶክዮስ የተፈጸሙትን እነዚህን ድርጊቶች ጻፈ፤ ደብዳቤ አዘጋጅቶም በመላው የንጉሥ ጠረክሲስ አውራጃ በቅርብና በሩቅ ለሚገኙት አይሁድ ሁሉ ላከ፤ 21የላከውም የአዳርን ወር ዐሥራ አራተኛና ዐሥራ አምስተኛ ቀን በየዓመቱ እንዲያከብሩ ነው፤ 22የሚያከብሩበትም ምክንያት አይሁድ ከጠላቶቻቸው ዕረፍት ያገኙበት፣ ሐዘናቸው ወደ ደስታ፣ ልቅሷቸውም ወደ ክብረ በዓል የተለወጠበት ቀን ስለሆነ ነው። ቀኖቹንም የተድላና የደስታ ቀኖች አድርገው፣ እርስ በርሳቸውም የምግብ ስጦታ እየተለዋወጡና ለድኾችም ስጦታ እየሰጡ እንዲያከብሩ ጻፈላቸው።

23ስለዚህ አይሁድ መርዶክዮስ የጻፈላቸውን ለመፈጸምና የጀመሩትን በዓል ለማክበር ተስማሙ፤ 24ምክንያቱም የአይሁድ ሁሉ ጠላት የሆነው የአጋጋዊው የሐመዳቱ ልጅ ሐማ አይሁድን ለማጥፋት አሢሮ ነበር፤ ሊፈጃቸውና ሊያጠፋቸውም ፉር የተባለ ዕጣ ጥሎ ነበር። 25ሤራው በንጉሡ ዘንድ እንደ ታወቀ9፥25 ወይም፣ አስቴር በንጉሡ ፊት በወጣች ጊዜ ሐማ በአይሁድ ላይ የሸረበው ሤራ በገዛ ራሱ ላይ እንዲጠመጠም፣ እርሱና ወንዶች ልጆቹም በዕንጨት ላይ እንዲሰቀሉ የጽሑፍ ትእዛዝ አስተላለፈ። 26ስለዚህ እነዚህ ቀኖች ፉር ከሚለው ቃል “ፉሪም” ለመባል በቁ። በዚህ ደብዳቤ ስለ ተጻፈው ሁሉ፣ ስላዩትና ስለ ደረሰባቸውም ነገር ሁሉ፣ 27አይሁድ በታዘዘውና በተወሰነው ጊዜ እነርሱና ዘሮቻቸው፣ እነርሱን የተጠጓቸውም ሁሉ እነዚህን ሁለት ቀኖች በየዓመቱ ባለማቋረጥ እንዲያከብሩ ሥርዐት አድርገው ራሳቸው ወሰኑ። 28እነዚህም ቀኖች በእያንዳንዱ ትውልድ፣ በእያንዳንዱ ቤተ ሰብ፣ በእያንዳንዱ አውራጃና በእያንዳንዱ ከተማ መታሰብና መከበር ይኖርባቸዋል፤ ይኸውም እነዚህ የፉሪም ቀኖች በአይሁድ ዘንድ ሳይከበሩ እንዳይቀሩ፤ መታሰቢያቸውም ከዘሮቻቸው መካከል እንዳይደመሰስ ነው።

29ስለዚህ የአቢካኢል ልጅ ንግሥት አስቴር ከአይሁዳዊው ከመርዶክዮስ ጋር በመሆን፣ ፉሪምን አስመልክተው ይህችን ሁለተኛዪቱን ደብዳቤ ለማጽናት በሙሉ ሥልጣን ጻፉ። 30መርዶክዮስም የመልካም ምኞት መግለጫና ማረጋገጫ የሆነውን ደብዳቤ በጠረክሲስ ግዛት ውስጥ በሚገኙት አንድ መቶ ሃያ ሰባት አውራጃዎች ለሚኖሩት አይሁድ ሁሉ ላከ፤ 31የላከውም አይሁዳዊው መርዶክዮስና ንግሥት አስቴር ባወጁላቸውና እንደዚሁም የጾሙንና የሰቈቃውን ጊዜ በሚመለከት ለራሳቸውና ለዘራቸው ባጸኑት ውሳኔ መሠረት እነዚህ የፉሪም ቀኖች በተወሰነላቸው ጊዜ እንዲከበሩ ነው። 32የአስቴር ዐዋጅ ስለ ፉሪም የወጣውን ሥርዐት አጸና፤ ይህም በመዝገብ ተጻፈ።

New International Reader’s Version

Esther 9:1-32

1The king’s order had to be carried out on the 13th day of the 12th month. That was the month of Adar. On that day the enemies of the Jews had hoped to win the battle over them. But now everything had changed. The Jews had gained the advantage over those who hated them. 2The Jews gathered together in their cities. They gathered in all the territories King Xerxes ruled over. They came together to attack those who were trying to destroy them. No one could stand up against them. The people from all the other nations were afraid of them. 3All the nobles in the territories helped the Jews. So did the royal officials, the governors and the king’s officers. That’s because they were so afraid of Mordecai. 4He was well known in the palace. His fame spread all through the territories. So he became more and more important.

5The Jews struck down with swords all their enemies. They killed them and destroyed them. They did what they pleased to those who hated them. 6The Jews killed 500 men. They destroyed them in the fort of Susa. 7They also killed Parshandatha, Dalphon, Aspatha, 8Poratha, Adalia, Aridatha, 9Parmashta, Arisai, Aridai and Vaizatha. 10They were the ten sons of Haman. He was the son of Hammedatha. Haman had been the enemy of the Jews. They didn’t take anything that belonged to their enemies.

11A report was brought to the king that same day. He was told how many men had been killed in the fort of Susa. 12He said to Queen Esther, “The Jews have killed 500 men. They destroyed them in the fort of Susa. They also killed the ten sons of Haman there. What have they done in the rest of my territories? Now what do you want? I’ll give it to you. What do you want me to do for you? I’ll do that too.”

13“If it pleases you,” Esther answered, “let the Jews in Susa carry out today’s order tomorrow also. Stick poles through the dead bodies of Haman’s ten sons. Set them up where everyone can see them.”

14So the king commanded that it be done. An order was sent out in Susa. And the king’s men did to the bodies of Haman’s sons everything they were told to do. 15The Jews in Susa came together on the 14th day of the month of Adar. They put 300 men to death in Susa. But they didn’t take anything that belonged to those men.

16During that time, the rest of the Jews also gathered together. They lived in the king’s territories. They came together to fight for their lives. They didn’t want their enemies to bother them anymore. They wanted to get some peace and rest. So they killed 75,000 of their enemies. But they didn’t take anything that belonged to them. 17It happened on the 13th of Adar. On the 14th day they rested. They made it a day to celebrate with great joy. And they enjoyed good food.

18But the Jews in Susa had gathered together on the 13th and 14th. Then on the 15th they rested. They made it a day to celebrate with great joy. And they enjoyed good food.

19That’s why Jews who live out in the villages celebrate on the 14th of Adar. They celebrate that day with great joy. And they enjoy good food. They also give presents to each other on that day.

Purim Is Celebrated

20Mordecai wrote down these events. He sent letters to all the Jews all through the territories of King Xerxes. It didn’t matter whether the Jews lived nearby or far away. 21Mordecai told them to celebrate the 14th and 15th days of the month of Adar. He wanted them to do it every year. 22Mordecai told the Jews to celebrate the time when they got rest from their enemies. That was the month when their sadness was turned into joy. It was when their weeping turned into a day for celebrating. He wrote the letters to celebrate those days as times of joy. He wanted the people to enjoy good food. He told them to give presents of food to one another. He also wanted them to give gifts to people who were poor.

23So the Jews agreed to continue the celebrating they had started. They kept doing what Mordecai had written to them. 24Haman was the son of Hammedatha, the Agagite. He had been the enemy of all the Jews. He had planned to destroy them. He had cast the lot to destroy them completely. The lot was called Pur. 25But the king had found out about Haman’s evil plan. So the king had sent out written orders. He had ordered that Haman’s evil plan against the Jews should happen to him instead. The king also commanded that poles be stuck through the dead bodies of Haman and his sons. Then they should be set up where everyone could see them. 26The days the Jews were celebrating were called Purim. Purim comes from the word Pur. Pur means Lot. Now the Jews celebrate these two days every year. They do it because of everything that was written in Mordecai’s letter. They also do it because of what they had seen and what had happened to them. 27So they established it as a regular practice. They decided they would always observe these two days of the year. They would celebrate in the required way. And they would celebrate at the appointed time. They and their children after them would always observe these days. And so would all who join them. 28The days should be remembered and celebrated. They should be remembered by every family for all time to come. They should be celebrated in every territory and in every city. The Jews should never stop celebrating the days of Purim. Their children after them should always remember these days.

29So Queen Esther, the daughter of Abihail, wrote a second letter. She wrote it together with Mordecai the Jew. They wanted to give their full authority to this second letter about Purim. 30Mordecai sent letters to all the Jews in the 127 territories of the kingdom of Xerxes. The letters had messages of kindness and hope in them. 31The letters established the days of Purim at their appointed times. They spoke about what Mordecai the Jew and Queen Esther had ordered the people to do. Everything should be done in keeping with the directions the Jews had set up for themselves and their children after them. The directions applied to their times of fasting and sadness. 32Esther’s order established the rules about Purim. It was written down in the records.